አስቴር 7 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

አስቴር 7:1-10

ሐማ ተሰቀለ

1ስለዚህ ንጉሡና ሐማ ከንግሥት አስቴር ጋር ለመጋበዝ ሄዱ፤ 2በሁለተኛውም ቀን የወይን ጠጅ እየጠጡ ሳለ፣ ንጉሡ እንደ ገና፣ “ንግሥት አስቴር ሆይ፤ የምትለምኚው ምንድን ነው? ይሰጥሻል፤ የምትጠይቂውስ ምንድን ነው? እስከ መንግሥቴ እኩሌታ እንኳ ቢሆን ይደረግልሻል” አላት።

3ከዚያም ንግሥት አስቴር እንዲህ ስትል መለሰች፤ “ንጉሥ ሆይ፤ በፊትህ ሞገስ አግኝቼና ግርማዊነትህን ደስ የሚያሰኝ ከሆነ፣ ሕይወቴን ታደጋት፤ ልመናዬ ይህ ነው፤ ሕዝቤን አትርፍ፤ ጥያቄዬም ይኸው ነው። 4እኔና ሕዝቤ ለጥፋት፣ ለዕርድና ለመደምሰስ ተሸጠናልና። ወንዶችና ሴቶች ባሮች ለመሆን የተሸጥን ቢሆን ኖሮ፣ ዝም ባልሁ ነበር፤ ምክንያቱም እንዲህ ያለው ጭንቀት ንጉሡን ለማስቸገር የሚበቃ አይደለም7፥4 ወይም፣ ዝም ባልሁም ነበር፤ ነገር ግን ባለጋራችን የሚሰጠው ካሣ ንጉሡ ከሚያጣው ነገር ጋር ከቶ አይነጻጸርም።”

5ንጉሥ ጠረክሲስም ንግሥት አስቴርን፣ “ለመሆኑ እርሱ ማን ነው? እንዲህ ያለውን ነገር ለማድረግ እስከዚህ የደፈረውስ ሰው የታለ?” ሲል ጠየቀ።

6አስቴርም፣ “ያ ባላጋራና ጠላት ይህ ክፉው ሐማ ነው” አለች።

ከዚያም ሐማ በንጉሡና በንግሥቲቱ ፊት እጅግ ደነገጠ። 7ንጉሡ ከተቀመጠበት በቍጣ ተነሣ፤ የወይን ጠጁንም ትቶ ወደ ቤተ መንግሥቱ የአትክልት ቦታ ሄደ። ሐማ ግን ንጉሡ ሊያጠፋው ቈርጦ መነሣቱን ስላወቀ፣ ንግሥት አስቴር ሕይወቱን እንድታተርፍለት ለመማጠን በዚያው ቀረ።

8ንጉሡ ከቤተ መንግሥቱ የአትክልት ቦታ ወደ ግብዣው አዳራሽ ሲመለስ አስቴር ደገፍ ባለችበት ድንክ ዐልጋ ላይ ሐማ ተደፍቶ ነበር።

ንጉሡም፣ “ይባስ ብሎ አብራኝ ያለችውን ንግሥት በገዛ ቤቴ ሊደፍራት ያስባልን?” ሲል ተናገረ።

ይህ ቃል ከንጉሡ አፍ ገና እንደ ወጣ፣ የሐማን ፊት ሸፈኑት። 9ከዚያም ንጉሡን በቅርብ ከሚያገለግሉት ጃንደረቦች አንዱ የሆነው ሐርቦና፣ “እነሆ ቁመቱ አምሳ ክንድ7፥9 23 ሜትር ያህል ነው። የሆነ ግንድ በሐማ ቤት አጠገብ ተተክሏል፤ ይህን ያዘጋጀው ንጉሡን ለማዳን በጎ ነገር ለተናገረው ለመርዶክዮስ ነው” አለ።

ንጉሡም፣ “በዚሁ ላይ ስቀሉት” አለ። 10ስለዚህ ለመርዶክዮስ ባዘጋጀው ግንድ ላይ ሐማን ሰቀሉት፤ ከዚያም የንጉሡ ቍጣ በረደ።

Thai New Contemporary Bible

เอสเธอร์ 7:1-10

ฮามานถูกแขวนคอ

1ดังนั้นกษัตริย์และฮามานก็มาร่วมรับประทานอาหารกับพระนางเอสเธอร์ 2ขณะที่ผู้คนกำลังดื่มเหล้าองุ่นกันอยู่ในงานเลี้ยงวันที่สอง กษัตริย์ตรัสถามพระนางอีกว่า “ราชินีเอสเธอร์ เจ้าจะขอสิ่งใดหรือ? เราจะให้ เจ้าปรารถนาอะไร? เราจะยกให้ แม้ถึงกึ่งราชสมบัติ”

3ราชินีเอสเธอร์จึงทูลว่า “ข้าแต่กษัตริย์ หากหม่อมฉันเป็นที่โปรดปรานและหากฝ่าพระบาทจะทรงกรุณา หม่อมฉันขอฝ่าพระบาททรงไว้ชีวิตหม่อมฉัน และหม่อมฉันปรารถนาให้ฝ่าพระบาทไว้ชีวิตพี่น้องร่วมชาติของหม่อมฉันด้วย 4เพราะหม่อมฉันกับพี่น้องร่วมชาติถูกขายให้ถึงแก่ความพินาศย่อยยับและถูกฆ่าล้างผลาญสิ้นชาติ หากเราเพียงแต่ถูกขายเป็นทาสชายหญิง หม่อมฉันอาจจะทนนิ่งอยู่ เพราะความทุกข์ของเราเช่นนั้นไม่เป็นเหตุอันควรที่จะทำให้กษัตริย์ต้องรำคาญพระทัย7:4 หรือทนนิ่งอยู่ แต่กษัตริย์จะทรงสูญเสียอย่างที่ศัตรูของเราไม่อาจชดเชยให้ได้

5กษัตริย์เซอร์ซีสตรัสถามพระนางเอสเธอร์ว่า “ผู้นั้นคือใคร? คนที่บังอาจทำเช่นนั้นอยู่ที่ไหน?”

6เอสเธอร์กราบทูลว่า “ฮามานคนชั่วนี่แหละเป็นศัตรูของเรา”

ฮามานตกใจกลัวมากต่อหน้ากษัตริย์และพระราชินี 7กษัตริย์ทรงผลุนผลันลุกขึ้นยืนด้วยพระพิโรธ ทิ้งเหล้าองุ่นและเสด็จเข้าไปในราชอุทยาน ขณะที่ฮามานวิงวอนขอชีวิตจากพระนางเอสเธอร์เพราะรู้ตัวว่ากษัตริย์ได้ตัดสินชะตากรรมของเขาแล้ว

8ฮามานหมอบกราบลงบนตั่งซึ่งพระนางเอสเธอร์กำลังเอนพระองค์อยู่ด้วยความสิ้นหวัง พอดีกับที่กษัตริย์เสด็จกลับจากราชอุทยานมายังบริเวณงานเลี้ยง

กษัตริย์ตรัสว่า “นี่มันจะขืนใจราชินีในขณะที่พระนางอยู่กับเราในวังเลยเชียวหรือ?”

เมื่อกษัตริย์ตรัสจบก็มีคนเอาผ้ามาคลุมหน้าฮามานไว้ 9แล้วขันทีฮารโบนาซึ่งถวายงานรับใช้แด่กษัตริย์เข้ามาทูลว่า “ขอเดชะ ฮามานเพิ่งสั่งให้สร้างตะแลงแกงสูง 50 ศอก7:9 คือ ประมาณ 23 เมตรในลานบ้าน เพื่อแขวนคอโมรเดคัยผู้ที่มารายงานเพื่อช่วยกษัตริย์”

กษัตริย์จึงตรัสว่า “แขวนคอฮามานบนนั้นแหละ!” 10พวกเขาก็แขวนฮามานไว้บนตะแลงแกงที่เขาเตรียมไว้สำหรับโมรเดคัย แล้วพระพิโรธของกษัตริย์ก็สงบลง