አስቴር 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

አስቴር 4:1-17

መርዶክዮስ የአስቴርን ርዳታ ጠየቀ

1መርዶክዮስ የተደረገውን ሁሉ ባወቀ ጊዜ፣ ልብሱን ቀደደ፤ ከዚያም ማቅ ለብሶ፣ በራሱ ላይ ዐመድ ነስንሶ ድምፁን ከፍ በማድረግ አምርሮ እየጮኸ ወደ ከተማዪቱ መካከል ወጣ። 2ማቅ የለበሰ እንዲገባ ስለማይፈቀድለት፣ የሄደው እስከ ንጉሡ በር ድረስ ብቻ ነበር። 3የንጉሡ ዐዋጅና ትእዛዝ በደረሰበት አውራጃ ሁሉ፣ በአይሁድ መካከል ታላቅ ሐዘን ሆነ፤ ጾሙ፤ አለቀሱ፤ ጮኹም። ብዙዎቹም ማቅና ዐመድ ላይ ተኙ።

4የአስቴር ደንገጡሮችና ጃንደረቦች መጥተው ስለ መርዶክዮስ በነገሯት ጊዜ፣ እጅግ ዐዘነች፤ እርሷም በማቁ ፈንታ የሚለብሰውን ልብስ ላከችለት፤ እርሱ ግን አልተቀበላቸውም። 5ከዚያም አስቴር ከንጉሡ ጃንደረቦች መካከል እርሷን እንዲያገለግል የተመደበውን ሀታክን ጠርታ፣ መርዶክዮስ ምን ችግር እንደ ገጠመውና ስለ ምንስ እንደዚህ እንደ ሆነ እንዲያጣራ ላከችው።

6ስለዚህ ሀታክ በንጉሡ በር ፊት ለፊት ወደሚገኘው ወደ ከተማዪቱ አደባባይ ወደ መርዶክዮስ ወጣ። 7መርዶክዮስ የደረሰበትን ነገር ሁሉ፣ እንዲሁም ሐማ የአይሁድን ሕዝብ ለማጥፋት ወደ ንጉሡ ግምጃ ቤት ለማግባት ቃል የገባውን የገንዘብ ልክ ጭምር ነገረው። 8አይሁድን ለማጥፋት በሱሳ የወጣውን የዋናውን ዐዋጅ ቅጅም ለአስቴር እንዲያሳያትና በዝርዝር እንዲያስረዳት ሰጠው፤ ወደ ንጉሡም ዘንድ ገብታ ስለ ሕዝቧ ምሕረት እንድትጠይቅና እንድትማልድ አጥብቆ ይነግራት ዘንድ አሳሰበው።

9ሀታክም ተመልሶ መርዶክዮስ የነገረውን ሁሉ ለአስቴር አስታወቃት። 10እርሷም ለመርዶክዮስ እንዲህ እንዲለው ነገረችው፤ 11“የንጉሡ ባሮችና በንጉሡ አውራጃዎች የሚገኙ ሰዎች ሁሉ ወንድም ሆነ ሴት፣ ማንም ሰው ሳይጠራ ንጉሡ ወዳለበት ወደ ውስጠኛው አደባባይ የሚገባ፣ ንጉሡ አንድ ሕግ ብቻ እንዳለው ያውቃል፤ ይኸውም እንዲህ ያደረገው ሰው ይገደላል፤ አንድ ሰው ከእንዲህ ዐይነቱ ሞት የሚተርፈው፣ ንጉሡ የወርቅ ዘንጉን ሲዘረጋለት ብቻ ነው። እኔ ግን ወደ ንጉሡ ዘንድ እንድገባ ከተጠራሁ ከሠላሳ ቀን በላይ ሆነ።”

12የአስቴር ቃል ለመርዶክዮስ በተነገረው ጊዜ፣ 13ይህን መልስ ላከባት፤ “አንቺ በንጉሥ ቤት በመሆንሽ ብቻ ሌላው የአይሁድ ሕዝብ ሲጠፋ አንቺ የምትተርፊ እንዳይመስልሽ፤ 14በዚህ ጊዜ አንቺ ዝም ብትዪ፣ ለአይሁድ ርዳታና ትድግና ከሌላ ስፍራ ይመጣላቸዋል፤ አንቺና የአባትሽ ቤት ግን ትጠፋላችሁ፤ ደግሞስ አንቺ ንግሥት ለመሆን የበቃሽው ለዚህ ጊዜ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?”

15ከዚያም አስቴር ለመርዶክዮስ ይህን መልስ ላከችበት፤ 16“ሂድና በሱሳ ያሉትን አይሁድ ሁሉ በአንድነት ሰብስብ፤ ስለ እኔም ጹሙልኝ፤ ቀንም ይሁን ሌሊት ለሦስት ቀን አትብሉ፤ አትጠጡም። እኔና ደንገጡሮቼም እናንተ እንደምታደርጉት ሁሉ እንጾማለን፤ ይህ ከተፈጸመ በኋላ ግን ነገሩ ምንም እንኳ ከሕግ ውጭ ቢሆንም፣ ወደ ንጉሡ ዘንድ እሄዳለሁ፤ ከጠፋሁም ልጥፋ።”

17ስለዚህ መርዶክዮስ ሄደ፤ የአስቴርንም ትእዛዝ ሁሉ ፈጸመ።

Thai New Contemporary Bible

เอสเธอร์ 4:1-17

โมรเดคัยขอให้เอสเธอร์ช่วย

1เมื่อโมรเดคัยรู้สิ่งที่เกิดขึ้นทั้งหมด ก็ฉีกเสื้อผ้า นุ่งห่มผ้ากระสอบ โปรยขี้เถ้าใส่ตัว และเข้าไปในตัวเมือง ร้องไห้เสียงดังอย่างรันทด 2แต่โมรเดคัยมาได้แค่ที่ประตูพระราชวังเท่านั้น เพราะผู้สวมเสื้อผ้ากระสอบจะไม่ได้รับอนุญาตให้ผ่านเข้าไป 3ชาวยิวทั้งหลายในทุกมณฑลซึ่งพระราชโองการของกษัตริย์ไปถึงก็ทุกข์โศกแสนสาหัส พวกเขาอดอาหาร ร้องไห้คร่ำครวญ หลายคนนุ่งห่มผ้ากระสอบและนอนบนกองขี้เถ้า

4เมื่อนางกำนัลและขันทีของเอสเธอร์มาทูลเรื่องโมรเดคัย พระนางก็ทรงทุกข์โศกยิ่งนัก จึงประทานเสื้อผ้าไปให้โมรเดคัยผลัดเปลี่ยนแทนผ้ากระสอบ แต่เขาไม่ยอมรับเสื้อผ้าเหล่านั้น 5เอสเธอร์จึงให้ตามตัวขันทีฮาธาคซึ่งมีหน้าที่รับใช้พระนางและบัญชาให้เขาออกไปพบโมรเดคัยเพื่อไต่ถามถึงสาเหตุและความทุกข์ร้อนของเขา

6ฮาธาคจึงออกไปพบโมรเดคัยที่ลานเมืองหน้าประตูพระราชวัง 7โมรเดคัยเล่าทุกสิ่งที่เกิดขึ้น รวมทั้งเรื่องจำนวนเงินที่ฮามานสัญญาจะมอบเข้าพระคลังหลวงเพื่อการทำลายล้างชาวยิว 8โมรเดคัยยังมอบสำเนาพระราชโองการที่ประกาศในป้อมเมืองสุสาให้ทำลายล้างชาวยิวแก่ฮาธาค กำชับให้นำไปมอบแด่เอสเธอร์และให้ทูลความเป็นไป พร้อมทั้งให้ฮาธาคเร่งพระนางให้เสด็จไปเข้าเฝ้ากษัตริย์ เพื่อทูลวิงวอนสำหรับพี่น้องร่วมชาติของพระนาง

9ฮาธาคนำความจากโมรเดคัยกลับไปทูลเอสเธอร์ 10เอสเธอร์สั่งเขาให้กลับมาบอกโมรเดคัยว่า 11“ข้าราชบริพารและประชาชนทั้งปวงย่อมรู้กฎดีว่า ผู้ใดก็ตามไม่ว่าชายหรือหญิงที่ล่วงล้ำเข้าไปในพระราชฐานชั้นในโดยไม่มีหมายเรียกให้เข้าเฝ้าย่อมมีโทษถึงตาย เว้นแต่กษัตริย์จะทรงยื่นคทาทองคำออกมาโปรด กษัตริย์ไม่ได้ตรัสเรียกข้าพเจ้าเข้าเฝ้ามากว่าสามสิบวันแล้ว”

12เมื่อมีคนนำคำตรัสของเอสเธอร์มาบอกกับโมรเดคัย 13โมรเดคัยตอบกลับมาว่า “อย่าคิดว่าเจ้าอยู่ในราชวังนี้แล้วจะเป็นชาวยิวคนเดียวที่รอดพ้นไปได้ 14หากเจ้านิ่งเงียบอยู่ในยามนี้ การกอบกู้และปลดปล่อยชาวยิวจะมาจากแหล่งอื่น ส่วนเจ้ากับครอบครัวของบิดาของเจ้าจะพินาศ บางทีที่เจ้ามารับตำแหน่งราชินีก็เพื่อยามคับขันนี้ก็เป็นได้ ใครจะรู้?”

15แล้วเอสเธอร์จึงให้คนมาบอกโมรเดคัยว่า 16“ขอให้ท่านรวบรวมชาวยิวทั้งหมดในป้อมเมืองสุสาให้ถืออดอาหารเพื่อข้าพเจ้า อย่ากินหรือดื่มอะไรตลอดสามวันสามคืน ข้าพเจ้ากับเหล่านางกำนัลก็จะถืออดอาหารเช่นเดียวกัน หลังจากนั้นข้าพเจ้าจะไปเข้าเฝ้ากษัตริย์ แม้ขัดกับกฎหมายก็ตามที ถ้าข้าพเจ้าต้องพินาศ ข้าพเจ้าก็ยอม”

17ดังนั้นโมรเดคัยจึงไปทำตามที่เอสเธอร์รับสั่ง