አስቴር 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

አስቴር 2:1-23

አስቴር ንግሥት ሆነች

1ከዚህ በኋላ ንጉሡ ጠረክሲስ ቍጣው ሲበርድለት አስጢንን፣ ያደረገችውን ነገርና በእርሷም ላይ ያስተላለፈውን ዐዋጅ ዐሰበ። 2ከዚያም የንጉሡ የቅርብ አገልጋዮች እንዲህ የሚል ሐሳብ አቀረቡ፤ “ለንጉሡ ቈንጆ ልጃገረዶች ይፈለጉለት፤ 3እነዚህን ሁሉ ቈንጆ ልጃገረዶች በሱሳ ግንብ ወደሚገኘው ልዩ የሴቶች መኖሪያ ቦታ እንዲያመጡ፣ ንጉሡ በግዛቱ በሚገኙት አውራጃዎቹ ሁሉ ባለ ሥልጣኖችን ይሹም፤ እነርሱም የሴቶች የበላይ ኀላፊ በሆነው በንጉሡ ጃንደረባ በሄጌ ኀላፊነት ሥር ይሁኑ፤ የውበትም እንክብካቤ ይደረግላቸው። 4ከዚያም ንጉሡን ደስ የምታሰኘው ልጃገረድ በአስጢን ፈንታ ንግሥት ትሁን።” ምክሩ ንጉሡን ደስ አሰኘው፤ በተባለውም መሠረት አደረገ።

5በዚህ ጊዜ ከብንያም ነገድ የቂስ ልጅ፣ የሰሜኢ ልጅ፣ የኢያዕር ልጅ መርዶክዮስ የሚባል አንድ አይሁዳዊ በሱሳ ግንብ ይኖር ነበር፤ 6እርሱም የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ከማረካቸው ከይሁዳ ንጉሥ ከኢኮንያን2፥6 በዕብራይስጥ፣ ኢኮንያን የሚለው ስም ኢዮአቄም ከሚለው ጋር አንድ ዐይነት ነው። ጋር ከኢየሩሳሌም በምርኮ ከተወሰዱት አንዱ ነበር። 7መርዶክዮስ አንዲት ሀደሳ የምትባል የአጎቱ ልጅ ነበረችው፤ አባትና እናት ስላልነበራት፣ ያሳደጋት እርሱ ነበር። አስቴር ተብላ የምትጠራው ይህች ልጃገረድ በተክለ ሰውነቷም ሆነ በመልኳ እጅግ ውብ ነበረች። አባቷና እናቷ ከሞቱ በኋላ መርዶክዮስ እንደ ራሱ ልጅ አድርጎ ወሰዳት።

8የንጉሡ ትእዛዝና ዐዋጅ በወጣ ጊዜ፣ ብዙ ልጃገረዶች ወደ ሱሳ ግንብ ተወስደው ለጠባቂው ለሄጌ ተሰጡ፤ አስቴርም ወደ ንጉሡ ቤተ መንግሥት ተወስዳ፣ ለሴቶቹ ጠባቂ ለሄጌ በዐደራ ተሰጠች። 9ልጃገረዲቱም ደስ አሰኘችው፤ በእርሱም ዘንድ መወደድን አተረፈች፤ እርሱም የውበት መንከባከቢያዋንና የተለየ ምግብ ወዲያውኑ ሰጣት። ከቤተ መንግሥቱ የተመረጡ ሰባት ደንገጡሮችን በመመደብም እርሷንና ደንገጡሮቿን ምርጥ ወደ ሆነው የሴቶች መጠበቂያ አዛወረ።

10መርዶክዮስ እንዳትናገር አዝዟት ስለ ነበር፣ አስቴር የየት አገር ሰውና የእነማን ወገን እንደ ሆነች አልገለጸችም። 11መርዶክዮስም አስቴር እንዴት እንደ ሆነችና ምንስ እንዳጋጠማት ለማወቅ፣ በየዕለቱ በሴቶች መጠበቂያ አደባባይ አጠገብ ወዲያና ወዲህ ይመላለስ ነበር።

12አንዲት ልጃገረድ ወደ ንጉሥ ጠረክሲስ ዘንድ ለመግባት ተራዋ ከመድረሱ በፊት ስድስት ወር በከርቤ ዘይት፣ ስድስት ወር ደግሞ ልዩ ልዩ ሽቱ በመቀባትና በተለያዩ የፊት ቀለሞች በመዋብ በአጠቃላይ ዐሥራ ሁለት ወር መቈየት ነበረባት፤ 13ወደ ንጉሡ ዘንድ የምትገባውም በዚህ ሁኔታ ሲሆን፣ ሴቶቹ ከሚኖሩበት ስፍራ ወደ ንጉሡ ቤተ መንግሥት ስትሄድ፣ መውሰድ የምትፈልገው ማናቸውም ነገር ይሰጣት ነበር። 14ሲመሽ ወደዚያው ትሄዳለች፤ ሲነጋም የቁባቶች ኀላፊ በሆነው በንጉሡ ጃንደረባ በሻአሽጋዝ ጥበቃ ሥር ወደሚገኘው ወደ ሌላው የሴቶች መጠበቂያ ቤት ትመለሳለች፤ ደስ የተሰኘባት ካልሆነችና በስሟም ካልጠራት ዳግመኛ ወደ ንጉሡ ዘንድ አትገባም።

15መርዶክዮስ እንደ ልጁ አድርጎ ያሳደጋት የአጎቱ የአቢካኢል ልጅ አስቴር ወደ ንጉሡ ዘንድ የምትሄድበት ተራ በደረሰ ጊዜ የሴቶች ልዩ ጥበቃ ቤት ኀላፊ የሆነው ሄጌ የነገራትን እንጂ፣ ሌላ ምንም አልጠየቀችም። አስቴር በሚያዩዋት ሁሉ ዘንድ ሞገስ አገኘች። 16በነገሠ በሰባተኛው ዓመት ቴቤት በተባለው በዐሥረኛው ወር ወደ ንጉሥ ጠረክሲስ ቤተ መንግሥት ተወሰደች።

17በዚህ ጊዜ ንጉሡ ከሌሎቹ ሴቶች ሁሉ ይበልጥ አስቴርን ወደዳት፤ ከሌሎቹ ደናግልም ሁሉ ይልቅ በእርሱ ዘንድ ሞገስንና መወደድን አገኘች። ስለዚህ የእቴጌነት ዘውድ በራሷ ላይ ጫነላት፤ በአስጢንም ፈንታ ንግሥት አደረጋት። 18ንጉሡም ስለ አስቴር ክብር ለመኳንንቱና ለሹማምቱ ሁሉ ታላቅ ግብዣ አደረገ፤ በዓሉም በየአውራጃዎቹ ሁሉ እንዲከበር ዐወጀ፤ በንጉሣዊ ልግስናውም ስጦታ አደረገ።

መርዶክዮስ በንጉሡ ላይ የተጠነሰሰውን ሤራ ደረሰበት

19ደናግሉ ለሁለተኛ ጊዜ ተሰብስበው ሳለ፣ መርዶክዮስ በንጉሡ በር ተቀምጦ ነበር። 20አስቴር ግን ልክ መርዶክዮስ እንደ ነገራት የማን ወገንና የየት አገር ሰው እንደ ሆነች ደብቃ ነበር፤ ይህ የሆነበት ምክንያት መርዶክዮስ በሚያሳድጋት ጊዜ ታደርግ እንደ ነበረው ሁሉ፣ አሁንም ምክሩን ትከተል ስለ ነበር ነው።

21መርዶክዮስ በንጉሡ በር ተቀምጦ ሳለ፣ በሩን ከሚጠብቁት ከንጉሡ የጦር አለቆች ሁለቱ ገበታና ታራ ተቈጡ፤ ንጉሥ ጠረክሲስንም ለመግደል ዶለቱ። 22መርዶክዮስም አድማውን ስለ ደረሰበት፣ ለንግሥት አስቴር ገለጠላት፤ እርሷም ይህን ከመርዶክዮስ ማግኘቷን ለንጉሡ ገልጣ ነገረችው። 23ነገሩ ሲጣራም እውነት ሆኖ ተገኘ፤ ሁለቱም ሹማምት በስቅላት ሞት ተቀጡ። ይህ ሁሉ በንጉሡ ፊት በታሪክ መዝገብ ተጻፈ።

Thai New Contemporary Bible

เอสเธอร์ 2:1-23

เอสเธอร์ได้รับเลือกเป็นราชินี

1ต่อมาเมื่อพระพิโรธของกษัตริย์เซอร์ซีสสงบลงแล้ว พระองค์ทรงคิดถึงพระนางวัชที ตลอดจนสิ่งที่พระนางได้ทำและพระราชโองการของพระองค์เองเกี่ยวกับพระนาง 2แล้วข้าราชบริพารส่วนพระองค์จึงทูลเสนอว่า “ควรเฟ้นหาหญิงสาวพรหมจารีผู้งดงามมาถวายกษัตริย์ 3ขอทรงตั้งเจ้าพนักงานในแต่ละมณฑลของอาณาจักรของพระองค์ให้เฟ้นหาตัวหญิงสาวโฉมงามทั้งหมด และนำตัวมายังฮาเร็มในป้อมเมืองสุสา ให้อยู่ในความดูแลของเฮกัยขันทีของกษัตริย์ซึ่งรับผิดชอบเกี่ยวกับเหล่าสตรี และให้พวกนางรับการประทินโฉม 4หลังจากนั้นให้สตรีซึ่งฝ่าพระบาทโปรดปรานเป็นราชินีแทนพระนางวัชที” กษัตริย์ก็พอพระทัยความคิดนี้และให้ลงมือปฏิบัติ

5ครั้งนั้นในป้อมเมืองสุสา มีชายชาวยิวจากเผ่าเบนยามินคนหนึ่งชื่อโมรเดคัย ผู้เป็นบุตรของยาอีร์ ผู้เป็นบุตรของชิเมอี ผู้เป็นบุตรของคีช 6เขาถูกจับมาเป็นเชลยเมื่อครั้งกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนทรงกวาดต้อนเชลยมาจากเยรูซาเล็มพร้อมกษัตริย์เยโฮยาคีน2:6 ภาษาฮีบรูว่าเยโคนิยาห์เป็นอีกรูปหนึ่งของเยโฮยาคีนแห่งยูดาห์ 7โมรเดคัยมีลูกพี่ลูกน้องเป็นหญิงสาวรูปโฉมงามน่ารักชื่อ ฮาดัสสาห์หรือเอสเธอร์ เขาเลี้ยงดูนางเป็นบุตรสาวบุญธรรมหลังจากที่บิดามารดาของนางสิ้นชีวิต

8เนื่องด้วยพระราชโองการของกษัตริย์ หญิงสาวหลายคนจึงถูกนำมาอยู่ที่ป้อมเมืองสุสาในความดูแลของเฮกัย และเอสเธอร์ก็ถูกนำมาที่พระราชวังของกษัตริย์และอยู่ในความดูแลของเฮกัยผู้ดูแลฮาเร็มเช่นกัน 9เฮกัยเอ็นดูและพอใจเอสเธอร์มาก เขาจึงรีบจัดหาเครื่องประทินโฉมและอาหารพิเศษให้นางทันที ทั้งจัดเด็กหญิงเจ็ดคนซึ่งคัดเลือกจากพระราชวังมาคอยรับใช้นาง และให้นางกับสาวใช้ย้ายไปอยู่ที่ที่ดีที่สุดในฮาเร็ม

10เอสเธอร์ไม่ได้เปิดเผยเรื่องเชื้อชาติและภูมิหลังครอบครัวของนางเพราะโมรเดคัยสั่งห้ามไว้ 11ทุกวันโมรเดคัยจะเดินวนเวียนแถวๆ ลานฮาเร็ม เพื่อถามข่าวคราวและความเป็นไปของเอสเธอร์

12ก่อนถึงเวรที่หญิงสาวแต่ละคนเข้าเฝ้ากษัตริย์เซอร์ซีส พวกนางจะต้องรับการประทินโฉมครบสิบสองเดือนตามที่กำหนดไว้คือ หกเดือนแรกบำรุงด้วยน้ำมันมดยอบ จากนั้นบำรุงด้วยน้ำหอมและเครื่องประทินผิวอีกหกเดือน 13เมื่อถึงรอบที่แต่ละคนจะเข้าเฝ้ากษัตริย์ จะขอนำอะไรจากฮาเร็มไปพระราชวังด้วยก็ได้ 14ในเวลาเย็นนางจะเข้าวัง และเช้าวันรุ่งขึ้นจะกลับไปอยู่อีกตำหนักหนึ่งในฮาเร็มซึ่งอยู่ในความดูแลของชาอัชกาสขันทีของกษัตริย์ผู้คอยดูแลพวกสนม นางจะไม่ได้เฝ้ากษัตริย์อีกเว้นเสียแต่ว่าพระองค์ทรงโปรดและเอ่ยนามเรียกตัวนางมาเข้าเฝ้า

15เมื่อถึงรอบของเอสเธอร์ที่จะเข้าเฝ้ากษัตริย์ (หญิงสาวที่โมรเดคัยรับเป็นบุตรบุญธรรม นางเป็นบุตรสาวของอาบีฮายิล ผู้เป็นลุงของโมรเดคัย) นางไม่ได้ขอสิ่งใดนอกจากที่ขันทีเฮกัยผู้ดูแลฮาเร็มแนะนำ และทุกคนที่เห็นเอสเธอร์ก็ชื่นชอบนาง 16เอสเธอร์ถูกนำมาเข้าเฝ้ากษัตริย์เซอร์ซีสในพระราชวังเมื่อเดือนเทเบท ซึ่งเป็นเดือนที่สิบปีที่เจ็ดแห่งรัชกาล

17กษัตริย์พอพระทัยเอสเธอร์มากกว่าหญิงอื่นทั้งปวง พระองค์โปรดปรานและพอพระทัยนางมากกว่าหญิงพรหมจารีคนอื่นๆ จึงสวมมงกุฎให้และตั้งนางเป็นราชินีแทนพระนางวัชที 18และกษัตริย์ทรงจัดงานเลี้ยงใหญ่ประทานแก่ขุนนางและข้าราชบริพารทั้งปวงเพื่อเอสเธอร์ พระองค์ทรงประกาศวันหยุดทั่วทุกมณฑล และประทานของขวัญด้วยพระทัยกว้างขวาง

โมรเดคัยทูลเรื่องแผนการของคนร้าย

19เมื่อมีการเฟ้นตัวหญิงสาวพรหมจารีครั้งที่สอง โมรเดคัยนั่งประจำอยู่ที่ประตูพระราชวัง 20แต่เอสเธอร์ยังคงไม่เปิดเผยเชื้อชาติและภูมิหลังครอบครัวของพระนางตามที่โมรเดคัยสั่งไว้ พระนางยังคงปฏิบัติตามคำสั่งของโมรเดคัยเหมือนตอนที่เขายังเลี้ยงดูพระนาง

21ในช่วงที่โมรเดคัยนั่งประจำอยู่ที่ประตูพระราชวัง ข้าราชการสองคนซึ่งเป็นยามเฝ้าประตู คือบิกธานา2:21 ภาษาฮีบรูว่าบิกธานเป็นอีกรูปหนึ่งของบิกธานาและเทเรช มีเรื่องแค้นเคืองและคบคิดกันจะลอบปลงพระชนม์กษัตริย์เซอร์ซีส 22แต่โมรเดคัยล่วงรู้และนำความไปแจ้งพระนางเอสเธอร์ พระนางจึงขึ้นกราบทูลกษัตริย์และทูลว่าเป็นความดีความชอบของโมรเดคัย 23มีการสอบสวนเรื่องนี้และพบว่าเป็นความจริง ข้าราชบริพารทั้งสองจึงถูกแขวนคอที่ตะแลงแกง2:23 หรือถูกแขวน(หรือถูกเสียบ)ไว้บนเสาเหมือนที่อื่นๆ ในพระธรรมเอสเธอร์ เรื่องราวทั้งหมดบันทึกอยู่ในจดหมายเหตุรัชกาลกษัตริย์เซอร์ซีส