አሞጽ 8 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

አሞጽ 8:1-14

የጐመራ ፍሬ የሞላበት ቅርጫት

1ጌታ እግዚአብሔር ይህን አሳየኝ፤ እነሆ፤ የጐመራ ፍሬ የሞላበት ቅርጫት ነበረ። 2እርሱም፣ “አሞጽ ሆይ፤ ምን ታያለህ?” አለኝ። እኔም፣ “የጐመራ ፍሬ የሞላበት ቅርጫት አያለሁ” አልሁ። ከዚያም በኋላ እግዚአብሔር እንዲህ አለኝ፤ “በሕዝቤ በእስራኤል ላይ ፍጻሜ መጥቷል፤ ከእንግዲህም አልምራቸውም።”

3ጌታ እግዚአብሔር፣ “በዚያ ቀን የቤተ መቅደሱ ዝማሬ ወደ ዋይታ8፥3 የቤተ መቅደሱ ዘማርያን ዋይታ ያሰማሉ የሚሉ አሉ። ይለወጣል፤ እጅግ ብዙ የሆነ የሰው ሬሳ ወድቆ ይገኛል፤ ዝምታም ይሰፍናል” ይላል።

4እናንት ችግረኞችን የምትረግጡ፣

የምድሪቱንም ድኾች የምታጠፉ ይህን ስሙ፤

5እንዲህም ትላላችሁ፤

“መስፈሪያውን በማሳነስ፣

ዋጋውን ከፍ በማድረግ፣

በሐሰተኛ ሚዛን በማጭበርበር፣

እህል እንድንሸጥ፣

የወር መባቻ መቼ ያበቃል?

ስንዴም ለገበያ እንድናቀርብ፣

ሰንበት መቼ ያልፋል?”

6ድኻውን በብር፣

ችግረኛውንም በጥንድ ጫማ እንገዛለን፤

ግርዱን እንኳ በስንዴ ዋጋ እንሸጣለን።

7እግዚአብሔር በያዕቆብ ክብር እንዲህ ሲል ምሏል፤ “እነርሱ ያደረጉትን ሁሉ ከቶ አልረሳም።

8“በዚህ ነገር ምድር አትናወጥምን?

በውስጧ የሚኖሩትስ ሁሉ አያለቅሱምን?

የምድር ሁለመና እንደ አባይ ወንዝ ይነሣል፤

እንደ ግብፅ ወንዝም ወደ ላይ ይፈናጠራል፤

ተመልሶም ይወርዳል።”

9ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በዚያ ቀን፣ ፀሓይ በቀትር እንድትጠልቅ አደርጋለሁ፤

ምድርንም ደማቅ ብርሃን ሳለ በቀን አጨልማታለሁ።

10ዓመት በዓላችሁን ወደ ልቅሶ፣

ዝማሬአችሁንም ሁሉ ወደ ዋይታ እለውጣለሁ፤

ሁላችሁም ማቅ እንድትለብሱ፣

ጠጕራችሁንም እንድትላጩ አደርጋለሁ፤

ያን ጊዜ ለአንድያ ልጅ ሞት እንደሚለቀስበት፣

ፍጻሜውንም እንደ መራራ ቀን አደርገዋለሁ።”

11ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በምድር ላይ ራብን የምሰድድበት ዘመን ይመጣል፤

ይኸውም የእግዚአብሔርን ቃል የመስማት ራብ እንጂ፣

እንጀራን የመራብ ወይም ውሃን የመጠማት አይደለም።

12ሰዎች እግዚአብሔርን ለመሻት፣

ከባሕር ወደ ባሕር፣

ከሰሜን ወደ ምሥራቅ ይንከራተታሉ፤

ነገር ግን አያገኙትም።

13“በዚያ ቀን፣

“ቈነጃጅት ሴቶችና ብርቱዎች ጕልማሶች፣

ከውሃ ጥም የተነሣ ይዝላሉ።

14በሰማርያ ኀፍረት8፥14 ወይም በአሼማ ወይም በጣኦት አማልክት የሚምሉ፣

ወይም፣ ‘ዳን ሆይ፤ ሕያው አምላክህን’ የሚሉ፣

ወይም ‘ሕያው የቤርሳቤህ አምላክን8፥14 ወይም መንገዱን’ ብለው የሚምሉ፣

ዳግመኛ ላይነሡ፣ ለዘላለም ይወድቃሉ።”

Ketab El Hayat

عاموس 8:1-14

سلة الثمار الناضجة

1ثُمَّ أَرَانِي السَّيِّدُ الرَّبُّ فِي رُؤْيَا سَلَّةً لِقِطَافِ الثِّمَارِ. 2وَسَأَلَنِي: «مَاذَا تَرَى يَا عَامُوسُ؟» فَأَجَبْتُ: «سَلَّةً مَلِيئَةً بِثِمَارِ الصَّيْفِ النَّاضِجَةِ». فَقَالَ لِي الرَّبُّ: «لَقَدْ دَنَتْ نِهَايَةُ شَعْبِي إِسْرَائِيلَ وَلَنْ أَعْفُوَ عَنْهُمْ بَعْدُ. 3فَتَتَحَوَّلُ أَغَانِي قُصُورِهِمْ إِلَى عَوِيلٍ فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ، وَتَكْثُرُ الْجُثَثُ وَيَطْرَحُونَهَا فِي كُلِّ مَكَانٍ بِصَمْتٍ».

4اسْتَمِعُوا هَذَا أَيُّهَا الدَّائِسُونَ عَلَى الْبَائِسِينَ، يَا مَنْ حَاوَلْتُمْ أَنْ تَقْضُوا عَلَى فُقَرَاءِ الأَرْضِ، 5قَائِلِينَ: «مَتَى يَنْقَضِي أَوَّلُ الشَّهْرِ حَتَّى نَبِيعَ الْقَمْحَ؟ مَتَى يَمْضِي السَّبْتُ لِنَعْرِضَ الْقَمْحَ فِي السُّوقِ، فَنَعْمَدَ إِلَى تَصْغِيرِ حَجْمِ مِكْيَالِ الإِيفَةِ وَنَرْفَعَ الأَسْعَارَ، وَنَسْتَعْمِلَ مِيزَاناً مَغْشُوشاً. 6لِنَشْتَرِيَ الْمِسْكِينَ بِقِطْعَةٍ مِنَ الْفِضَّةِ، وَالْبَائِسَ بِنَعْلَيْنِ، وَنَبِيعَ نُفَايَةَ الْقَمْحِ؟»

7قَدْ أَقْسَمَ الرَّبُّ بِعِزَّةِ يَعْقُوبَ قَائِلاً: «لَنْ أَنْسَى شَيْئاً مِنْ مَسَاوِئِهِمْ. 8ألا تَرْتَعِبُ الأَرْضُ مِنْ جَرَّاءِ ذَلِكَ، فَيَنُوحَ كُلُّ سَاكِنٍ فِيهَا، فَتَطْمُوَ كَنَهْرٍ، وَتَرْتَفِعَ وَتَنْخَفِضَ كَنِيلِ مِصْرَ؟ 9وَيَقُولُ الرَّبُّ: فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ أَجْعَلُ الشَّمْسَ تَغْرُبُ عِنْدَ الظَّهِيرَةِ، وَأَغْمُرُ الأَرْضَ بِالظُّلْمَةِ فِي رَابِعَةِ النَّهَارِ. 10أُحَوِّلُ أَعْيَادَكُمْ إِلَى مَآتِمَ، وَأَغَانِيَكُمْ إِلَى مَرَاثٍ، وَأُلْبِسُكُمُ الْمُسُوحَ عَلَى أَحْقَائِكُمْ، وَأُفْشِي الصَّلَعَ فِي كُلِّ رَأْسٍ، فَتُصْبِحُ أَعْيَادُكُمْ كَمَنَاحَةٍ عَلَى وَحِيدٍ، وَنِهَايَتُهَا كَيَوْمٍ مُفْعَمٍ بِالْمَرَارَةِ.

11سَتَأْتِي أَيَّامٌ أَجْعَلُ فِيهَا الْمَجَاعَةَ تَنْتَشِرُ فِي الأَرْضِ، لَا مَجَاعَةً إِلَى الْخُبْزِ، وَلا ظَمَأً إِلَى الْمَاءِ إِنَّمَا لِسَمَاعِ كَلامِ الرَّبِّ، يَقُولُ السَّيِّدُ الرَّبُّ. 12فَيَهِيمُونَ مِنْ بَحْرٍ إِلَى بَحْرٍ، وَمِنَ الشِّمَالِ إِلَى الشَّرْقِ. يَذْهَبُونَ وَيَجِيئُونَ بَحْثاً عَنْ كَلِمَةِ الرَّبِّ وَلا يَحْظَوْنَ بِها. 13فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ يُغْشَى عَلَى العَذَارَى الْجَمِيلاتِ وَالْفِتْيَانِ مِنْ فَرْطِ الظَّمَإِ. 14أَمَّا الَّذِينَ يُقْسِمُونَ بِأَوْثَانِ السَّامِرَةِ قَائِلِينَ: حَيٌّ إِلَهُكَ يَا دَانُ، وَحَيٌّ مَعْبُودُ بِئْرِ سَبْعٍ. هَؤُلاءِ يَسْقُطُونَ وَلا يَنْهَضُونَ أَبَداً ثَانِيَةً».