አሞጽ 7 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

አሞጽ 7:1-17

አንበጣ፣ እሳትና ቱንቢ

1ጌታ እግዚአብሔር ይህን አሳየኝ፤ የንጉሡ የመኸር እህል ከተሰበሰበ በኋላ ገቦው መብቀል በጀመረ ጊዜ፣ እርሱ የአንበጣ መንጋ እንዲፈለፈል አደረገ። 2አንበጦች የምድሩን ሣር ግጠው ከጨረሱት በኋላ፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ ይቅር እንድትል እለምንሃለሁ፤ ያዕቆብ ይህን እንዴት ሊቋቋመው ይችላል? ታናሽ ነው እኮ!” አልሁ።

3እግዚአብሔርም ስለዚህ ነገር ተጸጸተ፤ እግዚአብሔርም ይህ አይፈጸምም አለ።

4ጌታ እግዚአብሔር ይህንም አሳየኝ፤ ጌታ እግዚአብሔር በእሳት ሊፈርድ ተዘጋጀ፤ እሳቱም ታላቁን ጥልቅ አደረቀ፤ ምድሪቱንም በላ። 5ከዚያም በኋላ፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንድትተወው እለምንሃለሁ፤ ያዕቆብ ይህን እንዴት ሊቋቋመው ይችላል? ታናሽ ነው እኮ!” አልሁ።

6እግዚአብሔር ስለዚህ ነገር ተጸጸተ፤ ጌታ እግዚአብሔር፣ “ይህም ደግሞ አይፈጸምም” አለ።

7ይህንም ደግሞ አሳየኝ፤ ጌታ በእጁ ቱንቢ ይዞ በቱንቢ በተሠራ ቅጥር አጠገብ ቆሞ ነበር። 8እግዚአብሔር፣ “አሞጽ፣ የምታየው ምንድን ነው?” አለኝ።

እኔም፣ “ቱንቢ” አልሁ።

ጌታም እንዲህ አለ፤ “እነሆ፤ በሕዝቤ በእስራኤል መካከል ቱንቢ እዘረጋለሁ፤ ከእንግዲህም ወዲያ አልምራቸውም።

9“የይስሐቅ ማምለኪያ ኰረብታዎች ባድማ ይሆናሉ፤

የእስራኤል መቅደሶች ይፈርሳሉ፤

በኢዮርብዓምም ቤት ላይ በሰይፌ እነሣለሁ።”

አሞጽና አሜስያስ

10ከዚህ በኋላ የቤቴል ካህን አሜስያስ ወደ እስራኤል ንጉሥ ወደ ኢዮርብዓም እንዲህ ሲል መልእክት ላከ፤ “አሞጽ በእስራኤል ቤት መካከል በአንተ ላይ እያሤረ ነው፤ ምድሪቱም ቃሉን ሁሉ ልትሸከም አትችልም፤ 11አሞጽ እንዲህ ሲል ተናግሮ ነበርና፤

“ ‘ኢዮርብዓም በሰይፍ ይሞታል፤

እስራኤልም በርግጥ ከትውልድ አገሩ

ተማርኮ ይሄዳል።’ ”

12አሜስያስም፣ አሞጽን እንዲህ አለው፤ “አንተ ባለ ራእይ ከዚህ ሂድ! ከይሁዳ ምድር ሽሽ፤ እዚያም እንጀራህን ብላ፤ በዚያም ትንቢት ተናገር። 13ከእንግዲህ ወዲያ ግን በቤቴል ትንቢት አትናገር፤ የንጉሡ መቅደስ፣ የመንግሥቱም መኖሪያ ነውና።”

14አሞጽም ለአሜስያስ እንዲህ ሲል መለሰ፤ “እኔ እረኛና የባሉጥ ፍሬ ለቃሚ ነኝ እንጂ ነቢይ ወይም የነቢይ ልጅ አይደለሁም፤ 15እግዚአብሔር ግን የበግ መንጋ ከምጠብቅበት ቦታ ወስዶ፣ ‘ሂድና ለሕዝቤ ለእስራኤል ትንቢት ተናገር’ አለኝ፤ 16እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ።

“አንተ፣ ‘በእስራኤል ላይ ትንቢት አትናገር፤

በይስሐቅም ቤት ላይ አትስበክ’

ትላለህ።

17“ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ሚስትህ በከተማዪቱ ውስጥ ጋለሞታ ትሆናለች፤

ወንዶችና ሴቶች ልጆችህም በሰይፍ ይወድቃሉ፤

ምድርህም እየተለካ ይከፋፈላል፤

አንተ ራስህ በረከሰ7፥17 ዕብራይስጡ ርኩስ ይለዋል። ምድር ትሞታለህ፤

እስራኤልም ከትውልድ አገሩ፣

ተማርኮ ይሄዳል።’ ”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

阿摩司书 7:1-17

各种灾祸的异象

1以下是主耶和华让我看见的异象:看啊,祂造了一大群蝗虫。那时,王室的作物已经收割,第二季作物刚开始发苗。 2蝗虫吃尽地上的青苗时,我说:“主耶和华啊,求你赦免!雅各那么弱小,他怎么受得了呢?” 3于是,耶和华心生怜悯,说:“我不降这灾了。”

4以下是主耶和华让我看见的异象:看啊,主耶和华降下审判的大火。大火烧干了深海,正在吞噬土地。 5那时,我说:“主耶和华啊,求你停止吧!雅各那么弱小,他怎么受得了呢?” 6于是,耶和华心生怜悯,说:“我也不降这灾了。”

7以下是祂让我看见的异象:看啊,主站在一道按照准绳建造的墙边,手里拿着准绳。 8耶和华对我说:“阿摩司,你看见什么?”我答道:“一条准绳。”主说:“我要在我的以色列子民中吊起准绳,量度他们,我不会再饶恕他们。 9以撒子孙的丘坛必遭毁坏,以色列的庙宇必成废墟,我要用刀攻击耶罗波安王朝。”

阿摩司被逐

10伯特利的祭司亚玛谢派人告诉以色列耶罗波安:“阿摩司以色列家图谋背叛你,我们国家无法容忍他的言论。 11因为阿摩司这样说,‘耶罗波安将丧身刀下,以色列人必被掳去,远离家乡。’”

12亚玛谢对我说:“先见啊,走吧!逃回犹大去吧!你要在那里挣吃的,在那里说预言。 13不可再在伯特利说预言,这里是王的圣所,是国庙。”

14我答道:“我本不是先知,也不是先知的门徒。我只是一个牧人,也替人看护桑树。 15但耶和华不再让我看守羊群,祂对我说,‘去!向我的以色列子民说预言。’ 16亚玛谢啊,你说,‘不要说攻击以色列的预言,不要传讲攻击以撒子孙的信息。’现在你要听耶和华对你说的话。 17耶和华说,‘你的妻子必在这城里沦为妓女,你的儿女必丧身刀下,你的田地必被人丈量、瓜分,你自己必死在异乡7:17 异乡”希伯来文是“不洁之地”,指不信上帝的国家。以色列人必被掳去,远离家乡。’”