አሞጽ 6 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

አሞጽ 6:1-14

ተዘልላ ላለችው እስራኤል የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

1በጽዮን ተዘልላችሁ የምትቀመጡ፣

በሰማርያ ተራራ ያለ ሥጋት የምትኖሩ፣

የእስራኤልም ሕዝብ ለርዳታ ወደ እናንተ የሚመጡባችሁ፣

እናንት የአሕዛብ አለቆች ሆይ፤ ወዮላችሁ!

2ወደ ካልኔ ሂዱ፤ እርሱንም ተመልከቱ፤

ከዚያም ወደ ታላቂቱ ሐማት ሂዱ፤

ወደ ፍልስጥኤም ከተማ ወደ ጌትም ውረዱ፤

እነዚህ ከሁለቱ መንግሥታታችሁ ይሻላሉን?

የምድራቸውስ ስፋት ከእናንተ ይበልጣልን?

3ክፉውን ቀን ለምታርቁ፣

የግፍንም ወንበር ለምታቀርቡ ወዮላችሁ!

4በዝኆን ጥርስ ባጌጠ ዐልጋ ላይ ለምትተኙ፤

በድንክ ዐልጋችሁ ላይ ለምትዝናኑ፣

ከበጎች መንጋ ጠቦትን፣

ከጋጣም ጥጃን ለምትበሉ፤

5ባልተቃኘ በገና ለምትዘፍኑ፣

በሙዚቃ መሣሪያ ለመጫወት ለምትሹ፣

6በፋጋ የወይን ጠጅ ለምትጠጡ፣

ምርጥ ሽቱም ለምትቀቡ፣

ስለ ዮሴፍ መከራ ግን ለማታዝኑ ወዮላችሁ!

7ስለዚህ እናንተ በመጀመሪያ በምርኮ ከሚወሰዱት መካከል ናችሁ፤

መፈንጠዛችሁና መዝናናታችሁም ያበቃል።

እግዚአብሔር የእስራኤልን ትዕቢት ይጸየፋል

8ጌታ እግዚአብሔር

“የያዕቆብን ትዕቢት ተጸይፌአለሁ፤

ምሽጎቹንም ጠልቻለሁ፤

ከተማዪቱንና በውስጧ ያለውን ሁሉ፣

አሳልፌ እሰጣለሁ”

ሲል በራሱ ምሏል፤ ይላል የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር

9በአንድ ቤት ውስጥ ዐሥር ሰዎች ቢቀሩ እነርሱም ይሞታሉ። 10በድኖቹንም ከቤት አውጥቶ ማቃጠል ያለበት አንድ ዘመድ መጥቶ ተደብቆ ያለውን ሰው፣ “ከአንተ ጋር የቀረ ሌላ ሰው አለን?” ሲለው፣ እርሱም “የለም” ይለዋል፤ ከዚያም በኋላ፣ “ዝም በል፤ የእግዚአብሔርን ስም መጥራት አይገባንም” ይለዋል።

11እነሆ፤ እግዚአብሔር ትእዛዝ ሰጥቷልና፤

ታላላቅ ቤቶችን ያወድማቸዋል፤

ትንንሾቹንም ያደቅቃቸዋል።

12ፈረሶች በጭንጫ ላይ ይሮጣሉን?

ሰውስ እዚያ ላይ በበሬ ያርሳልን?

እናንተ ግን ፍትሕን ወደ መርዝነት፣

የጽድቅንም ፍሬ ወደ መራራነት ለወጣችሁ።

13እናንተ ሎዶባርን6፥13 ትርጕሙ ምንም ማለት ነው። በማሸነፋችሁ ደስ ያላችሁ፣

“ቃርናይምን6፥13 ቃርናይም ትርጕሙ ቀንዶች ማለት ነው፤ ቀንድ የጥንካሬ ምልክት ነው። በራሳችን ብርታት ይዘናል” የምትሉ።

14ሁሉን የሚገዛ አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፣

“የእስራኤል ሕዝብ ሆይ፤ እነሆ፤ እኔ ከሐማት መግቢያ6፥14 ወይም ከመግቢያው ጀምሮ እስከ ዓረባ ሸለቆ ድረስ፣

የሚያስጨንቃችሁን ሕዝብ፣ በእናንተ

ላይ አስነሣለሁ።”

Japanese Contemporary Bible

アモス書 6:1-14

6

安逸をむさぼる者への警告

1イスラエルの民の間で有名なエルサレムとサマリヤで、

ぜいたくにのんびり暮らしている者たちは、災いだ。

2カルネへ行って、そこで起こったことを見なさい。

それから大ハマテへ行き、

ペリシテ人の地にあるガテへも下って行きなさい。

かつてそこは、あなたがたより栄えていました。

しかし、今はどうなっているかを見なさい。

3あなたがたは、

迫っている罰のことを考えようとしません。

しかし、その行いによって、

さばきの日は近くなっているのです。

4あなたがたはぜいを尽くした

象牙のベッドに横になって、

柔らかい子羊の肉や最上の子牛の肉を食べています。

5堅琴に合わせて、むなしい歌を歌い、

ダビデ王のような

偉大な音楽家のつもりになっています。

6浴びるほどぶどう酒を飲み、

香油を体に塗っても、

助けを求める兄弟たちのことは全く気にしません。

7そのため、あなたがたが真っ先に

奴隷となって引いて行かれます。

酒盛りは突然終わるのです。

イスラエルの思い上がりに対する主の嫌悪

8全能の主は、

ご自分の名にかけて誓います。

「わたしはイスラエルの思い上がりと

偽りの栄光をきらい、彼らの美しい宮殿を憎む。

この町とそこにあるすべての物を敵の手に渡す。」

9一つの氏族で十人が残ったとしても、

彼らもまた死にます。

10親戚の者が葬ることになり、

死体を家から運び出す時、

家の中に一人だけ生き残っている者に

「ほかに残っている者がいるか」と聞くと、

「いない」という答えが返ってきます。

すると、「しーっ、声を出すな。主の名を口にするな。

おまえの言うことを聞いているかもしれないから」

と言うのです。

11主がこのように命じたからです。

大きな氏族も小さな氏族も、木っ端みじんになれと。

12馬は岩の上を走れるでしょうか。

牛は海を耕せるでしょうか。

これは聞くだけ愚かなことだが、

あなたがたのやっていることより

愚かなことはありません。

正義をあざけり、良いこと、正しいことを腐敗させ、

堕落させているではありませんか。

13また、無に等しい者なのに、

愚かにも、偉い者であるかのように喜びます。

ちっぽけな力を、たいそう自慢しています。

14全能の主は言います。

「イスラエルよ。

わたしは一つの民を起こして、

あなたがたを攻めさせる。

北の国境から南の端まで、

レボ・ハマテからアラバの川筋までの全域で、

彼らはあなたがたを虐げる。」