አሞጽ 4 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

አሞጽ 4:1-13

እስራኤል ወደ እግዚአብሔር አልተመለሰም

1እናንተ በሰማርያ ተራራ የምትኖሩ የባሳን ላሞች፤

ድኾችን የምትጨቍኑና ችግረኞችን የምታስጨንቁ፣

ባሎቻችሁንም፣ “መጠጥ አቅርቡልን”

የምትሉ ሴቶች ይህን ቃል ስሙ፤

2ጌታ እግዚአብሔር በቅድስናው እንዲህ ሲል ምሏል፤

“እነሆ፤ በመንጠቆ ተይዛችሁ የምትወሰዱበት

ትሩፋናችሁ እንኳ፣ በዓሣ መንጠቆ

የሚወሰድበት ጊዜ ይመጣል።

3እያንዳንዳችሁ በቅጥሩ በተነደለው መሽሎኪያ

ወደ ሬማንም4፥3 በተለያዩ የዕብራይስጥ ቃላት የተከፈለው የመጀመሪያው የዕብራይስጥ ቅጅ (የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ይመ) የጭቈና ተራራ ሆይ ራቅ ይላል። ትጣላላችሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

4“ወደ ቤቴል ሂዱና ኀጢአትን ሥሩ፤

ወደ ጌልገላም ሂዱና ኀጢአትን አብዙ፤

በየማለዳው መሥዋዕቶቻችሁን፣

በየሦስቱ4፥4 በየሦስቱ ቀናት ዐሥራታችሁን የሚሉ አሉ። ዓመት ዐሥራታችሁን አቅርቡ።

5እርሾ ያለበትን እንጀራ የምስጋና

መሥዋዕት አድርጋችሁ አቅርቡ፤

በፈቃዳችሁም በምታቀርቡት ቍርባን ተመኩ፤

እናንት እስራኤላውያን በእነርሱም ተኵራሩ፤ ማድረግ የምትወድዱት ይህን ነውና፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

6“በየከተማው ሆዳችሁን4፥6 ዕብራይስጡ ጥርሳችሁን አጠራለሁ ይላል። ባዶ አደረግሁት፤

በየመንደሩም የምትበሉትን

አሳጣኋችሁ፤ እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም”

ይላል እግዚአብሔር

7“መከር ሊደርስ ሦስት ወር ሲቀረውም፣

ዝናብ ከለከልኋችሁ፤

በአንዱ ከተማ ላይ አዘነብሁ፤

በሌላው ላይ ግን እንዳይዘንብ

አደረግሁ፤ አንዱ ዕርሻ ሲዘንብለት፣

ሌላው ዝናብ ዐጥቶ ደረቀ።

8ሰዎች ውሃ ፍለጋ ከከተማ ወደ ከተማ ባዘኑ፣

ይሁን እንጂ ጠጥተው አልረኩም፤

እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም፤”

ይላል እግዚአብሔር

9“የአትክልትና የወይን ቦታዎቻችሁን ብዙ ጊዜ መታሁ፤

በዋግና በአረማሞም አጠፋኋቸው፤

አንበጦችም የበለስና የወይራ ዛፎቻችሁን በሉ፤

እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም፤”

ይላል እግዚአብሔር

10“በግብፅ ላይ እንዳደረግሁት፣

መቅሠፍትን ላክሁባችሁ፤

ከተማረኩት ፈረሶቻችሁ ጋር፣

ጕልማሶቻችሁን በሰይፍ ገደልሁ፤

የሰፈራችሁ ግማት አፍንጫችሁ እንዲገባ አደረግሁ፤

እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም”

ይላል እግዚአብሔር

11“ሰዶምንና ገሞራን እንደ ገለበጥኋቸው፣

አንዳንዶቻችሁን ገለበጥሁ፤

ከእሳት እንደ ተነጠቀ ትንታግ ሆናችሁ፤

እናንተ ግን ወደ እኔ4፥11 ዕብራይስጡ አምላክ ይላል። አልተመለሳችሁም፤”

ይላል እግዚአብሔር

12“ስለዚህ እስራኤል ሆይ፤ እንደዚህ አደርግብሃለሁ፤

እንደዚህም ስለማደርግብህ፣ እስራኤል ሆይ፤

አምላክህን ለመገናኘት ተዘጋጅ።”

13ተራሮችን የሚሠራ፣

ነፋስን የሚፈጥር፣

ሐሳቡንም ለሰው የሚገልጥ፣

ንጋትን ጨለማ የሚያደርግ፣

የምድርንም ከፍታዎች የሚረግጥ፣

ስሙ የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ነው።

Ketab El Hayat

عاموس 4:1-13

إسرائيل لم ترجع لله

1اسْمَعِي هَذِهِ الْكَلِمَةِ يَا نِسَاءَ بَاشَانَ، اللَّوَاتِي يُقِمْنَ فِي جَبَلِ السَّامِرَةِ، مِمَّنْ يَظْلِمْنَ الْمِسْكِينَ وَيَسْحَقْنَ الْفُقَرَاءَ وَاللَّوَاتِي يَقُلْنَ لأَزْوَاجِهِنَّ: هَاتُوا مُسْكِراً لِنَشْرَبَ. 2قَدْ أَقْسَمَ السَّيِّدُ الرَّبُّ بِقَدَاسَتِهِ قَائِلاً: هَا أَيَّامٌ تُقْبِلُ عَلَيْكُنَّ، يَجُرُّكُنَّ فِيهَا الْعَدُوُّ بِالْكَلالِيبِ وَذُرِّيَّتَكُنَّ بِشُصُوصِ السَّمَكِ. 3وَتَخْرُجُ كُلُّ وَاحِدَةٍ مِنْكُنَّ مِنْ شَقٍّ، زَاحِفَةً عَلَى وَجْهِهَا، وَتُطْرَدْنَ إِلَى هَرْمُونَ، يَقُولُ الرَّبُّ.

4تَعَالَوْا إِلَى بَيْتِ إِيلَ وَارْتَكِبُوا الْمَعَاصِي، وَأَقْبِلُوا إِلَى الْجِلْجَالِ وَكَثِّرُوا ذُنُوبَكُمْ. قَرِّبُوا ذَبَائِحَكُمْ فِي كُلِّ صَبَاحٍ، وَعُشُورَكُمْ كُلَّ ثَلاثَةِ أَيَّامٍ. 5قَدِّمُوا مِنَ الْخَمِيرِ قُرْبَانَ شُكْرٍ، وَأَعْلِنُوا مُتَبَاهِينَ عَنْ تَقْدِمَاتِكُمُ التَّطَوُّعِيَّةِ، وَتَفَاخَرُوا بِها، لأَنَّ هَذَا مَا تُحِبُّونَ أَنْ تَفْعَلُوهُ يَا شَعْبَ إِسْرَائِيلَ، يَقُولُ السَّيِّدُ الرَّبُّ.

6قَدْ جَعَلْتُ الْجُوعَ يَعُمُّ مُدُنَكُمْ، فَلَمْ تَتَّسِخْ أَسْنَانُكُمْ بِالطَّعَامِ! وَأَفْقَرْتُكُمْ إِلَى الْخُبْزِ فِي كُلِّ أَمَاكِنِ سُكْنَاكُمْ، وَلَكِنَّكُمْ لَمْ تَرْجِعُوا إِلَيَّ تَائِبِينَ، يَقُولُ الرَّبُّ. 7مَنَعْتُ عَنْكُمُ الْمَطَرَ وَلَمْ يَكُنْ قَدْ بَقِيَ لِلْحَصَادِ سِوَى ثَلاثَةِ أَشْهُرٍ، وَأَمْطَرْتُ عَلَى مَدِينَةٍ دُونَ مَدِينَةٍ، وَعَلَى حَقْلٍ دُونَ الآخَرِ، فَجَفَّ الْحَقْلُ الَّذِي لَمْ أُمْطِرْ عَلَيْهِ. 8فَأَقْبَلَتْ مَدِينَتَانِ أَوْ ثَلاثٌ عَلَى مَدِينَةٍ وَاحِدَةٍ لِتَشْرَبَ مَاءً، وَلَكِنَّهَا لَمْ تَرْتَوِ، وَمَعَ ذَلِكَ لَمْ تَرْجِعُوا إِلَيَّ تَائِبِينَ، يَقُولُ الرَّبُّ.

9أَرْسَلْتُ الرِّيَاحَ اللّافِحَةَ وَالْيَرَقَانَ لِتُجَفِّفَ مَحَاصِيلَكُمْ، وَالْتَهَمَ الْجَرَادُ حَدَائِقَكُمْ وَكُرُومَكُمْ وَأَشْجَارَ تِينِكُمْ وَزَيْتُونِكُمْ. وَمَا رَجَعْتُمْ إِلَيَّ! 10أَصَبْتُكُمْ بِالأَوْبِئَةِ الَّتِي أُصِيبَتْ بِها مِصْرُ، وَقَضَيْتُ عَلَى شَبَابِكُمْ بِالسَّيْفِ وَسَبَيْتُ خُيُولَكُمْ، وَجَعَلْتُ نَتْنَ مُعَسْكَرِكُمْ يَزْكُمُ أُنُوفَكُمْ. وَلَكِنَّكُمْ لَمْ تَرْجِعُوا إِلَيَّ تَائِبِينَ يَقُولُ الرَّبُّ. 11دَمَّرْتُ بَعْضَ مُدُنِكُمْ كَمَا دَمَّرَ اللهُ سَدُومَ وَعَمُورَةَ، فَكَانَ مَنْ نَجَا مِنْكُمْ كَشُعْلَةٍ مُنْتَشَلَةٍ مِنَ النَّارِ. وَلَكِنَّكُمْ لَمْ تَرْجِعُوا إِلَيَّ تَائِبِينَ.

12لِذَلِكَ، هَذَا مَا أُجْرِيهِ عَلَيْكَ يَا إِسْرَائِيلُ. فَمِنْ أَجْلِ مَا أَصْنَعُهُ بِكَ تَأَهَّبْ لِلِقَاءِ إِلَهِكَ. 13فَانْظُرْ إِنَّهُ هُوَ صَانِعُ الْجِبَالِ وَخَالِقُ الرِّيَاحِ، الَّذِي أَعْلَنَ فِكْرَهُ لِلْبَشَرِ، وَأَحَالَ النَّهَارَ إِلَى لَيْلٍ، وَمَشَى فَوْقَ مَشَارِفِ الأَرْضِ، الرَّبُّ الإِلَهُ الْقَدِيرُ اسْمُهُ.