አሞጽ 2 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

አሞጽ 2:1-16

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የሞዓብ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

የኤዶምን ንጉሥ ዐጥንት፣

ዐመድ እስኪሆን ድረስ አቃጥሏልና፤

2የቂርዮትን ምሽጎች2፥2 ወይም ከተሞቿ እንዲበላ፣

በሞዓብ ላይ እሳት እሰድዳለሁ፤

ሞዓብ በጦርነት ጩኸትና በመለከት ድምፅ መሐል፣

በታላቅ ሁካታ ውስጥ ይሞታል።

3ገዧን እደመስሳለሁ፣

አለቆቿንም ሁሉ ከንጉሧ ጋር እገድላለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

4እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የይሁዳ ኀጢአት፣

ይልቁን ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

የእግዚአብሔርን ሕግ ንቀዋል፤

ትእዛዙንም አልጠበቁምና፤

አባቶቻቸው በተከተሏቸው2፥4 ወይም በውሸት አማልክት፣

በሐሰት2፥4 ወይም ውሸት አማልክት በመመራት ስተዋልና።

5የኢየሩሳሌምን ምሽጎች እንዲበላ፣

በይሁዳ ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

በእስራኤል ላይ የተሰጠ ፍርድ

6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የእስራኤል ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ጻድቁን ስለ ጥሬ ብር፣

ችግረኛውንም ስለ ጥንድ ጫማ ይሸጡታልና።

7የድኾችን ራስ፣

በምድር ትቢያ ላይ ይረግጣሉ፤

ፍትሕንም ከጭቍኖች ይነጥቃሉ፤

አባትና ልጅ ከአንዲት ሴት ጋር ይተኛሉ፤

እንዲህም እያደረጉ ቅዱስ ስሜን ያረክሳሉ።

8በመያዣነት በተወሰደው ልብስ ላይ፣

በየመሠዊያው ሥር ይተኛሉ፤

በአምላካቸው ቤት፣

በመቀጫነት የተወሰደውን የወይን ጠጅ ይጠጣሉ።

9“ቁመቱ እንደ ዝግባ፣

ጥንካሬውም እንደ ባሉጥ ዛፍ የነበረ ቢሆንም፣

አሞራዊውን ከፊታቸው አጠፋሁት፣

ከላይ ፍሬውን፣

ከታችም ሥሩን አጠፋሁ።

10የአሞራውያንን ምድር ልሰጣችሁ፣

ከግብፅ አወጣኋችሁ፤

አርባ ዓመትም በምድረ በዳ መራኋችሁ።

11“ደግሞም ነቢያትን ከወንዶች ልጆቻችሁ መካከል፣

ናዝራውያንንም ከጕልማሶቻችሁ መካከል አስነሣሁ፤

የእስራኤል ሕዝብ ሆይ፤ ይህ እውነት አይደለምን?”

ይላል እግዚአብሔር

12“እናንተ ግን ናዝራውያኑን የወይን ጠጅ አጠጣችኋቸው፤

ነቢያቱንም ትንቢት እንዳይናገሩ አዘዛችኋቸው።

13“እነሆ፤ በእህል የተሞላ ጋሪ እንደሚያደቅቅ፣

እኔም አደቅቃችኋለሁ።

14ፈጣኑ አያመልጥም፤

ብርቱውንም ብርታቱ አይረዳውም፤

ኀያሉም ነፍሱን አያድንም።

15ቀስተኛው በቦታው ጸንቶ አይቆምም፤

ፈጣኑም ተዋጊ ሮጦ አያመልጥም፤

ፈረሰኛውም ነፍሱን አያድንም።

16ጐበዞቹ ተዋጊዎች እንኳ፣

በዚያ ቀን ዕራቁታቸውን ይሸሻሉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

New International Version

Amos 2:1-16

1This is what the Lord says:

“For three sins of Moab,

even for four, I will not relent.

Because he burned to ashes

the bones of Edom’s king,

2I will send fire on Moab

that will consume the fortresses of Kerioth.2:2 Or of her cities

Moab will go down in great tumult

amid war cries and the blast of the trumpet.

3I will destroy her ruler

and kill all her officials with him,”

says the Lord.

4This is what the Lord says:

“For three sins of Judah,

even for four, I will not relent.

Because they have rejected the law of the Lord

and have not kept his decrees,

because they have been led astray by false gods,2:4 Or by lies

the gods2:4 Or lies their ancestors followed,

5I will send fire on Judah

that will consume the fortresses of Jerusalem.”

Judgment on Israel

6This is what the Lord says:

“For three sins of Israel,

even for four, I will not relent.

They sell the innocent for silver,

and the needy for a pair of sandals.

7They trample on the heads of the poor

as on the dust of the ground

and deny justice to the oppressed.

Father and son use the same girl

and so profane my holy name.

8They lie down beside every altar

on garments taken in pledge.

In the house of their god

they drink wine taken as fines.

9“Yet I destroyed the Amorites before them,

though they were tall as the cedars

and strong as the oaks.

I destroyed their fruit above

and their roots below.

10I brought you up out of Egypt

and led you forty years in the wilderness

to give you the land of the Amorites.

11“I also raised up prophets from among your children

and Nazirites from among your youths.

Is this not true, people of Israel?”

declares the Lord.

12“But you made the Nazirites drink wine

and commanded the prophets not to prophesy.

13“Now then, I will crush you

as a cart crushes when loaded with grain.

14The swift will not escape,

the strong will not muster their strength,

and the warrior will not save his life.

15The archer will not stand his ground,

the fleet-footed soldier will not get away,

and the horseman will not save his life.

16Even the bravest warriors

will flee naked on that day,”

declares the Lord.