አሞጽ 1 – NASV & NVI-PT

New Amharic Standard Version

አሞጽ 1:1-15

1በቴቁሔ ከነበሩት እረኞች መካከል አንዱ የሆነው አሞጽ፣ ዖዝያን የይሁዳ ንጉሥ በነበረ ጊዜ እንዲሁም የዮአስ1፥1 ዕብራይስጡ ዮአስ ያለው የኢዮአስ ተለዋጭ ስም ሳይሆን አይቀርም። ልጅ ኢዮርብዓም የእስራኤል ንጉሥ በነበረ ጊዜ፣ ይኸውም የምድር መናወጥ ከመሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ስለ እስራኤል ያየውና የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2እርሱም እንዲህ አለ፤

እግዚአብሔር ከጽዮን ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማል፤

ከኢየሩሳሌምም ያንጐደጕዳል፤

የእረኞች ማሰማሪያዎች ደርቀዋል1፥2 ወይም የእረኞች ሐዘን

የቀርሜሎስም ዐናት ጠውልጓል።”

በእስራኤል ጎረቤቶች ላይ የተሰጠ ፍርድ

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

የብረት ጥርስ ባለው ማሄጃ፣

ገለዓድን አሂዳለችና፤

4የወልደ አዴርን ምሽጎች እንዲበላ፣

በአዛሄል ቤት ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

5የደማስቆን በሮች እሰባብራለሁ፤

በቤት ዔደን በትር የያዘውን፣

በአዌን1፥5 አዌን የቃሉ ትርጕም ክፋት እንደ ማለት ነው። ሸለቆ ያለውን ንጉሥ1፥5 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤

የሶርያም ሕዝብ ተማርኮ ወደ ቂር ይሄዳል”

ይላል እግዚአብሔር

6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጋዛ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ በመውሰድ፣

ለኤዶም ሸጣለችና።

7ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጋዛ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

8በአስቀሎና በትር የያዘውን፣

የአሽዶድንም ንጉሥ1፥8 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰው

እስኪሞት ድረስ፣

እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

9እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጢሮስ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም።

የወንድማማችነትን ቃል ኪዳን በማፍረስ፣

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ ለኤዶም ሸጣለችና።

10ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጢሮስ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

11እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የኤዶም ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ርኅራኄን1፥11 ወይም ሰይፍ ወይም ከእርሱ ጋር የተባበሩትን አጠፉ በመንፈግ፣

ወንድሙን በሰይፍ አሳድዶታልና፤

የቍጣውንም ነበልባል ሳይገድብ፣

መዓቱን ሳያቋርጥ አውርዶበታልና፤

12የባሶራን ምሽጎች እንዲበላ፣

በቴማን ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የአሞን ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ድንበሩን ለማስፋት፣

የገለዓድን ነፍሰ ጡር ሴቶች ሆድ ቀድዷልና።

14በጦርነት ቀን በጩኸት ውስጥ፣

በማዕበል ቀን በዐውሎ ነፋስ ውስጥ፣

ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በረባት ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

15ንጉሧ1፥15 ወይም ሞሎክ በዕብራይስጡ ማልካም ይላል። ከሹማምቱ ጋር፣

በአንድነት ተማርኮ ይሄዳል፣”

ይላል እግዚአብሔር

Nova Versão Internacional

Amós 1:1-15

1Palavras que Amós, criador de ovelhas em Tecoa, recebeu em visões, a respeito de Israel, dois anos antes do terremoto. Nesse tempo, Uzias era rei de Judá e Jeroboão, filho de Jeoás, era rei de Israel.

2Ele disse:

“O Senhor ruge de Sião

e troveja de Jerusalém;

secam-se1.2 Ou pranteiam as pastagens dos pastores,

e murcha o topo do Carmelo”.

Julgamento dos Povos Vizinhos de Israel

3Assim diz o Senhor:

“Por três transgressões de Damasco

e ainda mais por quatro, não anularei o castigo.

Porque trilhou Gileade

com trilhos de ferro pontudos,

4porei fogo na casa de Hazael,

e as chamas consumirão as fortalezas de Ben-Hadade.

5Derrubarei a porta de Damasco;

destruirei o rei que está no vale1.5 Ou os habitantes do vale de Áven1.5 Áven significa iniquidade.

e aquele que segura o cetro em Bete-Éden1.5 Bete-Éden significa casa do prazer..

O povo da Síria irá para o exílio em Quir”,

diz o Senhor.

6Assim diz o Senhor:

“Por três transgressões de Gaza,

e ainda mais por quatro, não anularei o castigo.

Porque levou cativas comunidades inteiras

e as vendeu a Edom,

7porei fogo nos muros de Gaza,

e as chamas consumirão as suas fortalezas.

8Destruirei o rei1.8 Ou os habitantes de Asdode

e aquele que segura o cetro em Ascalom.

Erguerei a minha mão contra Ecrom,

até que morra o último dos filisteus”,

diz o Senhor, o Soberano.

9Assim diz o Senhor:

“Por três transgressões de Tiro,

e ainda mais por quatro,

não anularei o castigo.

Porque vendeu comunidades inteiras de cativos a Edom,

desprezando irmãos,

10porei fogo nos muros de Tiro,

e as chamas consumirão as suas fortalezas”.

11Assim diz o Senhor:

“Por três transgressões de Edom,

e ainda mais por quatro, não anularei o castigo.

Porque com a espada perseguiu seu irmão

e reprimiu toda a compaixão,1.11 Ou e destruiu os seus aliados,

mutilando-o furiosamente

e perpetuando para sempre a sua ira,

12porei fogo em Temã,

e as chamas consumirão as fortalezas de Bozra”.

13Assim diz o Senhor:

“Por três transgressões de Amom,

e ainda mais por quatro,

não anularei o castigo.

Porque rasgou ao meio as grávidas de Gileade

a fim de ampliar as suas fronteiras,

14porei fogo nos muros de Rabá,

e as chamas consumirão as suas fortalezas

em meio a gritos de guerra no dia do combate,

em meio a ventos violentos num dia de tempestade.

15O seu rei irá para o exílio,

ele e toda a sua corte”,

diz o Senhor.