ናሆም 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ናሆም 2:1-13

የነነዌ አወዳደቅ

1ነነዌ ሆይ፤ አጥቂ መጥቶብሻል፤

ምሽግሽን ጠብቂ፤

መንገድሽን ሰልዪ፤

ወገብሽን ታጠቂ፤

ኀይልሽን ሁሉ አሰባስቢ።

2አጥፊዎች ባድማ ቢያደርጓቸውም፣

የወይን ተክል ቦታቸውን ቢያጠፉባቸውም፣

እንደ እስራኤል ክብር ሁሉ፣

እግዚአብሔር የያዕቆብንም ክብር ይመልሳል።

3የወታደሮቹ ጋሻ ቀይ ነው፤

ተዋጊዎቹ ቀይ ልብስ ለብሰዋል፤

ዝግጁ በሆኑበት ቀን፣

የሠረገሎቹ ብረት ያብረቀርቃል፤

የጦሩ ዘንግ ይወዛወዛል2፥3 የዕብራይስጡ ትርጕም ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናቱና የሱርስቱ ቅጆች ግን ፈረሰኞች ይፈጥናሉ ይላሉ።

4ሠረገሎች በአደባባይ ወዲያ ወዲህ ይከንፋሉ፤

በመንገዶችም ላይ ይርመሰመሳሉ፤

የሚንበለበል ፋና ይመስላሉ፤

እንደ መብረቅም ይወረወራሉ።

5ምርጥ ተዋጊዎቹን ይጠራል፤

ዳሩ ግን መንገድ ላይ ይሰናከላሉ፤

ወደ ከተማዪቱ ቅጥር ይሮጣሉ፤

መከላከያ ጋሻውም በቦታው አለ።

6የወንዙ በር ወለል ብሎ ተከፈተ፤

ቤተ መንግሥቱም ወደቀ።

7ከተማዪቱ መማረኳና መወሰዷ እንደማይቀር፣

አስቀድሞ ተነግሯል2፥7 የዕብራይስጡ ቃል ትርጕም በትክክል አይታወቅም።

ሴቶች ባሪያዎቿ እንደ ርግብ ያለቅሳሉ፤

ደረታቸውንም ይደቃሉ።

8ነነዌ እንደ ኵሬ ናት፤

ውሃዋም ይደርቃል፤

“ቁም! ቁም!” ብለው ይጮኻሉ፤

ነገር ግን ወደ ኋላ የሚመለስ የለም።

9ብሩን ዝረፉ!

ወርቁን ንጠቁ!

በየግምጃ ቤቱ ያለው፣

የተከማቸውም ሀብት ስፍር ቍጥር የለውም።

10ተበዝብዛለች፤ ተዘርፋለች፤ ተራቍታለች።

ልብ ቀልጧል፤ ጕልበት ተብረክርኳል፤

ሰውነት ተንቀጥቅጧል፤ ፊት ሁሉ ገርጥቷል።

11አሁን ታዲያ የአንበሶቹ ዋሻ፣

ደቦሎቻቸውን ያበሉበት

ወንዱና ሴቷ አንበሳ የሄዱበት፣

ግልገሎችም ሳይፈሩ የተሰማሩበት ቦታ ወዴት ነው?

12አንበሳው ለግልገሎቹ የሚበቃውን ያህል ገደለ፤

ለእንስቶቹም ዐንቆ ገደለላቸው፤

የገደለውን በማረፊያ ቦታው፣

የነጠቀውንም በዋሻው ሞልቶታል።

13የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በእናንተ ላይ ተነሥቼባችኋለሁ፤

ሠረገሎቻችሁን አቃጥዬ አጨሳለሁ፤

ደቦል አንበሶቻችሁን ሰይፍ ይበላል፤

የምትበሉትን በምድር ላይ አልተውላችሁም፤

የመልእክተኞቻችሁም ድምፅ፣

ከእንግዲህ ወዲያ አይሰማም።”

Thai New Contemporary Bible

นาฮูม 2:1-13

นีนะเวห์จะล่มสลาย

1นีนะเวห์เอ๋ย ผู้โจมตีได้รุดหน้ามารบกับเจ้าแล้ว

จงเข้าประจำป้อม

เฝ้าทางไว้

เตรียมตัวให้ทะมัดทะแมง

และระดมกำลังทั้งหมดมา!

2องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงคืนความรุ่งเรืองให้ยาโคบ

เช่นเดียวกับความรุ่งเรืองของอิสราเอล

แม้ผู้ทำลายได้ทำให้มันเริศร้าง

และทำลายเถาองุ่นของมัน

3โล่ทหารของเขาเป็นสีแดง

นักรบก็สวมชุดสีแดงเข้ม

โลหะที่ตัวรถม้าศึกเปล่งประกายแวบวาบ

ในวันที่พวกเขาเตรียมพร้อม

หอกไม้สนก็กวัดแกว่ง2:3 ฉบับ LXX. และ Syr. ว่าม้าศึกก็ผาดโผนไปมา

4รถม้าศึกห้อตะบึงไปตามถนน

รีบรุดไปมาผ่านลานเมือง

มองดูเหมือนคบเพลิงลุกโชน

พวกเขาวิ่งปราดไปมาเหมือนสายฟ้า

5เขาระดมกองทหารที่หามาได้

แต่พวกเขาสะดุดล้มกลางทาง

พวกเขากรูเข้าไปที่กำแพงเมือง

โล่ป้องกันตั้งประจำที่

6ประตูด้านแม่น้ำถูกทำลายลง

และพระราชวังพังครืน

7มีประกาศิต2:7 ในภาษาฮีบรูคำนี้มีความหมายไม่ชัดเจนให้กรุงนั้น

ถูกจับและพาไปเป็นเชลย

พวกทาสหญิงร้องครวญครางเหมือนนกพิราบ

และตีอกชกตัว

8นีนะเวห์เป็นเหมือนสระ

และน้ำกำลังจะไหลออกไปหมด

พวกเขาร้องว่า “หยุดก่อน! หยุดก่อน!”

แต่ไม่มีใครหันกลับมา

9จงปล้นเงิน!

จงปล้นทอง!

ข้าวของมากมายใช้ไม่หมด

ทรัพย์สมบัติจากทุกคลังของนีนะเวห์มีมากเหลือเกิน!

10มันถูกปล้นทำลาย ถูกริบของมีค่าไปหมด!

หัวใจก็อ่อนล้า แข้งขาก็สิ้นแรง

เนื้อตัวสั่นเทาและทุกคนหน้าซีดเซียว

11ไหนล่ะถ้ำสิงโต

ที่พวกมันเลี้ยงดูลูกอ่อน

ไหนล่ะราชสีห์พ่อแม่ลูก

ที่ไม่หวั่นเกรงสิ่งใด?

12สิงโตที่ฆ่าเหยื่อมาให้ลูกๆ ของมันอย่างเพียงพอ

และคาบมาให้คู่ของมัน

แล้วสะสมเหยื่อไว้เต็มถ้ำ

สะสมสัตว์ที่มันฆ่าไว้เต็มรัง

13พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ประกาศว่า

“เราเป็นศัตรูกับเจ้า

เราจะเผารถม้าศึกของเจ้าจนควันโขมง

และดาบจะฟาดฟันสิงห์หนุ่มของเจ้า

เราจะไม่เหลือเหยื่อให้เจ้าบนโลกนี้

จะไม่ได้ยินเสียงผู้สื่อสารของเจ้าอีกต่อไป”