ነህምያ 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ነህምያ 3:1-32

የቅጥሩ ሠራተኞች

1ሊቀ ካህናቱ ኤልያሴብና ወንድሞቹ ካህናት ለሥራ ተነሡ፤ የበጎች በር የተባለውንም እንደ ገና ሠሩ። ቀደሱት፤ መዝጊያዎቹንም በየቦታቸው ላይ አቆሙ። መቶ ማማ እስከሚባለው ግንብና ሐናንኤል ማማ ተብሎ እስከሚጠራው ድረስ ሠርተው ቀደሱት፤ 2ቀጥሎ ያለውንም የኢያሪኮ ሰዎች ሠሩ፤ እነርሱ ከሠሩት ቀጥሎ ደግሞ የአምሪ ልጅ ዘኩር ሠራ።

3የዓሣ በሩን የሃስናአ ልጆች ሠሩ፤ እነርሱም ምሰሶዎቹን አቁመው መዝጊያዎቹን፣ መቀርቀሪያዎቹንና መወርወሪያዎቹን በየቦታቸው አኖሩ።

4የአቆስ ልጅ የኦርዮ ልጅ ሜሪሞት ከዚያ ቀጥሎ ያለውን ክፍል መልሶ ሠራ። ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን የሜሴዜቤል ልጅ የበራክያ ልጅ ሜሱላም መልሶ ሠራ። ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን የበዓና ልጅ ሳዶቅ መልሶ ሠራ፤ 5የሚቀጥለውን ክፍል የቴቁሐ ሰዎች መልሰው ሠሩ፤ መኳንንቶቻቸው ግን በተቈጣጣሪ አሠሪዎቻቸው3፥5 ጌቶቻቸው፤ ወይም ገዦቻቸው ሥር ሆነው በሥራው መጠመድ አልፈለጉም።

6አሮጌውን3፥6 ወይም የይሻናን በር የፋሴሐ ልጅ ዮዳሄና የበሶድያ ልጅ ሜሱላም መልሰው ሠሩ፤ እነርሱም ምሰሶዎቹን አቁመው መዝጊያዎቹን፣ ማያያዣዎቹንና መወርወሪያዎቹን በየቦታቸው አኖሩ። 7ከእነርሱም ቀጥሎ የዕድሳቱ ሥራ የተከናወነው በኤፍራጥስ ማዶ በሚገኘው አገረ ገዥ ሥልጣን ሥር ባሉት በገባዖንና በምጽጳ ሰዎች በገባዖናዊው በመልጥያና በሜሮኖታዊው በያዶን ነበር። 8ከወርቅ አንጥረኞች አንዱ የሆነው የሐርሃያ ልጅ ዑዝኤል የሚቀጥለውን ክፍል ሠራ፤ ከሽቱ ቀማሚዎች አንዱ የሆነው ሐናንያ ደግሞ ከዚያ ቀጥሎ ያለውን መልሶ ሠራ። እነርሱም “ሰፊው ቅጥር” ተብሎ እስከሚጠራው ድረስ ኢየሩሳሌምን መልሰው ሠሩ። 9ከዚያ የሚቀጥለውን ክፍል የኢየሩሳሌም አውራጃ እኩሌታ ገዥ የሆነው የሆር ልጅ ረፋያ መልሶ ሠራ። 10የኤርማፍ ልጅ ይዳያ ከቤቱ ፊት ለፊት ያለውን ክፍል መልሶ ሠራ፤ የአሰበንያ ልጅ ሐጡስ ደግሞ ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን መልሶ ሠራ። 11የካሪም ልጅ መልክያና የፈሐት ሞዓብ ልጅ አሱብ ሌላውን ክፍልና “የእቶን ግንብ” ተብሎ የሚጠራውን መልሰው ሠሩ። 12የኢየሩሳሌም አውራጃ እኩሌታ ገዥ የሆነው የአሎኤስ ልጅ ሰሎም ከሴት ልጆቹ ጋር በመሆን ቀጥሎ ያለውን ክፍል መልሶ ሠራ።

13“የሸለቆ በር” ተብሎ የሚጠራውን የሐኖንና የዛኖ ነዋሪዎች ዐደሱት፤ መልሰው ሠሩት፤ ከሠሩትም በኋላ መዝጊያዎቹን በየቦታቸው አኖሩ፤ መወርወሪያዎቹንና መቀርቀሪያዎቹንም አበጁ። እንዲሁም “የቈሻሻ መጣያ በር” ተብሎ እስከሚጠራው ድረስ ያለውን አንድ ሺሕ ክንድ3፥13 450 ሜትር ያህል ነው። ቅጥር መልሰው ሠሩ።

14“የቈሻሻ መጣያ በር” ተብሎ የሚጠራው የቤት ሐካሪም አውራጃ ገዥ የሆነው የሬካብ ልጅ መልክያ መልሶ ሠራ፤ መልሶ ከሠራ በኋላም መዝጊያዎቹን፣ መቀርቀሪያዎቹንና መወርወሪያዎቹን በየቦታቸው አኖረ።

15የምጽጳ አውራጃ የኮልሖዜ ልጅ ሰሎም “የምንጭ በር” ተብሎ የሚጠራውን መልሶ ሠራ፤ መልሶ ከሠራም በኋላ ከድኖ መዝጊያዎቹን በየቦታቸው አኖረ፤ መወርወሪያዎቹንና መቀርቀሪያዎቹንም አበጀ። “የንጉሥ አትክልት ቦታ” ተብሎ በሚጠራው አጠገብ የሚገኘውን የሼላን መዋኛ ግንብም፣ ከዳዊት ከተማ ጀምሮ ቍልቍል እስከሚወርደው ደረጃ ድረስ መልሶ ሠራ። 16ከእርሱም በኋላ የቤት ጹር አውራጃ እኩሌታ ገዥ የዓዝቡቅ ልጅ ነህምያ እስከ ዳዊት መቃብር ትይዩ እስከ ሰው ሠራሹ ኵሬና “የጀግኖች ቤት” ተብሎ እስከሚጠራው ድረስ ያለውን መልሶ ሠራ።

17ከእርሱ ቀጥሎ ሌዋውያኑ በባኒ ልጅ በሬሁ ሥር ሆነው የዕድሳት ሥራ ሠሩ። ከእርሱ ቀጥሎ የቅዒላ አውራጃ እኩሌታ ገዥ ሐሸብያ አውራጃውን መልሶ ሠራ። 18ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን ክፍል ደግሞ የሌላው የቅዒላ አውራጃ እኩሌታ ገዥ የኤንሐዳድ ልጅ በዋይና በእርሱም ሥር የነበሩት የአገሩ ሰዎች መልሰው ሠሩ። 19ከእርሱም ቀጥሎ ወደ ጦር መሣሪያ ግምጃ ቤት በሚያወጣውና እስከ ማእዘኑ በሚደርሰው ትይዩ ያለውን ሌላ ክፍል የምጽጳ ገዥ የኢያሱ ልጅ ኤጽር መልሶ ሠራ። 20ከእርሱም ቀጥሎ የዘባይ ልጅ ባሮክ ከማእዘኑ ጀምሮ እስከ ሊቀ ካህኑ እስከ ኤልያሴብ ቤት መግቢያ ያለውን ሌላ ክፍል በትጋት መልሶ ሠራ። 21ከእርሱ ቀጥሎ ከኤልያሴብ ቤት መግቢያ ጀምሮ እስከ መጨረሻው ያለውን ሌላ ክፍል የአቆስ ልጅ የኦርዮ ልጅ ሜሪሞት መልሶ ሠራ።

22ከእርሱም ቀጥሎ ያለውን ክፍል ከአካባቢው የመጡት ካህናት መልሰው ሠሩ። 23ከእነርሱ ቀጥሎ ብንያምና አሱብ ከቤታቸው ፊት ለፊት ያለውን መልሰው ሠሩ፤ ከእነርሱም ቀጥሎ የሐናንያ ልጅ የመዕሤያ ልጅ ዓዛርያስ በቤቱ አጠገብ ያለውን መልሶ ሠራ። 24ከእርሱም ቀጥሎ ከዓዛርያስ ቤት ጀምሮ እስከ ማእዘኑና እስከ ማእዘኑም ጫፍ ያለውን ሌላውን ክፍል የኤንሐደድ ልጅ ቢንዊ መልሶ ሠራ፤ 25የኡዛይ ልጅ ፋላል ከቅጥሩ ማእዘን ትይዩና በዘብ መጠበቂያው አደባባይ አጠገብ ካለው ከላይኛው ቤተ መንግሥት መጠበቂያ ግንብ ጀምሮ ያለውን መልሶ ሠራ። ከእርሱም ቀጥሎ የፋሮስ ልጅ ፈዳያና 26በዖፌል ኰረብታ ላይ የሚኖሩት የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች “የውሃ በር” ተብሎ ከሚጠራው ትይዩ ጀምሮ በስተ ምሥራቅ እስከሚገኘው ግንብ ድረስ መልሰው ሠሩ። 27ከእነርሱ ቀጥሎ የቴቁሐ ሰዎች ከታላቁ ግንብ ትይዩ ጀምሮ እስከ ዖፌል ቅጥር ድረስ ያለውን ሌላ ክፍል መልሰው ሠሩ።

28“የፈረስ በር” ተብሎ ከሚጠራው በላይ ያለውን ደግሞ ካህናቱ እያንዳንዳቸው በየመኖሪያ ቤታቸው ትይዩ ያለውን መልሰው ሠሩ። 29ከእነርሱም ቀጥሎ የኢሜር ልጅ ሳዶቅ በቤቱ ትይዩ ያለውን መልሶ ሠራ። ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን “የምሥራቅ በር” ጠባቂ የሆነው የሴኬንያ ልጅ ሸማያ መልሶ ሠራ። 30ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን ሌላ ክፍል ደግሞ የሰሌምያ ልጅ ሐናንያና የሴሌፍ ስድስተኛ ልጅ ሐኖን መልሰው ሠሩ። ከእነርሱም ቀጥሎ የበራክያ ልጅ ሜሱላም ከመኖሪያው ትይዩ ያለውን መልሶ ሠራ። 31ከእርሱ ቀጥሎ ከወርቅ አንጥረኞች አንዱ መልክያ በመቈጣጠሪያው በር ትይዩ እስከሚገኘው እስከ ቤተ መቅደሱ አገልጋዮችና እስከ ነጋዴዎቹ ቤት፣ እንዲሁም ከማእዘኑ በላይ እስከሚገኘው ክፍል ያለውን መልሶ ሠራ፤ 32ከማእዘኑ በላይ ከሚገኘው ክፍል ጀምሮ እስከ በጎች በር ያለውን ደግሞ ወርቅ አንጥረኞቹና ነጋዴዎቹ መልሰው ሠሩ።

Thai New Contemporary Bible

เนหะมีย์ 3:1-32

ผู้สร้างกำแพงเมือง

1มหาปุโรหิตเอลียาชีบและปุโรหิตอื่นๆ จึงลงมือซ่อมแซมประตูแกะ ทำพิธีถวายและติดตั้งประตู ซ่อมไปจนถึงหอคอยหนึ่งร้อยซึ่งพวกเขาทำพิธีถวาย และซ่อมไปจนถึงหอคอยฮานันเอล 2ชาวเมืองเยรีโคสร้างส่วนถัดไป และศักเกอร์บุตรอิมรีก็สร้างส่วนถัดไป

3บุตรทั้งหลายของหัสเสนาอาห์ซ่อมแซมประตูปลา เขาวางไม้คาน ติดตั้งประตู สลัก และดาล 4เมเรโมทบุตรอุรียาห์บุตรของฮักโขสซ่อมช่วงถัดไป เมชุลลามบุตรเบเรคิยาห์บุตรของเมเชซาเบลซ่อมแซมช่วงถัดจากเขา และศาโดกบุตรบาอานาซ่อมแซมช่วงถัดไป 5ถัดไปได้แก่ชาวเมืองเทโคอา แต่บรรดาขุนนางของเขาไม่ยอมทำงานตามคำสั่งของผู้ดูแล3:5 หรือเจ้านายของเขาหรือผู้ปกครอง

6โยยาดาบุตรปาเสอาห์กับเมชุลลามบุตรเบโสไดอาห์ซ่อมแซมประตูเยชานาห์3:6 หรือประตูเก่า พวกเขาวางคาน ติดตั้งประตู สลัก และดาล 7ถัดไปคืองานซ่อมแซมของเมลาติยาห์จากกิเบโอนกับของยาโดนจากเมโรโนท คนจากกิเบโอนและมิสปาห์ซึ่งเป็นเจ้าหน้าที่ของผู้ว่าการอีกฟากหนึ่งของแม่น้ำยูเฟรติส 8อุสซีเอลบุตรฮารฮายาห์ซึ่งเป็นช่างทองซ่อมแซมส่วนถัดไป ถัดจากนั้นคือฮานันยาห์ผู้ปรุงน้ำหอม พวกเขาซ่อมแซม3:8 หรือพวกเขาทิ้งส่วนของเยรูซาเล็มไปถึงกำแพงกว้าง 9เรไฟยาห์บุตรเฮอร์ผู้ปกครองเยรูซาเล็มครึ่งหนึ่งซ่อมแซมส่วนถัดไป 10ถัดไปคือเยดายาห์บุตรฮารุมัฟซ่อมส่วนที่อยู่ตรงข้ามบ้านของเขา ถัดไปคือฮัททัชบุตรฮาชับเนยาห์ 11มัลคียาห์บุตรฮาริมกับหัสชูบบุตรปาหัทโมอับซ่อมแซมอีกช่วงหนึ่งพร้อมทั้งหอคอยเตาอบ 12ชัลลูมบุตรฮัลโลเหชกับบรรดาบุตรสาวของเขาซ่อมแซมส่วนถัดไป เขาเป็นผู้ปกครองเยรูซาเล็มอีกครึ่งหนึ่ง

13ฮานูนกับชาวศาโนอาห์ซ่อมแซมประตูหุบเขา ติดตั้งประตู สลัก และดาล และซ่อมกำแพงยาว 1,000 ศอก3:13 คือ ประมาณ 450 เมตร ไปจนถึงประตูกองขยะ

14ผู้ที่ซ่อมประตูกองขยะคือ มัลคียาห์บุตรเรคาบผู้ปกครองเขตเบธฮัคเคเรม เขาซ่อมแซมและติดตั้งประตู สลัก และดาล

15ชัลลูมบุตรโคลโฮเซห์ผู้ปกครองเขตมิสปาห์ ซ่อมแซมประตูน้ำพุ และติดหลังคา ติดประตู สลัก และดาล และซ่อมกำแพงจากสระสิโลอัม3:15 ภาษาฮีบรูว่าเชลาห์เป็นอีกรูปหนึ่งของชิโลอาห์คือ สิโลอัมข้างอุทยานหลวงถึงขั้นบันไดจากเมืองดาวิด 16ถัดจากเขาคือเนหะมีย์บุตรอัสบูกผู้ปกครองเขตเบธซูร์ครึ่งหนึ่ง สร้างไปถึงจุดตรงข้ามสุสานของ3:16 สำเนา Vulg. บางฉบับ และฉบับ LXX. และ Syr. ว่าอุโมงค์ฝังพระศพดาวิดไปจนถึงอ่างเก็บน้ำและโรงทหาร

17ถัดไปเป็นกลุ่มคนเลวีภายใต้การกำกับดูแลของเรฮูมบุตรบานี ข้างๆ เขาคือฮาชาบิยาห์ผู้ปกครองเขตเคอีลาห์ครึ่งหนึ่ง ซึ่งซ่อมแซมส่วนที่อยู่ในเขตของเขา 18ถัดมาคือพี่น้องร่วมวงศ์ของเขานำโดยบินนุย3:18 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูส่วนใหญ่ว่าบัฟวัยบุตรเฮนาดัดผู้ปกครองเขตเคอีลาห์อีกครึ่งหนึ่ง 19ถัดจากเขาคือเอเซอร์บุตรเยชูอาผู้ปกครองเขตมิสปาห์ ซ่อมจากจุดที่หันหน้าไปทางขึ้นคลังอาวุธถึงมุมกำแพง 20ถัดมาคือบารุคบุตรศับบัยได้ซ่อมแซมอย่างแข็งขันจากมุมกำแพงไปถึงทางเข้าบ้านมหาปุโรหิตเอลียาชีบ 21ถัดมาคือเมเรโมทบุตรอุรียาห์บุตรของฮักโขส ซ่อมกำแพงจากทางเข้าบ้านของเอลียาชีบถึงริมสุดบ้าน

22ถัดมาซ่อมแซมโดยบรรดาปุโรหิตจากภูมิภาครอบๆ 23ถัดขึ้นไปเบนยามินกับหัสชูบซ่อมส่วนหน้าบ้านของเขา ถัดจากนั้นอาซาริยาห์บุตรมาอาเสอาห์ บุตรของอานานิยาห์ ซ่อมส่วนที่อยู่ข้างบ้านของเขา 24ถัดไปคือบินนุยบุตรเฮนาดัด ซ่อมอีกส่วนหนึ่งจากบ้านของอาซาริยาห์จนถึงมุมกำแพง 25ปาลาลบุตรอุซัยรับช่วงงานจากตรงข้ามมุมกำแพงและหอคอยที่ยื่นจากตำหนักบนซึ่งใกล้ลานทหารรักษาพระองค์ ถัดไปคือเปดายาห์บุตรปาโรช 26และผู้ช่วยงานในพระวิหารซึ่งอาศัยอยู่บนเนินเขาโอเฟล ซ่อมกำแพงไปจนถึงจุดตรงข้ามประตูน้ำไปทางตะวันออกและหอคอยที่ยื่นออกไป 27ถัดมาคือชาวเทโคอาซึ่งซ่อมกำแพงอีกช่วงหนึ่งจากหอคอยใหญ่ที่ยื่นออกไปจนถึงกำแพงโอเฟล

28บรรดาปุโรหิตซ่อมกำแพงเหนือประตูม้า แต่ละคนซ่อมส่วนที่อยู่หน้าบ้านของตน 29ถัดจากนั้นศาโดกบุตรอิมเมอร์ซ่อมส่วนที่อยู่ตรงข้ามบ้านของเขา ถัดไปคือเชไมอาห์บุตรเชคานิยาห์ยามประตูตะวันออกเป็นผู้ซ่อมแซม 30ถัดจากเขาคือฮานันยาห์บุตรเชเลมิยาห์ ฮานูนบุตรคนที่หกของศาลาฟซ่อมอีกส่วนหนึ่ง ถัดไปเมชุลลามบุตรเบเรคิยาห์ซ่อมแซมส่วนที่ตรงข้ามที่พักของเขา 31ถัดไปมัลคียาห์ช่างทองซ่อมแซมไปจนถึงเรือนผู้ช่วยงานในพระวิหารและเรือนพ่อค้า ตรงข้ามประตูตรวจตราไปจนถึงห้องชั้นบนตรงหัวมุม 32ช่างทองและพ่อค้าอื่นๆ ซ่อมส่วนที่อยู่ระหว่างห้องชั้นบนตรงหัวมุมนี้ไปจนถึงประตูแกะ