ቈላስይስ 2 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ቈላስይስ 2:1-23

1ስለ እናንተና በሎዶቅያ ስላሉት እንዲሁም በአካል አይተውኝ ስለማያውቁ ሁሉ ምን ያህል እየተጋደልሁ እንደ ሆነ እንድታውቁ እፈልጋለሁ፤ 2ደግሞም ልባቸው እንዲጽናናና በፍቅር እንዲተሳሰሩ፣ ፍጹም የሆነውን የመረዳት ብልጽግና አግኝተው የእግዚአብሔር ምስጢር የሆነውን ክርስቶስን እንዲያውቁ እተጋለሁ፤ 3የተሰወረ የጥበብና የዕውቀት ሀብት ሁሉ የሚገኘው በእርሱ ዘንድ ነውና። 4ማንም ንግግር በማሳመር እንዳያታልላችሁ ይህን እነግራችኋለሁ። 5ምንም በሥጋ ከእናንተ ርቄ ብገኝ በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝና በሥርዐት መኖራችሁንና በክርስቶስ ያላችሁን ጽኑ እምነት እያየሁ ደስ ይለኛል።

ከሰው ሠራሽ ሥርዐት በክርስቶስ ነጻ መሆን

6እንግዲህ ጌታ ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ተቀበላችሁት እንዲሁ በእርሱ ኑሩ፤ 7በእርሱ ተተክላችሁና ታንጻችሁ እንደ ተማራችሁት በእምነት ጸንታችሁ፣ የተትረፈረፈ ምስጋና እያቀረባችሁ ኑሩ።

8በክርስቶስ ላይ ሳይሆን፣ በሰዎች ልማድና በዚህ ዓለም መሠረታዊ ሕግጋት ላይ በተመሠረተ ፍልስፍናና ከንቱ ማግባቢያ ማንም ማርኮ እንዳይወስዳችሁ ተጠንቀቁ።

9የመለኮት ሙላት ሁሉ በአካል በእርሱ ይኖራልና፤ 10እናንተም የገዥነትና የሥልጣን ሁሉ ራስ በሆነው በክርስቶስ ሙሉ ሆናችኋል። 11በእርሱ ሆናችሁ በእጅ ባልተደረገ መገረዝ ተገረዛችሁ፤ በክርስቶስም መገረዝ የሥጋን ኀጢአታዊ ባሕርይ አስወገዳችሁ፤ 12በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፣ እርሱን ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር ኀይል በማመን ከእርሱ ጋር ደግሞ ተነሣችሁ።

13እናንተም በበደላችሁና የሥጋችሁን ኀጢአታዊ ባሕርይ ባለ መገረዝ ሙታን ሳላችሁ፣ እግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ሕያዋን አደረጋችሁ2፥13 አንዳንድ የጥንት ቅጆች አደረገን ይላሉ።፤ ኀጢአታችንንም ሁሉ ይቅር አለን፤ 14ሲቃወመንና ሲጻረረን የነበረውን የዕዳ ጽሕፈት ከነሕግጋቱ በመደምሰስ፣ በመስቀል ላይ ቸንክሮ ከመንገድ አስወገደው። 15የአለቆችንና የባለሥልጣናትንም ማዕረግ በመግፈፍ በመስቀሉ2፥15 ወይም በእርሱ ድል ነሥቶ በአደባባይ እያዞራቸው እንዲታዩ አደረገ።

16እንግዲህ በምትበሉትም ሆነ በምትጠጡት ወይም በዓልን፣ ወር መባቻንና ሰንበትን በማክበር ነገር ማንም አይፍረድባችሁ፤ 17እነዚህ ሊመጡ ላሉ ነገሮች ጥላ ናቸውና፤ አካሉ ግን የክርስቶስ ነው። 18ዐጕል ትሕትናንና የመላእክትን አምልኮ የሚወድድ ማንም ሰው እንዳያደናቅፋችሁ ተጠንቀቁ። እንደዚህ ያለ ሰው ስላየው ራእይ ከመጠን በላይ ራሱን እየካበ በሥጋዊ አእምሮው ከንቱ ሐሳብ ተሞልቶ ይታበያል፤ 19ይህ ሰው፣ አካል ሁሉ በጅማትና በማሰሪያ እየተጋጠመ ምግብንም እየተቀበለ እግዚአብሔር በሚሰጠው ማደግ ከሚያድግበት ራስ ከሆነው ጋር ግንኙነት የለውም።

20ለዚህ ዓለም መርሕ ከክርስቶስ ጋር ከሞታችሁ፣ ታዲያ ለምን እንደዚህ ዓለም ሰው ለሕጎቹ ተገዥ ትሆናላችሁ? 21“አትያዝ! አትቅመስ! አትንካ!” እንደሚሉት ዐይነት፣ 22እነዚህ ሁሉ በሰው ትእዛዝና ትምህርት ላይ የተመሠረቱ ስለሆኑ በተግባር ላይ ሲውሉ ጠፊ ናቸው። 23እነዚህ ነገሮች በገዛ ራስ ላይ ከሚፈጥሩት የአምልኮ ስሜት፣ ከዐጕል ትሕትናና ሰውነትን ከመጨቈን አንጻር በርግጥ ጥበብ ያለባቸው ይመስላሉ፤ ነገር ግን የሥጋን ልቅነት ለመቈጣጠር አንዳች ፋይዳ የላቸውም።

Knijga O Kristu

Kološanima 2:1-23

1Želim da znate koliko sam se mučio za vas, za Crkvu u Laodiceji i za sve one koji me još nisu osobno upoznali. 2Želim da se njihova srca ohrabre, povezana u ljubavi, da dobiju bogatu i punu spoznaju Božje tajne: Krista. 3U njemu su skrivena sva bogatstva mudrosti i spoznaje.

4Govorim vam to da vas nitko ne prevari uvjerljivim riječima. 5Iako sam daleko od vas, u mislima sam s vama. Veoma me raduje što živite kako treba i što je vaša vjera u Krista čvrsta.

Sloboda od pravila i novi život u Kristu

6Kako ste prihvatili Krista za Gospodina, tako nastavite s njime živjeti. 7Budite u njemu ukorijenjeni pa ćete se izgrađivati i učvršćivati u vjeri kako ste i poučeni. Obilno zahvaljujte Bogu.

8Nemojte da vas tko odvuče ispraznim mudrovanjem koje se temelji na ljudskim predajama i na počelima ovoga svijeta, a ne na Kristu. 9Jer u Kristu doslovce prebiva sva punina božanstva, 10a vi ste ispunjeni kroz zajedništvo s njime, koji je iznad svakoga poglavarstva i vlasti u svemiru.

11Kad ste došli Kristu, “obrezani” ste, ali ne tjelesno. Bio je to duhovni zahvat—“odrezana” je vaša grešna narav. 12Jer s Kristom ste ukopani pri krštenju. I s njim ste uskrsnuli u novi život jer ste se pouzdali u moćnu Božju silu, koja je i Krista podignula od mrtvih.

13Bili ste nekoć mrtvi zbog svojih prijestupa i zbog toga što vaša grešna narav još nije bila “odrezana”. Tada vas je Bog oživio s Kristom. Oprostio nam je sve prijestupe. 14Izbrisao je zadužnicu čije su odredbe bile protiv nas. Pribio ju je na Kristov križ i uništio. 15Tako je Bog razoružao zle vladare i vlasti. Javno ih je osramotio pobjedom na Kristovu križu.

16Neka vas zato nitko ne osuđuje zbog jela, pića ili zbog svetkovanja blagdana, mlađaka ili subote. 17Jer ta su pravila bila tek sjena prave stvarnosti—Krista. 18Ne dajte da vam oni koji uživaju u lažnoj poniznosti i štovanju anđela kažu kako niste zaslužili nagradu. Takvi ljudi, oholi zbog svoje tjelesne pameti, unedogled nabrajaju pojedinosti viđenja koja su imali. 19Ali ne drže se Krista, glave Tijela koje je snažno povezano i koje raste samo dobivajući hranu i snagu od Boga.

20Ako ste zaista umrli s Kristom, onda vas je on oslobodio temeljnih počela ovoga svijeta. Zašto se onda, kao da još pripadate ovomu svijetu, podvrgavate propisima kao što su: 21“Ne jedi! Ne kušaj! Ne takni!” 22Takva pravila obična su ljudska umotvorina jer se odnose na stvari koje uporabom nestaju. 23Ti propisi prividno su mudri zbog samozvanog bogoštovlja, poniznosti i trapljenja tijela, ali ne pomažu čovjeku da nadvlada svoje zle misli i želje.