ሮሜ 2 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሮሜ 2:1-29

የእግዚአብሔር ጻድቅ ፍርድ

1ስለዚህ አንተ በሌላው ላይ የምትፈርድ፣ የምታመካኝበት የለህም፤ በሌላው ላይ በምትፈርድበት ነገር ሁሉ፣ ራስህን ትኰንናለህ፤ ፈራጅ የሆንኸው አንተ ያንኑ ታደርጋለህና። 2እንደዚህ በሚያደርጉትም ላይ የእግዚአብሔር ፍርድ ትክክለኛ መሆኑን እናውቃለን። 3እንግዲህ አንተ ሰው በሌሎች ላይ እየፈረድህ ያንኑ የምታደርግ ከሆነ፣ ከእግዚአብሔር ፍርድ የምታመልጥ ይመስልሃል? 4ወይስ የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሓ የሚመራህ መሆኑን ሳትገነዘብ፣ የቸርነቱን፣ የቻይነቱንና የትዕግሥቱን ባለጠግነት ትንቃለህ?

5ነገር ግን በድንዳኔህና ንስሓ በማይገባ ልብህ ምክንያት ትክክለኛ ፍርዱ ሲገለጥ በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን በራስህ ላይ ቍጣን ታከማቻለህ። 6እግዚአብሔር “ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው ይሰጠዋል”። 7በጎ የሆነውን ጸንቶ በማድረግ ክብርን፣ ሞገስንና ዘላለማዊነትን ለሚሹ የዘላለም ሕይወት ይሰጣቸዋል። 8ነገር ግን በራስ ወዳዶች፣ እውነትን ትተው ክፋትን በሚከተሉ ፍርድና ቍጣ ይደርስባቸዋል። 9ክፉ በሚያደርግ በማንኛውም ሰው፣ አስቀድሞ በአይሁድ ከዚያም በአሕዛብ ላይ መከራና ጭንቀት ይሆናል፤ 10ነገር ግን በጎ ለሚሠራ ለማንኛውም፣ አስቀድሞ ለአይሁድ ከዚያም ለአሕዛብ ክብር፣ ሞገስና ሰላም ይሆንለታል፤ 11እግዚአብሔር ለማንም አያደላምና።

12ሕግ ሳይኖራቸው ኀጢአት የሠሩ ሁሉ ያለ ሕግ ይጠፋሉ፤ ሕግ እያላቸው ኀጢአት የሠሩ በሕግ ይፈረድባቸዋል፤ 13ምክንያቱም በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን የሚባሉት ለሕጉ የሚታዘዙ እንጂ፣ ሕጉን የሚሰሙ አይደሉም። 14ሕግ የሌላቸው አሕዛብ ሕግ የሚያዝዘውን ነገር በተፈጥሮ ሲያደርጉ፣ ሕግ ባይኖራቸውም እነርሱ ለራሳቸው ሕግ ናቸው። 15ኅሊናቸው ስለሚመሰክር፣ ሐሳባቸው ስለሚከስሳቸው፣ ደግሞም ስለሚከላከልላቸው የሕግ ትእዛዝ በልባቸው የተጻፈ መሆኑን ያሳያሉ። 16ይህም በወንጌል እንደማስተምረው እግዚአብሔር በሰው ልብ የተሰወረውን በክርስቶስ በኩል በሚፈርድበት ዕለት ግልጽ ይሆናል።

ሕግና አይሁድ

17አንተ ይሁዲ ነኝ ካልህ፣ በሕግ የምትተማመንና ከእግዚአብሔር ጋር ባለህ ግንኙነት የምትኵራራ፣ 18በሕግ በመመራትህም ፈቃዱን ዐውቀህ ፍጹም የሆነውን ለይተህ ከያዝህ፣ 19ለዕውሮች መሪ፣ በጨለማ ላሉትም ብርሃን መሆንህን ርግጠኛ ከሆንህ፣ 20በሕጉም ካገኘኸው ዕውቀትና እውነት የተነሣ አላዋቂ ለሆኑት መካሪ፣ ለሕፃናት አስተማሪ ከሆንህ፣ 21እንግዲህ አንተ ሌሎችን የምታስተምር፣ ራስህን አታስተምርምን? አትስረቅ ብለህ የምትሰብክ፣ ትሰርቃለህን? 22አንተ ሰዎች ማመንዘር የለባቸውም የምትል፣ ታመነዝራለህን? አንተ ጣዖትን የምትጸየፍ፣ ቤተ መቅደስን ትመዘብራለህን? 23አንተ በሕግ የምትመካ፣ ሕግን በመተላለፍ እግዚአብሔርን ታዋርዳለህን? 24ይህም “በእናንተ ምክንያት የእግዚአብሔር ስም በአሕዛብ ዘንድ ይሰደባል” ተብሎ እንደ ተጻፈው መሆኑ ነው።

25ሕግን የምትፈጽም ከሆነ ግዝረት ዋጋ አለው፤ ሕግን የምትተላለፍ ከሆነ ግን እንዳልተገረዝህ ትሆናለህ። 26ያልተገረዙት ሕጉ የሚያዝዘውን የሚፈጽሙ ከሆነ፣ እንደ ተገረዙ አይቈጠሩምን? 27አንተ የተጻፈ ሕግ፣ ግዝረትም ቢኖርህ፣ ሕግ ተላላፊ በመሆንህ፣ በሥጋ ያልተገረዘው ለሕግ በመታዘዙ ይፈርድብሃል።

28አንድ ሰው ለይምሰል በውጫዊው ብቻ ይሁዲ ልሁን ቢል ይሁዲ አይሆንም፤ እውነተኛ ግዝረትም ውጫዊና ሥጋዊ ሥርዐት አይደለም። 29ዳሩ ግን አንድ ሰው ይሁዲ የሚሆነው በውስጣዊ ማንነቱ ይሁዲ ሆኖ ሲገኝ ነው። ግዝረትም ግዝረት የሚሆነው በተጻፈው ሕግ ሳይሆን፣ በመንፈስ የልብ ግዝረት ሲኖር ነው። እንዲህ ያለው ሰው ምስጋናው ከሰው ሳይሆን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

羅馬書 2:1-29

上帝公義的審判

1因此,你這論斷人的啊,不管你是誰,都難逃罪責。你在什麼事上論斷別人,就在什麼事上定了自己的罪,因為你論斷別人的事,自己也在做。 2我們都知道,上帝必按真理審判做這些事的人。 3你這人啊,你論斷別人,自己卻做同樣的事,你以為自己能逃脫上帝的審判嗎? 4還是你藐視祂深厚的慈愛、寬容和忍耐,不知道祂的慈愛是要引導你悔改嗎? 5你這樣硬著心不肯悔改等於是為自己積蓄烈怒,上帝的烈怒在祂施行公義審判的那天必臨到你。 6上帝必照各人的行為施行賞罰。 7凡是恆心行善、尋求榮耀、尊貴和永恆福分的人,祂要把永生賜給他們; 8至於那些自私自利、違背真理、行為不義的人,祂的烈怒和怒氣要降在他們身上。 9一切作惡之人必受患難和痛苦,先是猶太人,然後是希臘人。 10祂要將榮耀、尊貴和平安賜給一切行善的人,先是猶太人,然後是希臘人。 11因為上帝不偏待人。

12沒有上帝律法的人若犯罪,雖然不按律法受審判,仍要滅亡;有上帝律法的人若犯罪,必按律法受審判。 13因為上帝眼中的義人不是聽到律法的人,而是遵行律法的人。 14沒有律法的外族人若順著天性做合乎律法的事,他們雖然沒有律法,自己就是自己的律法。 15這表明律法的要求刻在他們心裡,他們的良心也可以證明,因為他們的思想有時指控他們,有時為他們辯護。 16按照我所傳的福音,到了審判之日,上帝要藉著耶穌基督審判人一切隱祕的事。

猶太人與律法

17你自稱是猶太人,倚仗上帝所賜的律法,自誇與上帝有特別的關係; 18你受過律法的教導,知道上帝的旨意,能明辨是非; 19你自信可以做盲人的嚮導、黑暗中的人的光、 20愚昧人的師傅、小孩子的老師,因為你從律法中得到了知識和真理。 21那麼,你這教導別人的,為什麼不教導自己呢?你教導人不可偷盜,自己卻偷盜嗎? 22你告訴他人不可通姦,自己卻通姦嗎?你憎惡偶像,自己卻去偷廟裡的東西嗎? 23你以律法自誇,自己卻違犯律法羞辱上帝嗎? 24正如聖經上說:「因你們的緣故,上帝的名在外族人中受到褻瀆!」

25如果你遵行律法,割禮才有價值;如果你違犯律法,受了割禮也如同未受割禮。 26如果未受割禮的人遵行律法的教導,他豈不算是受了割禮嗎? 27身體未受割禮卻遵行律法的人,必審判你這有律法條文、受了割禮卻違犯律法的人。 28因為徒具外表的猶太人不是真正的猶太人,身體上的割禮也不是真正的割禮。 29唯有從心裡做猶太人的才是真猶太人,真割禮是藉著聖靈在心裡受的割禮,不在於律法條文。這樣的人得到的稱讚不是從人來的,而是從上帝來的。