ሮሜ 11 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሮሜ 11:1-36

የእስራኤል ቅሬታዎች

1እንግዲህ እግዚአብሔር ሕዝቡን ተዋቸውን? ብዬ እጠይቃለሁ፤ በፍጹም! እኔ ራሴ ከብንያም ነገድ፣ የአብርሃም ዘር የሆንሁ እስራኤላዊ ነኝ። 2እግዚአብሔር አስቀድሞ ያወቃቸውን ሕዝብ አልጣላቸውም። ኤልያስ በእስራኤል ላይ ክስ ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንዳቀረበ፣ መጽሐፍ ስለ እርሱ ምን እንደሚል አታውቁምን? 3“ጌታ ሆይ፤ ነቢያትህን ገድለዋል፤ መሠዊያዎችህን አፍርሰዋል፤ እኔም ብቻዬን ቀረሁ፤ ሊገድሉኝም ይፈልጋሉ።” 4እግዚአብሔር የሰጠው መልስ ግን ምን ነበር? “ለበኣል ያልሰገዱትን ሰባት ሺሕ ሰዎች ለራሴ አስቀርቻለሁ።”

5በአሁኑ ጊዜም እንደዚሁ በጸጋ የተመረጡ ቅሬታዎች አሉ። 6እንግዲህ በጸጋ ከሆነ በሥራ አይደለም፤ በሥራ ቢሆንማ ኖሮ ጸጋ፣ ጸጋ መሆኑ በቀረ ነበር።11፥6 አንዳንድ ቅጆች በሥራ ቢሆንማ ኖሮ ጸጋ መሆኑ በቀረ ነበር፤ በጸጋ ከሆነም ሥራ፣ ሥራ መሆኑ ይቀራል ይላሉ።

7እንግዲህ ምንድን ነው? እስራኤል አጥብቀው የፈለጉትን አላገኙትም፤ የተመረጡት ግን አገኙት፤ የቀሩትም ልባቸው ደነደነ፤ 8እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፤

“ዐይናቸው እንዳያይ፣

ጆሯቸውም እንዳይሰማ፣

እግዚአብሔር እስከዚህ ቀን ድረስ፣

የድንዛዜ መንፈስ ሰጣቸው።”

9ዳዊትም አለ፤

“ማእዳቸው አሽክላና ወጥመድ፣

ዕንቅፋትና ቅጣት ይሁንባቸው።

10ዐይኖቻቸው እንዳያዩ ይጋረዱ፤

ወገባቸውም ለዘላለም ይጕበጥ።”

የተዳቀሉ ቅርንጫፎች

11ተመልሰው እስከማይድኑ ድረስ ተሰናከሉን? ብዬ እንደ ገና እጠይቃለሁ፤ ከቶ አይደለም፤ ይልቁንም እስራኤልን ለማስቀናት ሲባል በእነርሱ መተላለፍ ምክንያት ድነት ለአሕዛብ መጥቷል። 12ነገር ግን የእነርሱ መተላለፍ ለዓለም በረከት ከሆነ፣ ውድቀታቸውም ለአሕዛብ በረከት ከሆነ፣ ሙላታቸው ምን ያህል ታላቅ በረከት ያመጣ ይሆን?

13አሕዛብ ሆይ፤ ለእናንተ እናገራለሁ፤ የአሕዛብ ሐዋርያ እንደ መሆኔ መጠን አገልግሎቴን በትጋት እፈጽማለሁ፤ 14ይኸውም የገዛ ወገኖቼን እንዲቀኑ አነሣሥቼ ከእነርሱ ጥቂቱን ለማዳን ተስፋ በማድረግ ነው። 15የእነርሱ መተው ለዓለም ዕርቅን ካስገኘ፣ ተቀባይነት ማግኘታቸውማ ከሞት መነሣት ነው ከማለት በቀር ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? 16በኵር ሆኖ የቀረበው የቡሖው ክፍል ቅዱስ ከሆነ፣ ቡሖው ደግሞ ቅዱስ ነው፤ ሥሩ ቅዱስ ከሆነ፣ ቅርንጫፎቹም ቅዱሳን ናቸው።

17ከቅርንጫፎቹ አንዳንዶቹ ቢሰበሩ፣ አንተም የበረሓ ወይራ ሆነህ ሳለ በሌሎቹ መካከል ገብተህ ከተጣበቅህና ከወይራው ዘይት ሥር የሚገኘውን በረከት ተካፋይ ከሆንህ፣ 18በእነዚያ ቅርንጫፎች ላይ አትኵራራ። ብትኰራ ግን ይህን አስተውል፤ አንተ ሥሩን አትሸከምም፤ ሥሩ ግን አንተን ይሸከምሃል እንጂ። 19እንግዲህ፣ “ቅርንጫፎች የተሰበሩት እኔ እንድገባ ነው” ትል ይሆናል። 20ትክክል ነው፤ እነርሱ የተሰበሩት ካለማመን የተነሣ ነው፤ አንተም በእምነት ቆመሃል፤ ፍራ እንጂ ትዕቢተኛ አትሁን። 21እግዚአብሔር በተፈጥሮ ቅርንጫፎች ለሆኑት ካልራራላቸው፣ ለአንተም አይራራልህምና።

22እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ጭካኔ ተመልከት፤ ጭካኔውም በወደቁት ላይ ነው፤ ቸርነቱ ግን በቸርነቱ ውስጥ እስካለህ ድረስ ለአንተ ነው፤ አለዚያ ግን አንተም ትቈረጣለህ። 23እነርሱም ባለማመናቸው ጸንተው ባይኖሩ፣ ተመልሰው ይገባሉ፤ እግዚአብሔር መልሶ ሊያስገባቸው ይችላልና። 24የበረሓ ከሆነው የወይራ ዛፍ የተቈረጥህና ተፈጥሮህ ወዳልሆነው ወደ መልካሙ ወይራ የገባህ ከሆንህ፣ በተፈጥሯቸው ቅርንጫፎቹ የሆኑት እነዚህ ወደ ራሳቸው ወይራ ዛፍ መግባታቸውማ ምን ያህል ይሆን?

እስራኤል ሁሉ ይድናል

25ወንድሞች ሆይ፤ ልባሞች የሆናችሁ እንዳይመስላችሁ፣ ይህን ምስጢር ሳታውቁ እንድትቀሩ አልፈልግም፤ የአሕዛብ ሙላት እስኪገባ ድረስ እስራኤል በከፊል በድንዳኔ ውስጥ ዐልፋለች። 26ስለዚህ እስራኤል ሁሉ ይድናሉ፤ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፤

“አዳኝ ከጽዮን ይወጣል፤

ከያዕቆብም ክፋትን ያስወግዳል።

27ኀጢአታቸውንም ሳስወግድ፣

ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳኔ ይህ ነው።”11፥27 ወይም ይህ ይሆናል

28እንደ ምሥራቹ ቃል ለእናንተ ሲባል ጠላቶች ናቸው፤ እንደ ምርጫ ከሆነ ግን፣ ለአባቶች ሲባል የተወደዱ ናቸው፤ 29የእግዚአብሔር ስጦታና ጥሪ ጸጸት የለበትም። 30እናንተም ቀድሞ ለእግዚአብሔር የማትታዘዙ እንደ ነበራችሁ፣ ከእነርሱ አለመታዘዝ የተነሣ አሁን ምሕረት እንዳገኛችሁ ሁሉ፣ 31እግዚአብሔር ለእናንተ ምሕረት ከማድረጉ የተነሣ፣ እነርሱም ምሕረት ያገኙ ዘንድ አሁን11፥31 አንዳድ ቅጆች አሁን የሚለው ቃል የላቸውም። የማይታዘዙ ልጆች ሆነዋል፤ 32እግዚአብሔር ለሁሉም ምሕረት ያደርግ ዘንድ ሰውን ሁሉ ባለመታዘዝ ዘግቶታልና።

ውዳሴ

33የእግዚአብሔር የጥበቡና የዕውቀቱ ባለጠግነት11፥33 ወይም ባለጠግነቱ፣ ጥበቡና ዕውቀቱ እንዴት ጥልቅ ነው!

ፍርዱ አይመረመርም፤

ለመንገዱም ፈለግ የለውም!

34“የጌታን ልብ ያወቀ ማነው?

አማካሪውስ የነበረ ማን ነው?”

35“እግዚአብሔር መልሶ እንዲሰጠው፣

ለእግዚአብሔር ያበደረ ከቶ ማን ነው?”

36ሁሉም ከእርሱ፣ በእርሱ፣ ለእርሱ ነውና፤

ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

羅馬書 11:1-36

上帝不放棄以色列人

1這樣,難道上帝放棄了祂的子民嗎?當然沒有!因我自己也是以色列人,是亞伯拉罕的後裔,屬於便雅憫支派。 2上帝並沒有放棄祂預先揀選的子民。你們不知道聖經上有關以利亞先知的記載嗎?他在上帝面前控告以色列人,說: 3「主啊!他們殘殺你的先知,拆毀你的祭壇,只剩下我一個人,他們還要殺我。」 4上帝怎樣回答呢?祂說:「我為自己留下七千人,他們未曾跪拜巴力。」

5現在的情況也是一樣,上帝按照揀選的恩典留下了少數人。 6既然說是出於恩典,就不再基於行為,不然恩典就不再是恩典了。 7這該怎麼說呢?以色列人努力追求,卻一無所得,只有蒙揀選的人得到了,其他的人都變得頑固不化。 8正如聖經上說:

「上帝使他們至今心智昏迷,

眼睛看不見,耳朵聽不到。」

9大衛也說:

「願他們的宴席成為網羅、

陷阱、絆腳石,

給他們帶來報應;

10願他們眼目昏暗,

無法看見,

永遠彎腰駝背。」

11那麼,以色列人一失足就再也爬不起來了嗎?當然不是!恰好相反,因他們的過犯,救恩臨到了外族人,使他們心生嫉妒。 12如果他們的過犯給世界帶來了富足,他們的失敗給外族人帶來了富足,那麼,他們發憤回頭的時候豈不要帶來更大的祝福嗎?

外族人得救

13我有話要對你們外族人說,因為我是外族人的使徒,我尊重自己的職分, 14希望使我的骨肉同胞心生嫉妒,好使他們當中的一些人得救。 15如果他們被拋棄,人類便有機會與上帝和好,那麼,當他們被接納的時候,又將怎樣呢?豈不是要死而復生嗎? 16獻祭時所獻的那部分麵團如果聖潔,整團麵也聖潔;樹根如果聖潔,樹枝也聖潔。

17如果橄欖樹上有幾條枝子被折了下來,你這野橄欖枝被接了上去,得以汲取橄欖樹根供應的汁漿,你就不可向折下來的枝子誇口。 18你怎能誇口呢?要知道:不是你托住樹根,而是樹根托住你。 19你也許會說:「原來的枝子被折下來,是為了把我接上去。」 20不錯,他們因為不信被折了下來,而你因為信被接了上去,然而不要自高,要敬畏上帝。 21上帝既然沒有留下原來的枝子,也可以不留下你。 22可見,上帝既慈愛又嚴厲。祂對墮落的人是嚴厲的,對你卻是慈愛的。你要常常活在祂的愛中,不然你也會被砍下來。 23當然,如果以色列人不再頑固不信,必會重新被接上去,因為上帝能把他們重新接上。 24你這從野生的橄欖樹上砍下來的枝子,尚且可以違反自然,被接到好橄欖樹上,何況原來的枝子被接回到原來的樹上呢?

全以色列都要得救

25弟兄姊妹,我不願意你們對以下這奧祕一無所知,還自以為聰明。這奧祕就是:雖然有些以色列人的心剛硬,但等到外族人得救的數目滿了以後, 26以色列都要得救。正如聖經上說:「救主必從錫安出來,祂將除去雅各子孫的罪惡。 27那時我要除去他們的罪,這是我與他們所立的約。」

28就福音而論,他們成為上帝的仇敵是為了使你們得到福音;就上帝的揀選而論,因為他們祖先的緣故,他們仍是上帝所愛的。 29因為上帝絕不會收回祂的恩賜和呼召。 30你們從前不順服上帝,然而因為他們的不順服,你們現在反蒙了憐憫。 31同樣,他們現在不順服是為了使你們蒙憐憫,好使他們也蒙憐憫。 32因為上帝把世人都歸在不順服之列,是為了要憐憫世人。

頌讚上帝

33啊,上帝的智慧和知識多麼博大精深!

祂的判斷多麼難測!

祂的蹤跡多麼難尋!

34誰曾知道主的心意?

誰曾做過祂的謀士?

35誰曾給過祂,

等祂償還呢?

36因為萬物都源於祂,

倚靠祂,歸於祂。

願榮耀歸給祂,

直到永遠。阿們!