ራእይ 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ራእይ 9:1-21

1አምስተኛው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ ከሰማይ ወደ ምድር የወደቀውንም ኮከብ አየሁ፤ ኮከቡም የጥልቁ ጕድጓድ መክፈቻ ተሰጠው። 2ጥልቁን ጕድጓድ በከፈተውም ጊዜ፣ ከውስጡ ከታላቅ እቶን እንደሚወጣ ያለ ጢስ ወጣ። ከጕድጓዱም በወጣው ጢስ ፀሓይና ሰማይ ጨለሙ። 3ከጢሱም አንበጦች ወጥተው በምድር ላይ ወረዱ፤ እንደ ምድር ጊንጦች ሥልጣን ያለ ሥልጣን ተሰጣቸው። 4እነርሱም የምድርን ሣር ወይም ማናቸውንም የለመለመ ተክል ወይም ዛፍ እንዳይጐዱ፣ ነገር ግን የእግዚአብሔር ማኅተም በግምባራቸው ላይ የሌለባቸውን ሰዎች ብቻ እንዲጐዱ ተነገራቸው። 5እነርሱንም አምስት ወር ብቻ እንዲያሠቃዩአቸው እንጂ እንዲገድሏቸው ሥልጣን አልተሰጣቸውም፤ የሚሠቃዩትም ሥቃይ ጊንጥ ሰውን ሲነድፍ እንደሚሰማው ዐይነት ሥቃይ ነው። 6በእነዚያ ቀኖች ሰዎች ሞትን ይፈልጋሉ፤ ነገር ግን አያገኙትም፤ ለመሞትም ይመኛሉ፤ ነገር ግን ሞት ከእነርሱ ይሸሻል።

7አንበጦቹ ለጦርነት የተዘጋጁ ፈረሶች ይመስሉ ነበር፤ በራሳቸውም ላይ የወርቅ አክሊል የመሰለ ነገር ደፍተዋል፤ ፊታቸውም የሰው ፊት ይመስል ነበር፤ 8ጠጕራቸው የሴት ጠጕር፣ ጥርሳቸውም የአንበሳ ጥርስ ይመስል ነበር። 9የብረት ጥሩር የሚመስል ጥሩር ነበራቸው፤ የክንፎቻቸውም ድምፅ ወደ ጦርነት የሚገሠግሡ የብዙ ፈረሶችና ሠረገሎች ድምፅ ይመስል ነበር። 10እንደ ጊንጥም ያለ፣ ጅራትና መንደፊያ ነበራቸው፤ ደግሞም ሰዎችን አምስት ወር የሚያሠቃዩበት ኀይል በጅራታቸው ላይ ነበር። 11በላያቸው ንጉሥ ነበራቸው፤ እርሱም የጥልቁ ጕድጓድ መልአክ ነው፤ ስሙም በዕብራይስጥ “አብዶን”፣ በግሪክ ደግሞ “አጶልዮን”9፥11 አብዶን ወይም አጶልዮን ትርጕሙ አጥፊ ማለት ነው። ይባላል።

12የመጀመሪያው ወዮ ዐልፏል፤ እነሆ፤ ከዚህ በኋላ ገና ሌላ ሁለት ወዮዎች ይመጣሉ።

13ስድስተኛው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ በእግዚአብሔር ፊት ካለው በወርቅ ከተሠራው መሠዊያ ቀንዶች ድምፅ ሲመጣ9፥13 ሲወጣ ማለት ነው። ሰማሁ፤ 14ድምፁም መለከት የያዘውን ስድስተኛውን መልአክ፣ “በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ የታሰሩትን አራቱን መላእክት ፍታቸው” አለው። 15ከሰው ዘር አንድ ሦስተኛውን እንዲገድሉ፣ ለዚህች ሰዓትና ዕለት እንዲሁም ለዚህች ወርና ዓመት ተዘጋጅተው የነበሩት አራቱ መላእክት ተፈቱ። 16የፈረሰኛው ሰራዊት ብዛት ሁለት መቶ ሚሊዮን ነበር፤ ቍጥራቸውንም ሰማሁ።

17በራእዬ ያየኋቸው ፈረሶችና በላያቸውም የተቀመጡት ይህን ይመስሉ ነበር፤ ጥሩራቸው እንደ እሳት ቀይ፣ እንደ ያክንት ሰማያዊና እንደ ዲን ብጫ ነበር፤ የፈረሶቹ ራስ የአንበሶችን ራስ ይመስል ነበር። ከአፋቸውም እሳትና ጢስ፣ ዲንም ይወጣ ነበር። 18ከአፋቸው በወጡት፣ በሦስቱ መቅሠፍቶች፣ ማለት በእሳቱ፣ በጢሱና በዲኑ አንድ ሦስተኛው የሰው ዘር ተገደለ። 19የፈረሶቹ ኀይል በአፋቸውና በጅራታቸው ላይ ነበር፤ ጅራታቸውም እባብ ይመስል ነበር፤ ራስ ስላላቸው ጕዳት የሚያደርሱት በእርሱ ነበር።

20በእነዚህ መቅሠፍቶች ሳይገደሉ የቀሩት ሰዎች አሁንም ከእጃቸው ሥራ ንስሓ አልገቡም፤ አጋንንትን እንዲሁም ማየት ወይም መስማት ወይም መሄድ የማይችሉትን፣ ከወርቅ፣ ከብር፣ ከናስ፣ ከድንጋይና ከዕንጨት የተሠሩትን ጣዖቶች ማምለክ አልተዉም፤ 21ደግሞም ከነፍስ ግድያቸው፣ ከጥንቈላ ሥራቸው፣ ከዝሙት ርኩሰታቸው ወይም ከስርቆት ተግባራቸው ንስሓ አልገቡም።

Thai New Contemporary Bible

วิวรณ์ 9:1-21

1ทูตสวรรค์องค์ที่ห้าเป่าแตรและข้าพเจ้าเห็นดาวดวงหนึ่งตกจากฟ้าลงมาบนโลก ดาวนั้นได้รับกุญแจไขนรกขุมลึก 2ซึ่งเมื่อเปิดออกควันก็พุ่งออกมาดั่งควันจากเตาหลอมมหึมาบดบังดวงอาทิตย์และท้องฟ้าให้มืดไป 3มีฝูงตั๊กแตนออกจากควันนั้นบินลงมายังโลก พระเจ้าประทานพิษร้ายให้แก่พวกมันเช่นเดียวกับพิษแมงป่องในโลก 4พวกมันถูกสั่งห้ามไม่ให้ทำลายหญ้า ต้นไม้ พืชพันธุ์ในโลก แต่ให้ทำร้ายเฉพาะผู้คนที่ไม่มีตราประทับของพระเจ้าบนหน้าผาก 5พระองค์ไม่ได้ให้อำนาจที่จะฆ่าคนเหล่านั้น เพียงแต่ให้ทรมานพวกเขาเป็นเวลาห้าเดือน เป็นความเจ็บปวดทรมานเหมือนถูกแมงป่องต่อย 6ตลอดช่วงนั้นพวกเขาจะร้องหาความตายแต่จะไม่พบ อยากตายแต่ความตายจะหลบลี้หนีหน้าไปจากเขา

7ตั๊กแตนนั้นดูคล้ายม้าศึกจะออกรบ ที่หัวมีสิ่งหนึ่งเหมือนมงกุฎทองคำ ใบหน้าคล้ายหน้ามนุษย์ 8ผมเหมือนผมผู้หญิง ฟันราวกับฟันสิงโต 9แผงกำบังอกคล้ายเกราะเหล็ก เสียงปีกขยับเหมือนเสียงกึกก้องของฝูงม้าศึกและเสียงรถม้าศึกทะยานสู่สงคราม 10พวกมันมีหางและเหล็กในเหมือนแมงป่อง หางของมันมีพิษสงทรมานมนุษย์เป็นเวลาห้าเดือน 11เจ้าเหนือหัวของพวกมันคือทูตแห่งนรกขุมลึกซึ่งมีชื่อในภาษาฮีบรูว่าอาบัดโดน และมีชื่อในภาษากรีกว่า อปอลลิโยน9:11อาบัดโดนและอปอลลิโยนแปลว่าผู้ทำลาย

12วิบัติที่หนึ่งผ่านไปแล้ว ยังมีอีกสองวิบัติที่จะมาถึง

13ทูตสวรรค์องค์ที่หกเป่าแตร และข้าพเจ้าได้ยินเสียงดังมาจากเชิงงอนของแท่นบูชาทองคำซึ่งตั้งอยู่ต่อหน้าพระเจ้า 14เสียงนั้นสั่งทูตองค์ที่หกซึ่งถือแตรอยู่ว่า “จงแก้มัดทูตสวรรค์ทั้งสี่ที่ถูกมัดไว้ที่แม่น้ำใหญ่ชื่อยูเฟรติส” 15และทูตสวรรค์ทั้งสี่ซึ่งพระเจ้าได้เตรียมไว้พร้อมแล้วสำหรับชั่วโมง วัน เดือน และปีนี้ ก็ถูกปล่อยให้ไปฆ่ามนุษย์เสียหนึ่งในสาม 16ข้าพเจ้าได้ยินว่าจำนวนพลทหารม้ามีสองร้อยล้าน

17ม้าและผู้ขี่ที่ข้าพเจ้าเห็นในนิมิตนั้นมีลักษณะดังนี้คือ ผู้ขี่นั้นสวมเกราะกำบังอกสีแดงเพลิง สีน้ำเงินเข้ม และสีเหลืองกำมะถัน หัวของม้าคล้ายหัวสิงโต มีไฟ ควัน และกำมะถันพุ่งออกมาจากปากของพวกมัน 18หนึ่งในสามของมนุษย์ถูกฆ่าด้วยภัยพิบัติสามอย่างคือ ไฟ ควัน และกำมะถันที่พุ่งออกมาจากปากม้า 19พิษสงของม้าอยู่ที่ปากและหางเพราะหางของมันเหมือนงูและมีหัวหลายหัวซึ่งมันใช้ทำร้ายคน 20มนุษย์ทั้งหลายที่ไม่ถูกฆ่าด้วยภัยพิบัตินี้ยังไม่ยอมสำนึกกลับใจจากการกระทำของตน ไม่เลิกกราบไหว้ภูติผีและรูปเคารพที่ทำด้วยทองคำ เงิน ทองสัมฤทธิ์ หิน และไม้ รูปเคารพซึ่งไม่สามารถเห็น ได้ยิน หรือเดิน 21ทั้งพวกเขาไม่ได้สำนึกผิด กลับใจจากการฆ่าฟันกัน การใช้ไสยศาสตร์ เวทมนตร์ การผิดศีลธรรมทางเพศ และการลักขโมยที่ทำอยู่