ራእይ 8 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ራእይ 8:1-13

ሰባተኛው ማኅተምና የወርቁ ጥና

1በጉ ሰባተኛውን ማኅተም በፈታ ጊዜ፣ ግማሽ ሰዓት ያህል በሰማይ ዝምታ ሆነ።

2ከዚያም በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፤ ሰባት መለከትም ተሰጣቸው።

3ሌላም መልአክ የወርቅ ጥና ይዞ መጣና በመሠዊያው አጠገብ ቆመ፤ እርሱም በዙፋኑ ፊት ባለው የወርቅ መሠዊያ ላይ ከቅዱሳን ጸሎት ሁሉ ጋር እንዲያቀርበው ብዙ ዕጣን ተሰጠው። 4የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳኑ ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ወጣ። 5መልአኩም ጥናውን ይዞ የመሠዊያውን እሳት ሞላበትና ወደ ምድር ወረወረው፤ ነጐድጓድ፣ ድምፅ፣ መብረቅና የምድር መናወጥ ሆነ።

ሰባቱ መለከቶች

6ከዚያም ሰባቱን መለከት የያዙት ሰባቱ መላእክት ለመንፋት ተዘጋጁ።

7የመጀመሪያው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ ደም የተቀላቀለበት በረዶና እሳት ወደ ምድር ተጣለ፤ የምድር አንድ ሦስተኛ ተቃጠለ፤ የዛፎችም አንድ ሦስተኛ ተቃጠለ፤ የለመለመውም ሣር ሁሉ ተቃጠለ።

8ሁለተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ ትልቅ ተራራ የሚመስል ነገር በእሳት እየተቀጣጠለ ወደ ባሕር ተጣለ፤ የባሕሩ አንድ ሦስተኛ ወደ ደም ተለወጠ፤ 9በባሕሩም ውስጥ ከሚኖሩት ሕያዋን ፍጡራን አንድ ሦስተኛ ሞተ፤ የመርከቦችም አንድ ሦስተኛ ወደመ።

10ሦስተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ እንደ ችቦ የሚነድድ ታላቅ ኮከብ በወንዞች አንድ ሦስተኛና በውሃ ምንጮች ላይ ከሰማይ ወደቀ፤ 11የኮከቡም ስም “እሬቶ8፥11 ምሬት ማለት ነው።” ይባል ነበር። የውሃውም አንድ ሦስተኛ መራራ ሆነ፤ ውሃው መራራ ከመሆኑ የተነሣም ብዙ ሰዎች ሞቱ።

12አራተኛው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ የብርሃናቸው አንድ ሦስተኛ ይጨልም ዘንድ፣ የፀሓይ አንድ ሦስተኛ፣ የጨረቃም አንድ ሦስተኛ፣ የከዋክብትም አንድ ሦስተኛ ተመታ፤ የቀንም አንድ ሦስተኛ፣ የሌሊቱም አንድ ሦስተኛ ብርሃን እንዳይሰጥ ተከለከለ።

13ከዚያም ተመለከትሁ፤ አንድ ንስር በሰማይ መካከል ይበርር ነበር፤ በታላቅ ድምፅም፣ “የቀሩት ሦስቱ መላእክት መለከት ስለሚነፉ፣ በምድር ላይ ለሚኖሩት ወዮላቸው! ወዮላቸው! ወዮላቸው!” ሲል ሰማሁ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

启示录 8:1-13

揭开第七印

1羔羊揭开第七印时,天上寂静无声,约半小时。 2然后,我看见站在上帝面前的七位天使领受了七支号角。

3另一位天使手里拿着金香炉上前来,站在祭坛旁边。他接过了许多香,把香和众圣徒的祈祷一起献在宝座前的金坛上。 4这香发出的烟,连同众圣徒的祷告从那天使的手中向上升,直达上帝面前。 5天使又拿着香炉,盛满祭坛的火,将它倒在地上,于是有雷鸣、巨响、闪电和地震。

天使吹号

6这时,那七位拿着号角的天使也预备要吹号。

7第一位天使吹响号角的时候,冰雹和火搀杂着血从天上倾盆而下。地的三分之一、树木的三分之一和一切的青草都被烧毁了。

8第二位天使吹号的时候,一座好像燃烧的大山被丢进海里。海洋的三分之一变成了血, 9海中的活物死了三分之一,船只也被毁了三分之一。

10第三位天使吹号的时候,有一颗好像火炬般燃烧着的巨星从天上坠落在三分之一的江河溪流和水泉里。 11这颗星名叫“苦艾”,它使三分之一的水都变苦了,许多人因为喝了这种苦水而死去。

12第四位天使吹号的时候,太阳、月亮和星辰的三分之一都受到重击,以致失去了光辉,于是日间的三分之一暗淡无光,夜间也是如此。 13我又看见有一只鹰在半空中飞翔,听见它大声宣告:“有祸了!有祸了!世上的居民有祸了!还有三位天使要吹响号角。”