ራእይ 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ራእይ 3:1-22

በሰርዴስ ላለው ቤተ ክርስቲያን

1“በሰርዴስ ላለው ቤተ ክርስቲያን መልአክ3፥1 ወይም መልእክተኛ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤

ሰባቱን የእግዚአብሔር መናፍስትና3፥1 ወይም ሰባት ዕጥፍ መንፈስ ሰባቱን ከዋክብት በእጁ የያዘው እንዲህ ይላል፤

ሥራህን ዐውቃለሁ፤ በስም ሕያው ነህ፤ ነገር ግን ሞተሃል። 2ስለዚህ ንቃ፤ ሊሞት የተቃረበውን የቀረውን ነገር አጽና፤ ሥራህ በአምላኬ ፊት ፍጹም ሆኖ አላገኘሁትም። 3እንግዲህ የተቀበልኸውንና የሰማኸውን አስታውስ፤ ታዘዘውም፤ ንስሓም ግባ። ባትነቃ ግን እንደ ሌባ እመጣብሃለሁ፤ በየትኛው ሰዓት እንደምመጣብህም አታውቅም።

4ነገር ግን ልብሳቸውን ያላሳደፉ ጥቂት ሰዎች በሰርዴስ ከአንተ ጋር አሉ፤ እነርሱም ነጭ ልብስ ለብሰው ከእኔ ጋር ይሄዳሉ፤ ይህ የሚገባቸው ነውና። 5ድል የሚነሣም እንደ እነርሱ ነጭ ልብስ ይለብሳል፤ እኔም በአባቴና በመላእክቱ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ ስሙንም ከሕይወት መጽሐፍ አልደመስስም። 6መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን ጆሮ ያለው ይስማ።

በፊላድልፍያ ላለው ቤተ ክርስቲያን

7“በፊላድልፍያ ላለው ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤

ቅዱስና እውነተኛ የሆነው፣ የዳዊትንም መክፈቻ በእጁ የያዘው እንዲህ ይላል፤ እርሱ የከፈተውን ማንም ሊዘጋው አይችልም፤ የዘጋውንም ማንም ሊከፍተው አይችልም፤

8ሥራህን ዐውቃለሁ። እነሆ፤ ማንም ሊዘጋው የማይችል የተከፈተ በር በፊትህ አድርጌአለሁ። ኀይልህ ትንሽ እንደ ሆነ ዐውቃለሁ፤ ሆኖም ቃሌን ጠብቀሃል፤ ስሜንም አልካድህም። 9እነሆ፣ አይሁድ ሳይሆኑ አይሁድ ነን የሚሉት፣ የሚዋሹት፣ ከሰይጣን ማኅበር የሆኑት ወደ አንተ እንዲመጡ በእግርህ ሥር እንዲሰግዱ፣ እኔ እንደ ወደድሁህም እንዲያውቁ አደርጋለሁ። 10በትዕግሥት እንድትጸና የሰጠሁህን ትእዛዜን ስለ ጠበቅህ፣ እኔ ደግሞ በምድር ላይ የሚኖሩትን ሊፈትናቸው በዓለም ሁሉ ላይ ከሚመጣው የፈተና ሰዓት እጠብቅሃለሁ።

11ቶሎ እመጣለሁ፤ ማንም አክሊልህን እንዳይወስድብህ ያለህን አጥብቀህ ያዝ። 12ድል የሚነሣውን በአምላኬ ቤተ መቅደስ ውስጥ ዐምድ አደርገዋለሁ፤ ከዚያም ከቶ አይወጣም። የአምላኬን ስምና የአምላኬን ከተማ ስም ይኸውም ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን የአዲሲቱን ኢየሩሳሌም ስም በእርሱ ላይ እጽፋለሁ፤ አዲሱን ስሜንም በእርሱ ላይ እጽፋለሁ። 13መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን ጆሮ ያለው ይስማ።

በሎዶቅያ ላለው ቤተ ክርስቲያን

14“በሎዶቅያ ላለው ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤

አሜን የሆነው፣ ደግሞም ታማኝና እውነተኛ ምስክር የሆነው፣ የእግዚአብሔርም ፍጥረት ምንጭ3፥14 ገዥ ወይም ጀማሪ የሆነው እንዲህ ይላል፤

15ቀዝቃዛ ወይም ትኵስ እንዳልሆንህ ሥራህን ዐውቃለሁ፤ ቀዝቃዛ ወይም ትኵስ ብትሆን በወደድሁ ነበር። 16እንግዲህ ለብ ያልህ ብቻ እንጂ ትኵስ ወይም ቀዝቃዛ ስላልሆንህ ከአፌ አውጥቼ ልተፋህ ነው። 17‘ሀብታም ነኝ፣ ባለጠጋ ነኝ፣ አንዳችም አያስፈልገኝም’ ትላለህ፤ ነገር ግን ጐስቋላ፣ ምስኪን፣ ድኻ፣ ዕውርና የተራቈትህ መሆንህን አታውቅም። 18ስለዚህ ሀብታም እንድትሆን፣ በእሳት የነጠረ ወርቅ እንድትገዛ፣ የዕራቍትነትህ ኀፍረት እንዳይታይ፣ ነጭ ልብስ እንድትለብስና ለማየት እንድትችል ዐይንህን በኵል እንድትኳል እመክርሃለሁ።

19እኔ የምወድዳቸውን እገሥጻለሁ፤ እቀጣለሁም። ስለዚህ ትጋ፤ ንስሓም ግባ። 20እነሆ፤ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ፤ ማንም ድምፄን ሰምቶ በሩን ቢከፍትልኝ ወደ እርሱ ገብቼ ከእርሱ ጋር እበላለሁ፤ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል።

21እኔ ድል ነሥቼ ከአባቴ ጋር በእርሱ ዙፋን ላይ እንደ ተቀመጥሁ፣ ድል የሚነሣውንም ከእኔ ጋር በዙፋኔ ላይ እንዲቀመጥ አደርገዋለሁ። 22መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን ጆሮ ያለው ይስማ።”

Thai New Contemporary Bible

วิวรณ์ 3:1-22

ถึงคริสตจักรที่เมืองซาร์ดิส

1“จงเขียนถึงทูตสวรรค์3:1 หรือผู้ส่งข่าวเช่นเดียวกับข้อ 7 และ 14แห่งคริสตจักรที่เมืองซาร์ดิสว่า

พระองค์ผู้ทรงครองวิญญาณทั้งเจ็ด3:1 หรือพระวิญญาณทั้งเจ็ดของพระเจ้าและดาวทั้งเจ็ดนั้นตรัสว่า เรารู้ถึงการกระทำของเจ้า เจ้าได้รับการยกย่องว่ามีชีวิตอยู่แต่เจ้าตายแล้ว 2จงตื่นขึ้น! เสริมกำลังส่วนที่เหลืออยู่และจวนจะตายนั้น เพราะเราพบว่าการกระทำของเจ้าไม่สมบูรณ์พร้อมในสายพระเนตรพระเจ้าของเรา 3เพราะฉะนั้นจงระลึกถึงสิ่งที่เจ้าได้รับไว้และได้ฟังมา จงทำตามสิ่งนั้นและกลับใจใหม่ แต่ถ้าเจ้าไม่ตื่นขึ้นเราจะมาอย่างขโมย และเจ้าไม่รู้ว่าเราจะมาหาเจ้าเวลาใด

4แต่ก็มีพวกเจ้าสองสามคนในซาร์ดิสที่ไม่ได้ทำให้เสื้อผ้าของตนแปดเปื้อน พวกเขาจะสวมชุดสีขาวเดินไปกับเราเพราะพวกเขาสมควรแล้วที่จะได้ทำเช่นนั้น 5ผู้ใดมีชัยชนะจะได้สวมชุดสีขาวเช่นเดียวกับพวกเขา เราจะไม่ลบชื่อผู้นั้นจากหนังสือแห่งชีวิตเลย แต่จะรับรองชื่อผู้นั้นต่อหน้าพระบิดาของเราและต่อหน้าเหล่าทูตสวรรค์ของพระองค์ 6ใครมีหูก็จงฟังสิ่งที่พระวิญญาณตรัสแก่คริสตจักรทั้งหลาย

ถึงคริสตจักรที่เมืองฟีลาเดลเฟีย

7“จงเขียนถึงทูตสวรรค์แห่งคริสตจักรที่เมืองฟีลาเดลเฟียว่า

พระองค์ผู้ทรงบริสุทธิ์และสัตย์จริง ผู้ทรงถือกุญแจของดาวิด สิ่งที่พระองค์ทรงเปิดแล้วไม่มีใครปิดได้และสิ่งที่พระองค์ทรงปิดแล้วไม่มีใครเปิดได้ พระองค์ตรัสว่า 8เรารู้ถึงการกระทำของเจ้า ดูเถิดเราได้เปิดประตูไว้ต่อหน้าเจ้าซึ่งไม่มีใครปิดได้ เรารู้ว่าเจ้ามีกำลังน้อย กระนั้นเจ้าก็ได้ประพฤติตามคำของเราและไม่ได้ปฏิเสธนามของเรา 9เราจะทำให้บรรดาผู้เป็นธรรมศาลาของซาตาน ผู้อ้างตัวเป็นยิวทั้งๆ ที่ไม่ได้เป็น แต่เป็นคนโกหก เราจะทำให้พวกเขามาล้มลงแทบเท้าของเจ้าและรับรู้ว่าเรารักพวกเจ้า 10เพราะพวกเจ้าได้อดทนอย่างยิ่งตามที่เราได้สั่งไว้ เราก็จะปกป้องเจ้าให้พ้นจากวาระแห่งการทดลองที่กำลังมาเหนือโลกทั้งโลกเพื่อทดสอบบรรดาผู้ที่อาศัยอยู่ในโลก

11เราจะมาในไม่ช้า จงยึดมั่นในสิ่งที่เจ้ามีอยู่เพื่อว่าจะไม่มีใครชิงมงกุฎของเจ้าไปได้ 12ผู้ใดมีชัยชนะเราจะตั้งผู้นั้นให้เป็นเสาหนึ่งในพระวิหารของพระเจ้าของเรา ผู้นั้นจะไม่จากพระวิหารไปอีกเลย บนตัวผู้นั้นเราจะจารึกพระนามพระเจ้าของเราและชื่อนครของพระเจ้าของเราคือ เยรูซาเล็มใหม่ซึ่งพระเจ้าของเรากำลังทรงส่งลงมาจากสวรรค์ และเราจะจารึกชื่อใหม่ของเราไว้บนตัวผู้นั้นด้วย 13ใครมีหูก็จงฟังสิ่งที่พระวิญญาณตรัสแก่คริสตจักรทั้งหลาย

ถึงคริสตจักรที่เมืองเลาดีเซีย

14“จงเขียนถึงทูตสวรรค์แห่งคริสตจักรที่เมืองเลาดีเซียว่า

พระองค์ผู้ทรงเป็นพระอาเมน3:14 เป็นพระนามหนึ่งของพระเจ้า ในที่นี้หมายถึงพระเยซูคริสต์ผู้ทรงค้ำประกันพระสัญญาและแผนการทั้งสิ้นของพระเจ้า เป็นพยานที่สัตย์ซื่อและเที่ยงแท้ เป็นผู้ปกครองเหนือสรรพสิ่งที่พระเจ้าทรงสร้างตรัสว่า 15เรารู้ถึงการกระทำของเจ้า เจ้าไม่ร้อนไม่เย็น เราอยากให้เจ้าร้อนหรือเย็นไปอย่างใดอย่างหนึ่ง! 16เพราะเจ้าอุ่นๆ ไม่ร้อนไม่เย็น ดังนั้นเรากำลังจะถ่มเจ้าออกจากปาก 17เจ้ากล่าวว่า ‘ข้าร่ำรวย ได้ทรัพย์สมบัติมากมาย และไม่ขัดสนสิ่งใดเลย’ แต่เจ้าไม่รู้ว่าตนเองเป็นคนน่าสังเวชน่าสงสาร ยากไร้ ตาบอด และเปลือยกายอยู่ 18เราแนะนำเจ้าให้ซื้อทองคำที่หลอมให้บริสุทธิ์แล้วด้วยไฟจากเราเพื่อเจ้าจะได้มั่งคั่ง ซื้อเสื้อผ้าสีขาวมาสวมใส่เพื่อปกปิดความเปลือยเปล่าอันน่าละอาย และซื้อยามาทาตาของเจ้าเพื่อเจ้าจะได้มองเห็น

19เราว่ากล่าวและตีสอนผู้ที่เรารัก ดังนั้นจงกระตือรือร้นและกลับใจใหม่ 20เราอยู่ที่นี่แล้ว! เรายืนเคาะอยู่ที่ประตู ถ้าผู้ใดได้ยินเสียงของเราและเปิดประตู เราจะเข้าไปรับประทานอาหารกับผู้นั้นและเขาจะรับประทานร่วมกับเรา

21ผู้ใดมีชัยชนะเราจะให้เขามีสิทธิ์นั่งกับเราบนบัลลังก์ของเรา เหมือนที่เราได้มีชัยชนะและได้นั่งกับพระบิดาของเราบนบัลลังก์ของพระองค์ 22ใครมีหูก็จงฟังสิ่งที่พระวิญญาณตรัสแก่คริสตจักรทั้งหลาย”