ራእይ 19 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ራእይ 19:1-21

ሃሌ ሉያ

1ከዚህ በኋላ የብዙ ሰዎችን ድምፅ የሚመስል ታላቅ ድምፅ በሰማይ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“ሃሌ ሉያ!

ማዳን፣ ክብርና ኀይል የአምላካችን ነው፤

2ፍርዱ እውነትና ጽድቅ ነውና፤

በዝሙቷ ምድርን ያረከሰችውን፣

ታላቂቱን አመንዝራ ፈርዶባታል፤

ስለ አገልጋዮቹም ደም ተበቅሏታል።”

3ደግሞም እንዲህ አሉ፤

“ሃሌ ሉያ!

ጢስ ከእርሷ ከዘላለም እስከ ዘላለም ይወጣል።”

4ሃያ አራቱ ሽማግሌዎችና አራቱ ሕያዋን ፍጡራን በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው አምላክ ወድቀው ሰገዱ፤ እንዲህም አሉ፤

“አሜን፣ ሃሌ ሉያ!”

5ከዚህ በኋላ እንዲህ የሚል ድምፅ ከዙፋኑ ወጣ፤

“እናንተ አገልጋዮቹ ሁሉ፣

እርሱን የምትፈሩ፣

ታናናሾችና ታላላቆችም፣

አምላካችንን አመስግኑ!”

6ደግሞም እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ፣ እንደ ኀይለኛ ወራጅ ውሃ ድምፅ፣ እንደ ብርቱም ነጐድጓድ ድምፅ የሚመስል እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“ሃሌ ሉያ!

ሁሉን ቻይ ጌታ አምላካችን ነግሧልና።

7የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ፣

የእርሱም ሙሽራ ራሷን ስላዘጋጀች

ደስ ይበለን፤ ሐሤት እናድርግ፤

ክብርም እንስጠው።

8የሚያንጸባርቅና ንጹሕ፣

ከተልባ እግር የተሠራ ቀጭን ልብስ እንድትለብስ ተሰጣት።”

ከተልባ እግር የተሠራው ቀጭን ልብስ የቅዱሳን የጽድቅ ሥራ ነው።

9መልአኩም፣ “ ‘ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው’ ብለህ ጻፍ” አለኝ፤ ቀጥሎም፣ “እነዚህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃሎች ናቸው” አለኝ።

10እኔም ልሰግድለት በእግሩ ሥር ተደፋሁ፤ እርሱ ግን፣ “ተው! ይህን አታድርግ! እኔም ከአንተና የኢየሱስን ምስክር ከያዙት ወንድሞችህ ጋር አገልጋይ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ፤ የኢየሱስ ምስክር የትንቢት መንፈስ ነውና” አለኝ።

በነጭ ፈረስ ላይ የተቀመጠው

11ከዚያም ሰማይም ተከፍቶ አየሁ፤ እነሆ አንድ ነጭ ፈረስ ነበረ፤ በፈረሱም ላይ፣ “ታማኝና እውነተኛ” የሚባል ተቀምጦ ነበር፤ እርሱም በጽድቅ ይፈርዳል፤ ይዋጋልም። 12ዐይኖቹ እንደ እሳት ነበልባል ናቸው፤ በራሱም ላይ ብዙ ዘውዶች አሉ። ከእርሱ በቀር ማንም የማያውቀው ስም በእርሱ ላይ ተጽፏል። 13እርሱ በደም የተነከረ ልብስ ለብሷል፤ ስሙም የእግዚአብሔር ቃል ነው። 14የሰማይም ሰራዊት ነጭ፣ ንጹሕና ከተልባ እግር የተሠራ ቀጭን ልብስ ለብሰው፣ በነጫጭ ፈረሶች ላይ ተቀምጠው ይከተሉት ነበር። 15ሕዝቦችን የሚመታበት ስለታም ሰይፍ ከአፉ ወጣ፤ “በብረት በትርም ይገዛቸዋል።” እርሱም ሁሉን ቻይ የሆነውን የእግዚአብሔርን የብርቱ ቍጣ ወይን መጭመቂያ ይረግጣል። 16በልብሱና በጭኑ ላይ እንዲህ የሚል ስም ተጽፏል፤

“የነገሥታት ንጉሥና የጌቶች ጌታ።”

17ቀጥሎም አንድ መልአክ በፀሓይ ውስጥ ቆሞ አየሁ፤ እርሱም በሰማይ መካከል ለሚበርሩ ወፎች ሁሉ እንዲህ ሲል በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ “ኑ፤ ወደ ታላቁ የእግዚአብሔር እራት ተሰብሰቡ፤ 18የምትሰበሰቡትም የነገሥታትን ሥጋ፣ የጦር አዛዦችን ሥጋ፣ የብርቱ ሰዎችን ሥጋ፣ የፈረሶችንና የፈረሰኞችን ሥጋ እንዲሁም የሰዎችን ሁሉ፣ ይኸውም የጌቶችንና የባሮችን፣ የታናናሾችንና የታላላቆችን ሥጋ እንድትበሉ ነው።”

19ከዚህ በኋላ አውሬው፣ የምድር ነገሥታትና ሰራዊታቸው በፈረሱ ላይ ከተቀመጠውና ከሰራዊቱ ጋር ለመዋጋት ተሰብስበው አየሁ። 20ነገር ግን አውሬው ተያዘ፤ ከእርሱም ጋር በፊቱ ምልክቶችን ያደርግ የነበረው ሐሰተኛው ነቢይ ተያዘ። በእነዚህ ምልክቶች የአውሬውን ምልክት የተቀበሉትንና ለምስሉ የሰገዱትን አሳተ። ሁለቱም በሕይወት እንዳሉ በዲን ወደሚቃጠለው የእሳት ባሕር ተጣሉ። 21የቀሩት ደግሞ በፈረሱ ላይ ከተቀመጠው አፍ በሚወጣው ሰይፍ ተገደሉ፤ ወፎችም ሁሉ ከሥጋቸው በልተው ጠገቡ።

Thai New Contemporary Bible

วิวรณ์ 19:1-21

สรรเสริญพระเจ้า!

1จากนั้นข้าพเจ้าได้ยินเสียงกึกก้องราวกับเสียงผู้คนเป็นอันมากในสวรรค์ร้องตะโกนว่า

“ฮาเลลูยา!19:1 แปลว่าสรรเสริญพระเจ้าเช่นเดียวกับข้อ 3,4 และ 6

ความรอดมาจากพระเจ้าของเรา พระองค์ทรงพระเกียรติสิริและเดชานุภาพ

2เพราะบรรดาการพิพากษาของพระองค์เที่ยงธรรมและเที่ยงแท้

พระองค์ทรงตัดสินโทษหญิงโสเภณีตัวฉกาจนั้นแล้ว

ผู้ซึ่งทำให้โลกเสื่อมทรามด้วยการล่วงประเวณีของนาง

พระองค์ทรงให้นางชดใช้เลือดของผู้รับใช้ของพระองค์แล้ว”

3และพวกเขาร้องตะโกนอีกครั้งว่า

“ฮาเลลูยา!

ควันไฟจากนครนั้นพลุ่งขึ้นสืบๆ ไปเป็นนิตย์”

4ผู้อาวุโสทั้งยี่สิบสี่คนกับสิ่งมีชีวิตทั้งสี่หมอบกราบนมัสการพระเจ้าผู้ประทับบนพระที่นั่ง และร้องว่า

“อาเมน ฮาเลลูยา!”

5แล้วมีเสียงหนึ่งดังจากพระที่นั่งกล่าวว่า

“ท่านทั้งปวงที่เป็นผู้รับใช้ของพระองค์

ผู้ที่ยำเกรงพระองค์

ทั้งผู้ใหญ่และผู้น้อย

จงสรรเสริญพระเจ้าของเรา”

6จากนั้นข้าพเจ้าได้ยินเสียงคล้ายเสียงผู้คนมากมายเหมือนเสียงน้ำเชี่ยวกรากและเหมือนเสียงฟ้าร้องกึกก้องตะโกนว่า

“ฮาเลลูยา!

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าพระเจ้าผู้ทรงฤทธิ์

ของเราทรงครอบครองอยู่

7ให้เราทั้งหลายชื่นชมยินดีและเปรมปรีดิ์

และถวายพระเกียรติสิริแด่พระองค์!

เพราะถึงกำหนดอภิเษกสมรสของพระเมษโปดกแล้ว

และเจ้าสาวของพระองค์เตรียมตัวพร้อมแล้ว

8ทรงให้เจ้าสาวสวมชุดผ้าลินินเนื้อดี

ที่สะอาดสดใสแล้ว”

(ผ้าลินินเนื้อดีหมายถึงการประพฤติอันชอบธรรมของประชากรของพระเจ้า)

9แล้วทูตสวรรค์นั้นบอกข้าพเจ้าว่า “จงเขียนว่า ‘ความสุขมีแก่บรรดาผู้ที่ได้รับเชิญมายังงานเลี้ยงฉลองอภิเษกสมรสของพระเมษโปดก!’ ” และทูตนั้นกล่าวอีกว่า “สิ่งเหล่านี้เป็นพระวจนะแท้ของพระเจ้า”

10ถึงตรงนี้ข้าพเจ้าหมอบลงแทบเท้าทูตสวรรค์เพื่อนมัสการ แต่ทูตนั้นกล่าวแก่ข้าพเจ้าว่า “อย่าทำเช่นนั้น! เราเป็นเพื่อนผู้รับใช้ร่วมกับท่านและร่วมกับพี่น้องของท่านที่ยึดมั่นในคำพยานเรื่องพระเยซู จงนมัสการพระเจ้า! เพราะคำพยานเรื่องพระเยซูนั้นคือหัวใจของการเผยพระวจนะ”

ผู้ทรงม้าขาว

11ข้าพเจ้าเห็นฟ้าสวรรค์เปิดอยู่และมีม้าขาวตัวหนึ่งยืนอยู่ต่อหน้าข้าพเจ้า พระนามของพระองค์ผู้ทรงม้านั้นคือพระผู้สัตย์ซื่อและเที่ยงแท้ พระองค์ทรงพิพากษาและสู้ศึกด้วยความยุติธรรม 12พระเนตรของพระองค์ดุจไฟโชติช่วง บนพระเศียรมีมงกุฎหลายอัน ทรงมีพระนามจารึกไว้บนพระกาย ไม่มีผู้ใดรู้จักพระนามนั้นเลยนอกจากพระองค์เอง 13ทรงฉลองพระองค์ซึ่งได้จุ่มในเลือด และพระนามของพระองค์คือพระวาทะของพระเจ้า 14บรรดากองทัพสวรรค์สวมอาภรณ์ผ้าลินินเนื้อดีขาวสะอาดนั่งบนหลังม้าขาวกำลังตามเสด็จพระองค์ไป 15พระแสงคมกริบออกมาจากพระโอษฐ์ของพระองค์ ทรงใช้พระแสงนี้ฟาดฟันประชาชาติ “พระองค์จะทรงปกครองพวกเขาด้วยคทาเหล็ก”19:15 สดด.2:9 พระองค์ทรงเหยียบย่ำองุ่นในบ่อย่ำแห่งพระพิโรธเกรี้ยวกราดของพระเจ้าผู้ทรงฤทธิ์ 16ที่เสื้อคลุมและต้นขาจารึกพระนามของพระองค์ว่า

กษัตริย์เหนือกษัตริย์ทั้งหลาย เจ้านายเหนือเจ้านายทั้งหลาย

17แล้วข้าพเจ้าเห็นทูตสวรรค์องค์หนึ่งยืนอยู่ที่ดวงอาทิตย์ร้องเสียงดังประกาศแก่นกทั้งมวลซึ่งบินอยู่กลางอากาศว่า “จงมาร่วมชุมนุมกันในงานเลี้ยงใหญ่ของพระเจ้า 18เพื่อเจ้าจะได้กินเนื้อของกษัตริย์ เนื้อของขุนพลและนายทหาร เนื้อม้าและเนื้อคนขี่ม้า และเนื้อประชาชนทั้งปวง เนื้อของทาสและไท เนื้อของผู้ใหญ่และผู้น้อย”

19แล้วข้าพเจ้าเห็นสัตว์ร้ายนั้นกับบรรดากษัตริย์ของโลกพร้อมทั้งกองทัพของพวกเขามาชุมนุมกันเพื่อรบกับพระองค์ผู้ทรงม้าขาวและกองทัพของพระองค์ 20แต่สัตว์ร้ายนั้นถูกจับพร้อมด้วยผู้เผยพระวจนะเท็จซึ่งได้ทำหมายสำคัญแทนสัตว์ร้ายนั้น ด้วยหมายสำคัญเหล่านี้เขาได้ล่อลวงบรรดาผู้ที่ได้รับเครื่องหมายของสัตว์ร้ายนั้นและได้กราบนมัสการรูปจำลองของมัน ทั้งสัตว์ร้ายและผู้เผยพระวจนะเท็จถูกโยนลงในบึงไฟกำมะถันลุกโชนทั้งเป็น 21ส่วนพวกที่เหลือถูกฆ่าด้วยพระแสงดาบซึ่งออกมาจากพระโอษฐ์ของพระองค์ผู้ทรงม้าขาว แล้วนกทั้งปวงก็รุมทึ้งกินเนื้อคนเหล่านั้น