ራእይ 18 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ራእይ 18:1-24

የባቢሎን ውድቀት

1ከዚህ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ ከክብሩም ነጸብራቅ የተነሣ ምድር በራች፤ 2እርሱም በብርቱ ድምፅ እንዲህ ብሎ ጮኸ፤

“ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች! ወደቀች!

የአጋንንት መኖሪያ፣

የርኩሳን መናፍስት ሁሉ መጠጊያ፣

የርኩስና የአስጸያፊ ወፎች ሁሉ መጠለያ ሆነች።

3ሕዝቦች ሁሉ የዝሙቷን ቍጣ ወይን ጠጅ ጠጥተዋልና፤

የምድር ነገሥታት ከእርሷ ጋር አመንዝረዋል፤

የምድርም ነጋዴዎች ከብዙ ምቾቷ ኀይል

የተነሣ በልጽገዋል።”

4ከዚያም ከሰማይ ሌላ ድምፅ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“ሕዝቤ ሆይ፤ በኀጢአቷ እንዳትተባበሩ፤

ከመቅሠፍቷም እንዳትካፈሉ፤

ከእርሷ ውጡ፤

5ኀጢአቷ እስከ ሰማይ ድረስ ተከምሯልና፤

እግዚአብሔርም ዐመፃዋን አስታውሷል።

6በሰጠችው መጠን ብድራቷን መልሱላት፤

ለሠራችው ሁሉ ዕጥፍ ክፈሏት፤

በቀላቀለችውም ጽዋ ዕጥፍ አድርጋችሁ ቀላቅሉባት።

7ለራሷ ክብርና ምቾት የሰጠችውን ያህል፣

ሥቃይና ሐዘን ስጧት፤

በልቧም እንዲህ እያለች ትመካለች፤

‘እንደ ንግሥት ተቀምጬአለሁ፤

መበለትም አይደለሁም፤ ከቶም

አላዝንም፤’

8ስለዚህ መቅሠፍቶቿ በአንድ ቀን ይመጡባታል፤

ሞት፣ ሐዘንና ራብ ይሆኑባታል፤

የሚፈርድባት ጌታ እግዚአብሔር ብርቱ ስለሆነ፣

በእሳት ትቃጠላለች።

9“ከእርሷ ጋር ያመነዘሩና በምቾት የኖሩ የምድር ነገሥታት፣ እርሷ ስትቃጠል የሚወጣውን ጢስ ሲያዩ ስለ እርሷ ያለቅሳሉ፤ ያዝናሉም። 10ሥቃይዋንም በመፍራት በሩቅ ቆመው እንዲህ ይላሉ፤

“ ‘አንቺ ታላቂቱ ከተማ ወዮልሽ! ወዮልሽ!

አንቺ ባቢሎን ብርቱዪቱ ከተማ፣

ፍርድሽ በአንድ ሰዓት ውስጥ መጥቷል።’

11“ጭነታቸውን ከእንግዲህ የሚገዛ ስለሌለ፣ የምድር ነጋዴዎችም ስለ እርሷ ያለቅሳሉ፤ ያዝናሉ፤ 12ጭነቱም፦ ወርቅ፣ ብር፣ የከበረ ድንጋይ፣ ዕንቍ፣ ከተልባ እግር የተሠራ ቀጭን ልብስ፣ ሐምራዊ ልብስ፣ ሐር ልብስ፣ ቀይ ልብስ፣ መልካም ሽታ ያለው ዕንጨት ሁሉ፣ ከዝሆን ጥርስ፣ ከውድ ዕንጨት፣ ከናስ፣ ከብረትና ከእብነ በረድ የተሠራ ዕቃ ሁሉ፣ 13ቀረፋ፣ ቅመም፣ ከርቤ፣ ቅባት፣ ዕጣን፣ የወይን ጠጅ፣ የወይራ ዘይት፣ የተሰለቀ ዱቄት፣ ስንዴ፣ ከብቶች፣ በጎች፣ ፈረሶች፣ ሠረገሎች፣ እንዲሁም ባሮችና18፥13 ግሪኩ ሰውነቶችና ይላል። የሰዎች ነፍሶች ነው።

14“እነርሱም፣ ‘የተመኘሽው ፍሬ ከአንቺ ርቋል፤ ብልጽግናሽና ክብርሽ ሁሉ ጠፍቷል፤ ዳግመኛም ተመልሶ አይመጣም’ ይላሉ። 15እነዚህን ነገሮች በመሸጥ በእርሷ የበለጸጉ ነጋዴዎች ሥቃይዋን ፈርተው በሩቅ ይቆማሉ፤ እነርሱም ያለቅሳሉ፤ ያዝናሉም፤ 16ድምፃቸውን ከፍ አድርገው እንዲህ ይላሉ፤

“ ‘ቀጭን የተልባ እግር፣ ሐምራዊና ቀይ ልብስ የለበሰች፣

በወርቅ፣ በከበረ ድንጋይና በዕንቍም ያጌጠች፣

ታላቂቱ ከተማ ወዮላት! ወዮላት!

17ያ ሁሉ ሀብት በአንድ ሰዓት ውስጥ ጠፋ።’

“የመርከብ አዛዦች ሁሉ፣ በመርከብ የሚጓዙ መንገደኞች ሁሉ፣ የመርከብ ሠራተኞችና ኑሯቸውን በባሕር ላይ የመሠረቱ ሁሉ በሩቅ ይቆማሉ። 18እርሷ ስትቃጠል የሚወጣውን ጢስ ሲያዩ፣ ‘እንደዚህች ያለ ታላቅ ከተማ ከቶ የት አለ?’ እያሉ ይጮኻሉ። 19በራሳቸውም ላይ አቧራ ነስንሰው እያለቀሱና እያዘኑ እንዲህ ብለው ጮኹ፤

“ ‘በባሕር ላይ መርከቦች ያላቸው ሁሉ፣

በእርሷም ሀብት የበለጸጉ፣

ለታላቂቱ ከተማ ወዮላት! ወዮላት!

በአንድ ሰዓት ውስጥ ጠፍታለች!’

20“ሰማይ ሆይ፤ በእርሷ ላይ ሐሤት አድርግ!

ቅዱሳን፣ ሐዋርያትና ነቢያትም ሐሤት አድርጉ!

በእናንተ ላይ ባደረሰችው ነገር እግዚአብሔር ፈርዶባታልና።”

21ከዚያም አንድ ብርቱ መልአክ፣ ትልቅ የወፍጮ ድንጋይ የሚመስል ድንጋይ አንሥቶ ወደ ባሕር ወረወረው፤ እንዲህም አለ፤

“ታላቂቱ ከተማ ባቢሎን፣

እንዲህ ባለ ኀይል ትወረወራለች፤

ተመልሳም አትገኝም።

22የበገና ደርዳሪዎችና የሙዚቀኞች ድምፅ፣

የዋሽንትና የመለከት ነፊዎች ድምፅ፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይሰማም፤

የእጅ ጥበብ ባለሙያ፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይገኝም፤

የወፍጮ ድምፅም፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይሰማም።

23የመብራት ብርሃን፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይበራም፤

የሙሽራውና የሙሽራዪቱ ድምፅ፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይሰማም፤

ነጋዴዎችሽ የዓለም ታላላቅ ሰዎች ነበሩ፤

በአስማትሽም ሕዝቦች ሁሉ ስተዋል።

24በእርሷም ውስጥ የነቢያትና የቅዱሳን፣

በምድርም የተገደሉት ሁሉ ደም ተገኘ።”

Japanese Contemporary Bible

ヨハネの黙示録 18:1-24

18

大いなる都の最後

1これらのことの後、私はもう一人の天使が、大きな権威を授けられて、天から下って来るのを見ました。地上は、その輝きで明るくなりました。 2彼は大声で叫びました。「バビロンが倒れた。あの大いなるバビロンが倒れた。そこは悪魔の巣窟、悪霊やあらゆる汚れた霊のたまり場であった。 3あらゆる国の人々が、彼女のみだらな毒ぶどう酒に酔いしれたからだ。また、地上の支配者たちは彼女と快楽にふけり、地上の商人たちは、彼女のぜいたくな浪費のおかげで大もうけをしたからだ。」

4それから私は、天から別の声を聞きました。

「クリスチャンよ。あの女から遠ざかりなさい。その罪に連なってはなりません。そうでないと、いっしょに罰を受けることになります。 5あの女の罪は数えきれず、それは積み上げられて天にまで達したので、神の罰がいよいよ下るのです。 6あなたがたは、彼女から受けた仕打ちをそっくりそのまま、いや、二倍にして返しなさい。彼女は人々に、多くの災いの飲み物を飲ませようとたくらみました。それを倍にして彼女に飲ませなさい。 7ぜいたく三昧に遊び暮らした女に、それに見合うだけの苦しみと悲しみとを与えなさい。彼女はおごっています。『私は女王で、身寄りのない未亡人とは違う。悲しみなど知らない。』 8そのため、たった一日のうちに、死の悲しみと嘆きと飢えとに襲われ、焼き滅ぼされてしまうのです。さばきをなさる主は、力ある偉大なお方だからです。 9彼女の不純な行為に手を貸し、多くの分け前をもらって、ぜいたくの限りを尽くした地上の支配者たちは、その焼けこげた死体から立ちのぼる煙を見て、涙にくれるでしょう。 10そして、恐怖に震えながら、遠巻きにして立ち、『ああ、悲しいことだ。力ある都バビロンよ。あなたへのさばきは、一瞬のうちに下った』と叫ぶでしょう。

11また、彼女から富を得ていた地上の商人たちも泣き悲しむでしょう。もはや、彼らの商品を買う人がいなくなったからです。 12商品とは、金、銀、宝石、真珠、上等の麻布、紫布、絹、緋色(真紅)の布、種々の香木、象牙細工、高価な木彫り、青銅、鉄、大理石、 13肉桂、香水、香料、香油、乳香、ぶどう酒、オリーブ油、上質の小麦粉、小麦、牛、羊、馬、戦車、奴隷に及び、さらには人の命までも商ったのです。 14地上の商人たちは嘆きます。『あなたの高価な秘蔵品は、全部その手から奪い去られた。あれほど自慢だった、ぜいを尽くした生活はもう二度とできない。すべては永久に失われたのだから。』 15それらの品を商って、彼女から富を得ていた彼らは、わが身への危険を恐れて、遠く離れて立ち、泣き悲しむでしょう。 16-17『ああ、悲しいことだ。あんなに美しかった大いなる都が、あっという間に荒れ果ててしまった。最高級の紫布と緋色の布をまとい、金や宝石や真珠で飾りたてていた都よ。そのすべての富も一瞬のうちに消えてしまった。』

また、各国の船主や商船の船長、乗組員も遠くから、 18彼女が焼かれる煙を見て、涙ながらに、『あれほどすばらしい都が、この世にあっただろうか』と嘆くでしょう。 19そして、頭にちりをかぶって悲しむのです。『ああ、大いなる都よ。その有り余る富のおかげで、われわれは大金持ちになれたのに。それが何もかも、一瞬のうちに失われてしまった。』 20しかし、天よ、神の子どもよ、預言者よ、使徒よ。彼女の最期を喜びなさい。ついに神は、あなたがたのために、彼女にさばきを下されたのです。」

21その時、一人の強い天使が、ひき臼のような丸い石を持ち上げ、海に放り投げて叫びました。「大いなる都バビロンは、この石のように投げ捨てられ、もはや、永久に浮かび上がりません。 22歌声はとだえ、竪琴や笛、ラッパの音ももう聞こえません。さまざまな産業はすたれ、ひき臼をひく人影も、二度と見ることはありません。 23夜は真っ暗闇で、窓からは明かりももれず、結婚式の喜びの鐘も、花婿と花嫁の楽しそうな声も聞こえません。その名を世界に鳴りとどろかせた商人たちも、鳴りをひそめます。彼らは、すべての国の人々をたぶらかす彼女の魔術のおかげで、もうけていたのです。 24彼女には、殉教したすべての預言者や神のきよい民の、血の責任が問われるのです。」