ራእይ 18 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ራእይ 18:1-24

የባቢሎን ውድቀት

1ከዚህ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ ከክብሩም ነጸብራቅ የተነሣ ምድር በራች፤ 2እርሱም በብርቱ ድምፅ እንዲህ ብሎ ጮኸ፤

“ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች! ወደቀች!

የአጋንንት መኖሪያ፣

የርኩሳን መናፍስት ሁሉ መጠጊያ፣

የርኩስና የአስጸያፊ ወፎች ሁሉ መጠለያ ሆነች።

3ሕዝቦች ሁሉ የዝሙቷን ቍጣ ወይን ጠጅ ጠጥተዋልና፤

የምድር ነገሥታት ከእርሷ ጋር አመንዝረዋል፤

የምድርም ነጋዴዎች ከብዙ ምቾቷ ኀይል

የተነሣ በልጽገዋል።”

4ከዚያም ከሰማይ ሌላ ድምፅ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“ሕዝቤ ሆይ፤ በኀጢአቷ እንዳትተባበሩ፤

ከመቅሠፍቷም እንዳትካፈሉ፤

ከእርሷ ውጡ፤

5ኀጢአቷ እስከ ሰማይ ድረስ ተከምሯልና፤

እግዚአብሔርም ዐመፃዋን አስታውሷል።

6በሰጠችው መጠን ብድራቷን መልሱላት፤

ለሠራችው ሁሉ ዕጥፍ ክፈሏት፤

በቀላቀለችውም ጽዋ ዕጥፍ አድርጋችሁ ቀላቅሉባት።

7ለራሷ ክብርና ምቾት የሰጠችውን ያህል፣

ሥቃይና ሐዘን ስጧት፤

በልቧም እንዲህ እያለች ትመካለች፤

‘እንደ ንግሥት ተቀምጬአለሁ፤

መበለትም አይደለሁም፤ ከቶም

አላዝንም፤’

8ስለዚህ መቅሠፍቶቿ በአንድ ቀን ይመጡባታል፤

ሞት፣ ሐዘንና ራብ ይሆኑባታል፤

የሚፈርድባት ጌታ እግዚአብሔር ብርቱ ስለሆነ፣

በእሳት ትቃጠላለች።

9“ከእርሷ ጋር ያመነዘሩና በምቾት የኖሩ የምድር ነገሥታት፣ እርሷ ስትቃጠል የሚወጣውን ጢስ ሲያዩ ስለ እርሷ ያለቅሳሉ፤ ያዝናሉም። 10ሥቃይዋንም በመፍራት በሩቅ ቆመው እንዲህ ይላሉ፤

“ ‘አንቺ ታላቂቱ ከተማ ወዮልሽ! ወዮልሽ!

አንቺ ባቢሎን ብርቱዪቱ ከተማ፣

ፍርድሽ በአንድ ሰዓት ውስጥ መጥቷል።’

11“ጭነታቸውን ከእንግዲህ የሚገዛ ስለሌለ፣ የምድር ነጋዴዎችም ስለ እርሷ ያለቅሳሉ፤ ያዝናሉ፤ 12ጭነቱም፦ ወርቅ፣ ብር፣ የከበረ ድንጋይ፣ ዕንቍ፣ ከተልባ እግር የተሠራ ቀጭን ልብስ፣ ሐምራዊ ልብስ፣ ሐር ልብስ፣ ቀይ ልብስ፣ መልካም ሽታ ያለው ዕንጨት ሁሉ፣ ከዝሆን ጥርስ፣ ከውድ ዕንጨት፣ ከናስ፣ ከብረትና ከእብነ በረድ የተሠራ ዕቃ ሁሉ፣ 13ቀረፋ፣ ቅመም፣ ከርቤ፣ ቅባት፣ ዕጣን፣ የወይን ጠጅ፣ የወይራ ዘይት፣ የተሰለቀ ዱቄት፣ ስንዴ፣ ከብቶች፣ በጎች፣ ፈረሶች፣ ሠረገሎች፣ እንዲሁም ባሮችና18፥13 ግሪኩ ሰውነቶችና ይላል። የሰዎች ነፍሶች ነው።

14“እነርሱም፣ ‘የተመኘሽው ፍሬ ከአንቺ ርቋል፤ ብልጽግናሽና ክብርሽ ሁሉ ጠፍቷል፤ ዳግመኛም ተመልሶ አይመጣም’ ይላሉ። 15እነዚህን ነገሮች በመሸጥ በእርሷ የበለጸጉ ነጋዴዎች ሥቃይዋን ፈርተው በሩቅ ይቆማሉ፤ እነርሱም ያለቅሳሉ፤ ያዝናሉም፤ 16ድምፃቸውን ከፍ አድርገው እንዲህ ይላሉ፤

“ ‘ቀጭን የተልባ እግር፣ ሐምራዊና ቀይ ልብስ የለበሰች፣

በወርቅ፣ በከበረ ድንጋይና በዕንቍም ያጌጠች፣

ታላቂቱ ከተማ ወዮላት! ወዮላት!

17ያ ሁሉ ሀብት በአንድ ሰዓት ውስጥ ጠፋ።’

“የመርከብ አዛዦች ሁሉ፣ በመርከብ የሚጓዙ መንገደኞች ሁሉ፣ የመርከብ ሠራተኞችና ኑሯቸውን በባሕር ላይ የመሠረቱ ሁሉ በሩቅ ይቆማሉ። 18እርሷ ስትቃጠል የሚወጣውን ጢስ ሲያዩ፣ ‘እንደዚህች ያለ ታላቅ ከተማ ከቶ የት አለ?’ እያሉ ይጮኻሉ። 19በራሳቸውም ላይ አቧራ ነስንሰው እያለቀሱና እያዘኑ እንዲህ ብለው ጮኹ፤

“ ‘በባሕር ላይ መርከቦች ያላቸው ሁሉ፣

በእርሷም ሀብት የበለጸጉ፣

ለታላቂቱ ከተማ ወዮላት! ወዮላት!

በአንድ ሰዓት ውስጥ ጠፍታለች!’

20“ሰማይ ሆይ፤ በእርሷ ላይ ሐሤት አድርግ!

ቅዱሳን፣ ሐዋርያትና ነቢያትም ሐሤት አድርጉ!

በእናንተ ላይ ባደረሰችው ነገር እግዚአብሔር ፈርዶባታልና።”

21ከዚያም አንድ ብርቱ መልአክ፣ ትልቅ የወፍጮ ድንጋይ የሚመስል ድንጋይ አንሥቶ ወደ ባሕር ወረወረው፤ እንዲህም አለ፤

“ታላቂቱ ከተማ ባቢሎን፣

እንዲህ ባለ ኀይል ትወረወራለች፤

ተመልሳም አትገኝም።

22የበገና ደርዳሪዎችና የሙዚቀኞች ድምፅ፣

የዋሽንትና የመለከት ነፊዎች ድምፅ፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይሰማም፤

የእጅ ጥበብ ባለሙያ፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይገኝም፤

የወፍጮ ድምፅም፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይሰማም።

23የመብራት ብርሃን፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይበራም፤

የሙሽራውና የሙሽራዪቱ ድምፅ፣

ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይሰማም፤

ነጋዴዎችሽ የዓለም ታላላቅ ሰዎች ነበሩ፤

በአስማትሽም ሕዝቦች ሁሉ ስተዋል።

24በእርሷም ውስጥ የነቢያትና የቅዱሳን፣

በምድርም የተገደሉት ሁሉ ደም ተገኘ።”

Habrit Hakhadasha/Haderekh

התגלות 18:1-24

1אחרי כן ראיתי מלאך אחר יורד מן השמים. מלאך זה היה בעל סמכות גדולה וכוח רב, וזוהר כבודו האיר על כל הארץ.

2”בבל הגדולה נפלה!“ קרא המלאך בקול אדיר. ”בבל הפכה למשכן שדים, ומחסה לרוחות טמאות ולעופות טמאים ושנואים. 3כי כל העמים שתו מיין זנותה; מלכי הארץ זנו ונאפו איתה, וסוחרי הארץ התעשרו מחיי התענוגות, המותרות והבזבוז שניהלה.“

4ואז שמעתי קול אחר מן השמים: ”צאו ממנה, עמי! אל תשתתפו בחטאיה, פן תיענשו כמוה! 5כי חטאותיה הגיעו עד השמים, ואלוהים מוכן לשפטה על פשעיה! 6שלמו לה כגמולה; השיבו לה כפליים מהמעשים הרעים שעשתה לאחרים. היא מזגה כוס תמרורים לאנשים רבים – מיזגו לה אתם שתי כוסות! 7‏-8השיבו לה צער וייסורים כמידת גאוותה ותענוגותיה! כי בלבה היא מתייהרת ואומרת: ’אני מלכה שלטת – אינני אלמנה חסרת־אונים ולא אסבול צער וכאב!‘ משום כך ביום אחד היא תוכה בצער, מוות, אבל, רעב ותישרף באש, כי האלוהים השופט אותה הוא אל גיבור!“

9כשיביטו מלכי הארץ שזנו איתה בעשן העולה משריפתה, הם יבכו ויספדו. 10הם יעמדו מרחוק, כי יפחדו מעינוייה, ויקראו: ”אוי לך, בבל העיר הגדולה והחזקה! ברגע אחד בא משפטך ונחרץ דינך!“

11סוחרי הארץ יבכו ויתאבלו עליה, כי איש לא יקנה יותר את הסחורה שייבאו באוניות. 12היא הייתה הלקוחה הגדולה ביותר שלהם לקניית זהב, כסף, אבנים־יקרות, פנינים, בדים יקרים, ארגמן, משי, שני, עצי בושם למיניהם, כלי שנהב, כלי עץ יקרים, כלי נחושת, ברזל ושיש; 13קינמון, בשמים יקרים, יינות, שמן, סולת, קמח, בקר וצאן, סוסים, מרכבות, עבדים ואפילו נפשות אדם.

14”כל הדברים היקרים שחמדת ואהבת כל־כך נלקחו ממך!“ יקראו הסוחרים. ”כל הפאר, ההדר והפינוקים אשר אהבת אבדו לך לעולמים!“

15הסוחרים אשר התעשרו ממנה יעמדו מרחוק, מתוך פחד ויראה מייסוריה, יתאבלו ויבכו: 16”אוי, העיר הגדולה והיפה, העיר שדומה לאישה עטופה באריג משובח, אדום וארגמן, ומקושטת בזהב, באבנים יקרות ובפנינים, 17ברגע אחד ירד כל העושר הזה לטמיון!“

כל בעלי האוניות, רבי־החובלים ויורדי־הים האחרים יעמדו מרחוק, 18ובהביטם על עשנה עולה שמימה יקראו: ”היש עוד עיר גדולה כעיר הזאת?“ 19הם יזרקו עפר על ראשם, יבכו, יספדו ויצעקו: ”אוי ואבוי לעיר הגדולה! היא העשירה את כולנו – את הסוחרים ואת יורדי־הים – ועתה, בשעה אחת הוחרבה…“

20גילו, השמים, שמחו על סופה! בני־אלוהים, השליחים והנביאים שמחו גם אתם, כי סוף־סוף שפט אותה אלוהים בשמכם!

21מלאך גיבור הרים אבן גדולה שנראתה כאבן־רחיים, השליכה בעוצמה אל תוך הים ואמר: ”כך תושלך בבל הגדולה ותיעלם לנצח! 22לא יישמע בקרבך קול זימרה, נגינת כינורות, חלילים וחצוצרות. לא יישמע אצלך קול מסגר בעבודתו או קול בעל־מלאכה אחר, ולא יישמע קול טחינת החיטה. 23לעולם לא יאיר בקרבך אור מנורה; לא ייערכו אצלך יותר חגיגות־חתונה, ולא תישמענה צהלות שמחה של חתן וכלה.

”כי הסוחרים שלך היו מנכבדי הארץ, ובקסמיך וכישופיך רימית את כל העמים.

24”את אחראית לדם הנביאים, בני־האלוהים וכל אלה שנרצחו בארץ, כי דמם נמצא בך!“