ራእይ 16 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ራእይ 16:1-21

ሰባቱ የእግዚአብሔር ቍጣ ጽዋዎች

1ከዚያም ለሰባቱ መላእክት፣ “ሂዱ፤ ሰባቱን የእግዚአብሔር ቍጣ ጽዋዎች በምድር ላይ አፍስሱ” የሚል ታላቅ ድምፅ ከቤተ መቅደሱ ሰማሁ።

2የመጀመሪያው መልአክ ሄዶ ጽዋውን በምድር ላይ አፈሰሰ፤ የአውሬውን ምልክት በተቀበሉትና ለምስሉም በሰገዱት ሰዎች ላይ ክፉኛ የሚያሠቃይ ቍስል ወጣባቸው።

3ሁለተኛው መልአክ ጽዋውን በባሕር ላይ አፈሰሰ፤ ባሕሩም እንደ ሞተ ሰው ደም ሆነ፤ በባሕሩ ውስጥ የሚኖሩ ሕይወት ያላቸው ነገሮች ሁሉ ሞቱ።

4ሦስተኛው መልአክ ጽዋውን በወንዞችና በውሃ ምንጮች ላይ አፈሰሰ፤ እነርሱም ደም ሆኑ። 5ከዚያም በውሆች ላይ ሥልጣን ያለው መልአክ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“ያለህና የነበርህ ቅዱሱ ሆይ፤

እንዲህ ስለ ፈረድህ፣

አንተ ጻድቅ ነህ፤

6የቅዱሳንንና የነቢያትን ደም ስላፈሰሱ፣

አንተም ደግሞ ደም እንዲጠጡ አደረግሃቸው፤ ይህ የሚገባቸው ነውና።”

7እንዲሁም ከመሠዊያው እንዲህ የሚል ድምፅ ሰማሁ፤

“አዎን፤ ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ ሆይ፤

ፍርድህ እውነትና ጽድቅ ነው።”

8አራተኛውም መልአክ ጽዋውን በፀሓይ ላይ አፈሰሰ፤ ፀሓይም ሰዎችን በእሳት እንድታቃጥል ኀይል ተሰጣት። 9እነርሱም በታላቅ ሐሩር ተቃጠሉ፤ በእነዚህም መቅሠፍቶች ላይ ሥልጣን ያለውን የእግዚአብሔርን ስም ተሳደቡ እንጂ ንስሓ አልገቡም፤ ክብርም አልሰጡትም።

10አምስተኛውም መልአክ ጽዋውን በአውሬው ዙፋን ላይ አፈሰሰ፤ የአውሬውም መንግሥት በጨለማ ተዋጠ፤ ሰዎችም ከሥቃያቸው የተነሣ ምላሳቸውን ያኝኩ ነበር፤ 11ደግሞም ከሥቃያቸውና ከቍስላቸው የተነሣ የሰማይን አምላክ ተሳደቡ እንጂ ከሥራቸው ንስሓ አልገቡም።

12ስድስተኛውም መልአክ ጽዋውን በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ ላይ አፈሰሰ፤ ከምሥራቅ ለሚመጡ ነገሥታት መንገድ እንዲዘጋጅላቸው የወንዙ ውሃ ደረቀ። 13ከዚያም ከዘንዶው አፍ፣ ከአውሬው አፍና ከሐሰተኛው ነቢይ አፍ እንቍራሪት የሚመስሉ ሦስት ርኩሳን መናፍስት ሲወጡ አየሁ። 14እነርሱም ምልክቶች የሚያደርጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸው፤ ሁሉን በሚችል አምላክ ታላቅ ቀን ለሚሆነው ጦርነት እንዲሰበስቧቸው ወደ ዓለም ሁሉ ነገሥታት ይሄዳሉ።

15“እነሆ፤ እንደ ሌባ እመጣለሁ፤ ዕራቍቱን እንዳይሆን ኀፍረቱም እንዳይታይ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ሰው ብፁዕ ነው።”

16እነርሱም ነገሥታቱን በዕብራይስጥ አርማጌዶን በሚባል ስፍራ ሰበሰቧቸው።

17ሰባተኛውም መልአክ ጽዋውን በአየር ላይ አፈሰሰ፤ በቤተ መቅደሱ ውስጥ ካለው ዙፋንም “ተፈጸመ!” የሚል ታላቅ ድምፅ ወጣ። 18ከዚያም መብረቅ፣ ድምፅ፣ ነጐድጓድና ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ ሰው በምድር ላይ ከተፈጠረ ጀምሮ እንዲህ ያለ ታላቅ የምድር መናወጥ ታይቶ አይታወቅም፤ ነውጡም እጅግ ታላቅ ነበር። 19ታላቂቱ ከተማ ከሦስት ተከፈለች፤ የሕዝቦች ከተሞችም ፈራረሱ፤ እግዚአብሔርም ታላቂቱን ባቢሎን አስታወሰ፤ በብርቱ ቍጣው ወይን ጠጅ የተሞላውን ጽዋ ሰጣት። 20ደሴቶች ሁሉ ሸሹ፤ ተራሮችም ሊገኙ አልቻሉም። 21በሚዛን ሲመዘን እያንዳንዱ አርባ አምስት ኪሎ ግራም16፥21 ግሪኩ አንድ ታላንት ይለዋል። የሚሆን ታላቅ በረዶ በሰዎች ላይ ከሰማይ ወረደባቸው፤ መቅሠፍቱ እጅግ አሠቃቂ ስለ ነበር፣ ሰዎቹ ከበረዶው መቅሠፍት የተነሣ እግዚአብሔርን ተሳደቡ።

Thai New Contemporary Bible

วิวรณ์ 16:1-21

ขันทั้งเจ็ดแห่งพระพิโรธของพระเจ้า

1จากนั้นข้าพเจ้าได้ยินเสียงดังออกมาจากพระวิหารสั่งทูตสวรรค์ทั้งเจ็ดว่า “จงไปเทพระพิโรธของพระเจ้าที่อยู่ในขันทั้งเจ็ดลงบนโลกเถิด”

2ทูตสวรรค์องค์แรกออกไปเทขันของตนลงบนแผ่นดินโลก แผลร้ายน่าเกลียดที่สร้างความเจ็บปวดก็เกิดขึ้นที่ตัวของบรรดาผู้มีเครื่องหมายของสัตว์ร้ายและกราบนมัสการรูปจำลองของมัน

3ทูตสวรรค์องค์ที่สองเทขันของตนลงบนทะเล ทะเลก็กลายเป็นเลือดดั่งเลือดของคนตาย สิ่งมีชีวิตในนั้นจึงตายหมด

4ทูตสวรรค์องค์ที่สามเทขันของตนลงบนแม่น้ำและบ่อน้ำพุทั้งหลาย น้ำก็กลายเป็นเลือด 5แล้วข้าพเจ้าได้ยินทูตสวรรค์ผู้ดูแลห้วงน้ำกล่าวว่า

“ข้าแต่องค์ผู้บริสุทธิ์

พระองค์ผู้ทรงดำรงอยู่ทั้งในอดีตและในปัจจุบ้น

พระองค์ทรงพิพากษาลงโทษอย่างยุติธรรมแล้ว

6เนื่องจากพวกเขาทำให้ประชากรของพระเจ้า

และผู้เผยพระวจนะของพระองค์ต้องหลั่งเลือด

สมควรแล้วที่พระองค์ทรงให้พวกเขาดื่มเลือด”

7และข้าพเจ้าได้ยินแท่นบูชาขานรับว่า

“จริงเช่นนั้นข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้าพระเจ้าผู้ทรงฤทธิ์

การพิพากษาของพระองค์เที่ยงแท้และเที่ยงธรรม”

8ทูตสวรรค์องค์ที่สี่เทขันของตนลงบนดวงอาทิตย์ ดวงอาทิตย์ก็ได้รับอำนาจที่จะแผดแสงเผามนุษย์ 9พวกเขาถูกความร้อนแรงกล้าแผดเผาและพวกเขาแช่งด่าพระนามของพระเจ้าผู้ทรงควบคุมภัยพิบัติเหล่านี้ แต่พวกเขาไม่ยอมกลับใจสำนึกผิดและถวายพระเกียรติสิริแด่พระองค์

10ทูตสวรรค์องค์ที่ห้าเทขันของตนลงบนบัลลังก์ของสัตว์ร้ายนั้น อาณาจักรของมันก็จมดิ่งสู่ความมืดมิด ผู้คนกัดลิ้นด้วยความทุกข์ทรมาน 11และแช่งด่าพระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์เพราะความเจ็บปวดรวดร้าวและแผลร้ายของตน แต่พวกเขาไม่ยอมกลับใจจากบาปที่ได้ทำไป

12ทูตสวรรค์องค์ที่หกเทขันของตนลงบนแม่น้ำใหญ่ชื่อยูเฟรติส น้ำก็เหือดแห้งเพื่อเตรียมทางไว้สำหรับกษัตริย์ทั้งหลายจากตะวันออก 13แล้วข้าพเจ้าเห็นวิญญาณชั่ว16:13 ภาษากรีกว่าโสโครกสามตนรูปร่างคล้ายกบ ออกมาจากปากพญานาค จากปากของสัตว์ร้าย และจากปากของผู้เผยพระวจนะเท็จ 14พวกมันเป็นวิญญาณของผีมารที่ทำหมายสำคัญต่างๆ มันออกไปหาปวงกษัตริย์ทั่วโลกเพื่อระดมกษัตริย์เหล่านั้นมาทำสงครามในวันยิ่งใหญ่แห่งพระเจ้าผู้ทรงฤทธิ์

15“ดูเถิด เราจะมาเหมือนขโมยที่มาโดยไม่มีใครคาดคิด ความสุขมีแก่ผู้ที่ตื่นอยู่และแต่งตัวเตรียมพร้อมเพื่อพวกเขาจะได้ไม่ต้องเดินเปลือยกายให้อับอายขายหน้า”

16แล้ววิญญาณชั่วทั้งสามก็ระดมกษัตริย์ทั้งหลายมาชุมนุมกันในที่ซึ่งภาษาฮีบรูเรียกว่า อารมาเกดโดน

17ทูตสวรรค์องค์ที่เจ็ดเทขันของตนลงในอากาศและมีเสียงมาจากพระที่นั่งในพระวิหารว่า “สำเร็จแล้ว!” 18จากนั้นเกิดฟ้าแลบแวบวาบ เสียงครืนๆ เสียงฟ้าร้องกึกก้อง และแผ่นดินไหวครั้งรุนแรงนับตั้งแต่มนุษย์อยู่บนโลกมาไม่เคยมีแผ่นดินไหวร้ายแรงเช่นครั้งนี้เลย 19มหานครแยกออกเป็นสามส่วน เมืองใหญ่ๆ ของประเทศต่างๆ พังทลายลง พระเจ้าทรงจดจำบาปของบาบิโลนมหานครได้ พระองค์ทรงให้มันดื่มจากถ้วยที่เต็มด้วยเหล้าองุ่นแห่งพระพิโรธอันใหญ่หลวงของพระองค์ 20เกาะทุกเกาะและภูเขาทุกลูกจมหายไปหมด 21ลูกเห็บมหึมาตกจากฟ้าใส่ผู้คน แต่ละก้อนหนักราว 50 กิโลกรัม16:21 ภาษากรีกว่า1 ตะลันต์ และพวกเขาแช่งด่าพระเจ้าเพราะภัยพิบัติจากลูกเห็บนี้ร้ายแรงยิ่งนัก