ራእይ 13 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ራእይ 13:1-18

1ዘንዶውም13፥1 አንዳንድ የጥንት ቅጆች እኔም በባሕሩ ዳር ቆሜ ነበር ይላሉ። በባሕሩ ዳር ቆሞ ነበር።

ከባሕር የወጣው አውሬ

ከዚያም አንድ አውሬ ከባሕር ሲወጣ አየሁ፤ እርሱም ዐሥር ቀንዶችና ሰባት ራሶች ነበሩት፤ በቀንዶቹም ላይ ዐሥር ዘውዶች፣ በራሶቹም ላይ የስድብ ስሞች ነበሩት። 2ያየሁትም አውሬ ነብር ይመስል ነበር፤ ነገር ግን እግሮቹ የድብ፣ አፉ ደግሞ የአንበሳ አፍ ይመስል ነበር፤ ዘንዶው የራሱን ኀይልና የራሱን ዙፋን እንዲሁም ታላቅ ሥልጣን ለአውሬው ሰጠው። 3ከአውሬው ራሶች አንዱ ለሞት የሚያደርስ ቍስል ያለበት ይመስል ነበር። ነገር ግን ለሞት የሚያደርሰው ቍስሉ ዳነ፤ ዓለም በሙሉ በመደነቅ አውሬውን ተከተለው። 4ሰዎችም ለዘንዶው ሰገዱለት፤ ምክንያቱም ሥልጣኑን ለአውሬው ሰጥቶታል። ደግሞም፣ “አውሬውን የሚመስል ማን ነው? ከእርሱስ ጋር ማን ሊዋጋ ይችላል?” በማለት ለአውሬው ሰገዱለት።

5አውሬው የትዕቢት ቃል የሚናገርበትና የሚሳደብበት አፍ ተሰጠው፤ አርባ ሁለት ወር በሥልጣን እንዲሠራም ተፈቀደለት። 6እርሱም እግዚአብሔርን ለመሳደብ እንዲሁም ስሙንና ማደሪያውን፣ በሰማይም የሚኖሩትን ለመሳደብ አፉን ከፈተ። 7ቅዱሳንን እንዲዋጋና ድልም እንዲነሣቸው ኀይል ተሰጠው። በነገድ፣ በወገን፣ በቋንቋና በሕዝብም ሁሉ ላይ ሥልጣን ተሰጠው። 8ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ13፥8 ወይም ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ስሞቻቸው በታረደው በግ የሕይወት መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈው በታረደው በግ የሕይወት መጽሐፍ ላይ ስሞቻቸው ያልተጻፈ የምድር ሰዎች ሁሉ ለአውሬው ይሰግዳሉ።

9ጆሮ ያለው ቢኖር ይስማ።

10ማንም የሚማረክ ቢኖር፣

እርሱ ይማረካል፤

ማንም በሰይፍ የሚገደል13፥10 አንዳንድ የጥንት ቅጆች የሚገድል ይላሉ። ቢኖር፣

እርሱ በሰይፍ ይገደላል።

ይህም የቅዱሳን ትዕግሥትና እምነት የሚታየው በዚህ እንደ ሆነ ያስገነዝባል።

ከምድር የወጣው አውሬ

11ከዚያም ሌላ አውሬ ከምድር ሲወጣ አየሁ፤ እርሱም እንደ በግ ሁለት ቀንዶች ነበሩት፤ ነገር ግን እንደ ዘንዶ ይናገር ነበር። 12በመጀመሪያው አውሬ ስም በሙሉ ሥልጣን ይሠራ ነበር፤ ምድርና በእርሷም የሚኖሩ ሁሉ፣ ለሞት ከሚያደርሰው ቍስል የዳነውን የመጀመሪያውን አውሬ እንዲያመልኩ አደረገ። 13በሰዎቹም ፊት እሳት ከሰማይ ወደ ምድር እስኪያወርድ ድረስ ታላላቅ ምልክቶችን አደረገ። 14በመጀመሪያው አውሬ ስም ምልክቶችን እንዲያደርግ ሥልጣን ስለ ተሰጠው፣ በምድር የሚኖሩ ሰዎችን አሳተ፤ በሰይፍ ቈስሎ ለነበረው፣ ነገር ግን በሕይወት ለሚኖረው አውሬ ምስል እንዲያቆሙም አዘዛቸው። 15ደግሞም የመጀመሪያው አውሬ ምስል መናገር እንዲችል ለምስሉ እስትንፋስ ለመስጠትና ለዚህም ምስል የማይሰግዱ ሁሉ እንዲገደሉ ለማድረግ ሥልጣን ተሰጠው። 16እንዲሁም ታናናሾችና ታላላቆች፣ ሀብታሞችና ድኾች፣ ጌቶችና ባሮች ሁሉ በቀኝ እጃቸው ወይም በግንባራቸው ላይ ምልክት እንዲቀበሉ አስገደዳቸው፤ 17ይህም የሆነው የአውሬው ምልክት፣ ይኸውም ስሙ ወይም የስሙ ቍጥር የሌለው ማንም ሰው ለመግዛትም ሆነ ለመሸጥ እንዳይችል ነው።

18ይህ ጥበብ ይጠይቃል፤ አእምሮ ያለው ማንኛውም ሰው የአውሬውን ቍጥር ያስላው፤ ምክንያቱም ቍጥሩ የሰው ቍጥር ነው። ቍጥሩ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት ነው።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

התגלות 13:1-18

1עתה ראיתי חיה מוזרה עולה מן הים ולה שבעה ראשים, עשר קרניים ועל כל קרן כתר. על כל אחד משבעת ראשיה היו כתובים שמות גידופים, כל שם מקלל ומבזה את אלוהים. 2החיה נראתה כנמר, אך רגליה דמו לרגלי דוב ופיה דמה לפי אריה. התנין העניק לה את כוחו, את כסא מלכותו וסמכות רבה.

3אחד מראשי החיה נראה פצוע פצעי מוות, אך הפצעים הגלידו. העולם כולו התפעל מהפלא הזה, ואנשים רבים הלכו אחרי החיה. 4בני־האדם השתחוו לתנין מפני שהעניק לחיה כוח רב; הם השתחוו גם לחיה וקראו: ”מי ידמה לחיה? מי מסוגל להילחם נגדה?“

5החיה הורשתה לקלל ולחרף את שם ה׳, וניתנה לה סמכות לעשות כרצונה במשך ארבעים ושניים חודשים. 6היא פתחה את פיה, חרפה וניאצה את אלוהים, את שמו, את מקדשו ואת כל השוכנים בשמים. 7החיה הורשתה להילחם במאמינים ולנצחם. היא אף קיבלה שלטון על כל העמים, הארצות והשפות בעולם. 8כל בני־האדם אשר שמם לא נכתב בספר־החיים של השה הטבוח, לפני בריאת העולם, השתחוו לחיה הרעה.

9מי שמסוגל לשמוע שיקשיב היטב: 10על מי שנגזר להיאסר, ייאסר; מי שמיועד למות בחרב ימות בחרב. אולם אל תפחדו, כי זוהי לכם הזדמנות להוכיח את אמונתכם ואת כוח־עמידתכם.

11אחרי כן ראיתי חיה מוזרה אחרת עולה מן האדמה. היו לה שתי קרניים כקרני השה וקולה כקול התנין. 12לחיה השנייה ניתנו כוח וסמכות מאת החיה הראשונה, והיא הביאה לכך שכל הארץ ותושביה ישתחוו לחיה שפצעי־המוות שלה הגלידו. 13החיה השנייה חוללה ניסים ונפלאות; היא אפילו הורידה אש מן השמים לנגד עיני בני־האדם שצפו בה. 14באמצעות הניסים והנפלאות שניתן לה לחולל בנוכחות החיה הראשונה, היא הוליכה שולל את אנשי הארץ. היא ציוותה עליהם לבנות פסל בדמות החיה הראשונה שהוכתה מכת מוות אך שבה לתחייה. 15הותר לה להפיח רוח חיים בפסל, ואפילו להביאו לכדי דיבור. את כל אלה שסירבו להשתחוות לפסל בדמות החיה הראשונה, היא המיתה.

16‏-17החיה השנייה דרשה מכל בני־האדם – מקטן ועד גדול, מהעניים ומהעשירים, מהעבדים ומבני־החורין – לסמן סימן היכר מיוחד על ידם הימנית או על מצחם, (את שמה, או את הערך הגמטרי של שמה) כדי שאיש לא יוכל למכור או לקנות ללא סימן ההיכר של החיה. 18כאן דרושה תבונה. מי שיכול יפענח את מספר החיה, שהיא אדם והערך הגמטרי של שמו 666.