ራእይ 12 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ራእይ 12:1-17

ሴቲቱና ዘንዶው

1ታላቅና አስደናቂ ምልክት በሰማይ ታየ፤ ፀሓይን የለበሰች፣ ጨረቃን ከእግሮቿ በታች የረገጠችና በራሷም ላይ ዐሥራ ሁለት ከዋክብት ያሉት አክሊል የደፋች አንዲት ሴት ታየች። 2እርሷም ነፍሰ ጡር ነበረች፤ ልትወልድ ስትል ምጥ ይዟት ተጨንቃ ጮኸች። 3ከዚያም ሌላ ምልክት በሰማይ ታየ፤ እነሆ፤ ሰባት ራሶችና ዐሥር ቀንዶች የነበሩት፣ በራሶቹም ላይ ሰባት አክሊል የደፋ ታላቅ ቀይ ዘንዶ ታየ። 4ጅራቱ የከዋክብትን አንድ ሦስተኛ ከሰማይ ስቦ ወደ ምድር ጣላቸው፤ እርሷም በወለደች ጊዜ ልጇን ለመዋጥ ፈልጎ ዘንዶው ልትወልድ በተቃረበችው ሴት ፊት ቆመ። 5ሕዝቦችን ሁሉ በብረት በትር የሚገዛውን ወንድ ልጅ ወለደች፤ ልጇም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ። 6ሴቲቱም አንድ ሺሕ ሁለት መቶ ስድሳ ቀን ክብካቤ እንዲደረግላት እግዚአብሔር ወዳዘጋጀላት ስፍራ ወደ በረሓ ሸሸች።

7በሰማይም ጦርነት ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ከዘንዶው ጋር ተዋጉ፤ ዘንዶውና መላእክቱም መልሰው ተዋጓቸው፤ 8ነገር ግን ድል ተመቱ፤ በሰማይም የነበራቸውን ስፍራ ዐጡ። 9ታላቁ ዘንዶ፣ የጥንቱ እባብ ተጣለ፤ እርሱም ዲያብሎስ ወይም ሰይጣን ተብሎ የሚጠራው፣ ዓለምን ሁሉ የሚያስተው ነው፤ እርሱ ወደ ምድር ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።

10ከዚህ በኋላ ታላቅ ድምፅ በሰማይ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“አሁን የአምላካችን ማዳን፣ ኀይልና

መንግሥት፣

የእርሱ ክርስቶስ ሥልጣንም መጥቷል።

ቀንና ሌሊት በአምላካችን ፊት ሲከስሳቸው

የነበረው፣

የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሏልና።

11እነርሱም በበጉ ደም፣

በምስክርነታቸውም ቃል፣

ድል ነሡት፤

እስከ ሞት ድረስ እንኳ፣

ለነፍሳቸው አልሳሱም።

12ስለዚህ ሰማያት ሆይ፣

በውስጣቸውም የምትኖሩ ሆይ፣

ደስ ይበላችሁ፤

ምድርና ባሕር ግን ወዮላችሁ! ምክንያቱም ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን ብቻ

እንደ ቀረው ስላወቀ፣

በታላቅ ቍጣ ተሞልቶ ወደ እናንተ ወርዷል።”

13ዘንዶው ወደ ምድር እንደ ተጣለ ባየ ጊዜ፣ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሳደዳት። 14ሴቲቱም በበረሓ ወደ ተዘጋጀላት ስፍራ በርራ መሄድ እንድትችል ሁለት የታላቁ ንስር ክንፎች ተሰጣት፤ ይህም የሆነው በዚያ ከእባቡ ፊት ርቃ ለአንድ ዘመን፣ ለዘመናትና ለዘመን እኩሌታ በክብካቤ እንድትኖር ነው። 15እባቡም ሴቲቱ በጐርፍ እንድትወሰድ፣ እንደ ወንዝ ያለ ውሃ ከአፉ ተፋ። 16ምድር ግን ሴቲቱን ረዳቻት፤ አፏንም ከፍታ ዘንዶው ከአፉ ያፈሰሰውን ወንዝ ዋጠች። 17ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጣ፤ ከቀሩት ልጆቿም ጋር ሊዋጋ ሄደ፤ እነርሱ የእግዚአብሔርን ትእዛዞች የሚጠብቁና የኢየሱስን ምስክር አጥብቀው የያዙ ናቸው።

Thai New Contemporary Bible

วิวรณ์ 12:1-17

ผู้หญิงและพญานาค

1มีหมายสำคัญอันอัศจรรย์และยิ่งใหญ่ปรากฏขึ้นในสวรรค์คือ หญิงคนหนึ่งมีดวงอาทิตย์เป็นอาภรณ์ ดวงจันทร์อยู่ใต้เท้า และดาวสิบสองดวงเป็นมงกุฎบนศีรษะ 2หญิงนั้นตั้งครรภ์และร้องด้วยความเจ็บปวดเพราะจวนจะคลอดแล้ว 3จากนั้นมีหมายสำคัญอีกอย่างหนึ่งเกิดขึ้นในสวรรค์คือ พญานาคใหญ่สีแดงตัวหนึ่ง มีเจ็ดหัวและสิบเขา ทั้งเจ็ดหัวสวมมงกุฎ 4หางของมันตวัดหนึ่งในสามของดวงดาวในท้องฟ้าทิ้งลงมาบนโลก พญานาคนั้นยืนอยู่หน้าหญิงที่กำลังจะคลอดเพื่อมันจะได้กินทารกในทันทีที่เกิดมา 5หญิงนั้นคลอดบุตรชายผู้ซึ่งจะปกครองมวลประชาชาติด้วยคทาเหล็ก บุตรนั้นถูกฉวยออกมาและนำขึ้นไปเข้าเฝ้าพระเจ้า ไปยังพระที่นั่งของพระองค์ 6ส่วนหญิงนั้นหนีไปยังถิ่นกันดารสู่ที่พำนักซึ่งพระเจ้าทรงเตรียมไว้สำหรับนาง ที่นั่นนางจะได้รับการเลี้ยงดูเป็นเวลา 1,260 วัน

7และเกิดสงครามขึ้นในสวรรค์ มีคาเอลกับทูตสวรรค์ของเขาสู้รบกับพญานาคและสมุนของมัน 8ฝ่ายของพญานาคพ่ายแพ้ ถูกขับไล่ออกจากสวรรค์ 9พญานาคใหญ่ถูกเหวี่ยงลงมา พญานาคนี้คืองูดึกดำบรรพ์ที่เรียกกันว่า มาร หรือ ซาตาน ผู้ล่อลวงคนทั้งโลกให้หลงผิด มันถูกเหวี่ยงลงมาบนโลกพร้อมกับทูตสวรรค์ของมัน

10แล้วข้าพเจ้าได้ยินเสียงดังในสวรรค์กล่าวว่า

“บัดนี้ความรอด เดชานุภาพ และราชอาณาจักรของพระเจ้าของเรา

และสิทธิอำนาจแห่งพระคริสต์ของพระองค์มาถึงแล้ว

เพราะผู้กล่าวโทษบรรดาพี่น้องของเรา

ซึ่งกล่าวโทษเขาต่อหน้าพระเจ้า

ของเราทั้งวันทั้งคืน

ได้ถูกเหวี่ยงลงไปแล้ว

11พวกเขาชนะพญามาร

โดยพระโลหิตของพระเมษโปดก

และโดยคำพยานของตน

พวกเขาไม่กลัวตาย

ไม่เสียดายชีวิต

12เพราะฉะนั้นสวรรค์และชาวสวรรค์เอ๋ย

จงชื่นชมยินดีเถิด!

แต่วิบัติแก่แผ่นดินและทะเล

เพราะมารได้ลงไปหาเจ้า!

ด้วยความโกรธยิ่งนัก

เนื่องจากรู้ว่าเวลาของมันมีน้อย”

13เมื่อพญานาคเห็นว่าตนถูกทิ้งลงบนโลกก็ไล่ล่าหญิงซึ่งคลอดบุตรชายนั้น 14หญิงนั้นได้รับปีกพญาอินทรีสองปีกเพื่อจะได้บินไปยังที่ซึ่งจัดเตรียมไว้ให้นางในถิ่นกันดาร ที่นั่นนางจะได้รับการปกป้องเลี้ยงดูให้พ้นจากพญานาคตลอดหนึ่งวาระ สองวาระและครึ่งวาระ 15พญานาคนั้นก็พ่นน้ำออกมามากมายเหมือนแม่น้ำเพื่อซัดนางให้ลอยไปตามกระแสน้ำ 16แต่แผ่นดินช่วยนางไว้ มันแยกออกสูบเอาแม่น้ำซึ่งพญานาคพ่นออกจากปากลงไป 17แล้วพญานาคก็โกรธแค้นหญิงนั้นและไปทำสงครามกับลูกหลานของนางที่เหลือคือ คนเหล่านั้นที่เชื่อฟังพระบัญชาของพระเจ้าและยึดมั่นในคำพยานเรื่องพระเยซู