ራእይ 12 – NASV & SNC

New Amharic Standard Version

ራእይ 12:1-17

ሴቲቱና ዘንዶው

1ታላቅና አስደናቂ ምልክት በሰማይ ታየ፤ ፀሓይን የለበሰች፣ ጨረቃን ከእግሮቿ በታች የረገጠችና በራሷም ላይ ዐሥራ ሁለት ከዋክብት ያሉት አክሊል የደፋች አንዲት ሴት ታየች። 2እርሷም ነፍሰ ጡር ነበረች፤ ልትወልድ ስትል ምጥ ይዟት ተጨንቃ ጮኸች። 3ከዚያም ሌላ ምልክት በሰማይ ታየ፤ እነሆ፤ ሰባት ራሶችና ዐሥር ቀንዶች የነበሩት፣ በራሶቹም ላይ ሰባት አክሊል የደፋ ታላቅ ቀይ ዘንዶ ታየ። 4ጅራቱ የከዋክብትን አንድ ሦስተኛ ከሰማይ ስቦ ወደ ምድር ጣላቸው፤ እርሷም በወለደች ጊዜ ልጇን ለመዋጥ ፈልጎ ዘንዶው ልትወልድ በተቃረበችው ሴት ፊት ቆመ። 5ሕዝቦችን ሁሉ በብረት በትር የሚገዛውን ወንድ ልጅ ወለደች፤ ልጇም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ። 6ሴቲቱም አንድ ሺሕ ሁለት መቶ ስድሳ ቀን ክብካቤ እንዲደረግላት እግዚአብሔር ወዳዘጋጀላት ስፍራ ወደ በረሓ ሸሸች።

7በሰማይም ጦርነት ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ከዘንዶው ጋር ተዋጉ፤ ዘንዶውና መላእክቱም መልሰው ተዋጓቸው፤ 8ነገር ግን ድል ተመቱ፤ በሰማይም የነበራቸውን ስፍራ ዐጡ። 9ታላቁ ዘንዶ፣ የጥንቱ እባብ ተጣለ፤ እርሱም ዲያብሎስ ወይም ሰይጣን ተብሎ የሚጠራው፣ ዓለምን ሁሉ የሚያስተው ነው፤ እርሱ ወደ ምድር ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።

10ከዚህ በኋላ ታላቅ ድምፅ በሰማይ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“አሁን የአምላካችን ማዳን፣ ኀይልና

መንግሥት፣

የእርሱ ክርስቶስ ሥልጣንም መጥቷል።

ቀንና ሌሊት በአምላካችን ፊት ሲከስሳቸው

የነበረው፣

የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሏልና።

11እነርሱም በበጉ ደም፣

በምስክርነታቸውም ቃል፣

ድል ነሡት፤

እስከ ሞት ድረስ እንኳ፣

ለነፍሳቸው አልሳሱም።

12ስለዚህ ሰማያት ሆይ፣

በውስጣቸውም የምትኖሩ ሆይ፣

ደስ ይበላችሁ፤

ምድርና ባሕር ግን ወዮላችሁ! ምክንያቱም ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን ብቻ

እንደ ቀረው ስላወቀ፣

በታላቅ ቍጣ ተሞልቶ ወደ እናንተ ወርዷል።”

13ዘንዶው ወደ ምድር እንደ ተጣለ ባየ ጊዜ፣ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሳደዳት። 14ሴቲቱም በበረሓ ወደ ተዘጋጀላት ስፍራ በርራ መሄድ እንድትችል ሁለት የታላቁ ንስር ክንፎች ተሰጣት፤ ይህም የሆነው በዚያ ከእባቡ ፊት ርቃ ለአንድ ዘመን፣ ለዘመናትና ለዘመን እኩሌታ በክብካቤ እንድትኖር ነው። 15እባቡም ሴቲቱ በጐርፍ እንድትወሰድ፣ እንደ ወንዝ ያለ ውሃ ከአፉ ተፋ። 16ምድር ግን ሴቲቱን ረዳቻት፤ አፏንም ከፍታ ዘንዶው ከአፉ ያፈሰሰውን ወንዝ ዋጠች። 17ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጣ፤ ከቀሩት ልጆቿም ጋር ሊዋጋ ሄደ፤ እነርሱ የእግዚአብሔርን ትእዛዞች የሚጠብቁና የኢየሱስን ምስክር አጥብቀው የያዙ ናቸው።

Slovo na cestu

Zjevení 12:1-17

Ďábel pronásleduje Krista a věřící, ale je poražen

1Na nebi se objevil nápadný úkaz: Žena oděná sluncem, s měsícem pod nohama a korunou z dvanácti hvězd na hlavě. 2Byla těhotná a sténala, protože přicházely její porodní bolesti. 3Vzápětí další úkaz na obloze: Veliký ohnivě zbarvený drak se sedmi hlavami a deseti rohy, na každé hlavě korunu. 4Ocasem smetl třetinu hvězd z nebe na zem. Postavil se před ženu a číhal, aby sežral její dítě, jakmile se narodí. 5Porodila chlapce, který má vládnout všem národům železnou rukou. Bůh však vzal to dítě a přenesl je ke svému trůnu. 6Žena utekla na poušť, kde ji Bůh ukrýval a pečoval o ni dvanáct set šedesát dní.

7V nebi se strhla bitva: Michael se svými anděly bojoval proti draku a jeho andělům. 8-9Veliký drak se svou družinou byl poražen, vyhnán z nebe a svržen na zem. To je ten dávný had z ráje, nepřítel, pomlouvač a svůdce všech lidí.

10Nebem zazněl mohutný hlas:

„Nyní se dovršilo dílo záchrany.

Bůh dokázal svoji plnou moc,

nastolil svoje království a Kristus se ujal vlády.

Je svržen žalobce,

který dnem i nocí osočoval naše bratry před Bohem.

11Zvítězili nad ním krví Krista,

Beránka obětovaného za ně,

a svým svědectvím o něm.

Nemilovali svůj život natolik,

aby se zalekli smrti.

12Jásejte nebesa! Jásejte,

vy na nebi!

Ale běda zemi a moři.

Vrhl se na vás ďábel a zuří – ví,

jak málo času mu zbývá.“

13Když se drak octl na zemi, začal pronásledovat tu ženu, která porodila toho chlapce. 14Ona však dostala orlí křídla, aby mohla uletět do pustiny, kde se před tím hadem ukrývala po tři a půl roku. 15Had vychrlil z tlamy mohutný proud vody, aby ženu smetl. 16Země jí však přišla na pomoc: otevřela své útroby a proud pohltila. 17Rozlícený drak se chtěl ženě pomstít, a tak rozpoutal boj proti jejím ostatním dětem, které zachovávají Boží přikázání a je jim svěřeno Ježíšovo poselství.