ራእይ 12 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ራእይ 12:1-17

ሴቲቱና ዘንዶው

1ታላቅና አስደናቂ ምልክት በሰማይ ታየ፤ ፀሓይን የለበሰች፣ ጨረቃን ከእግሮቿ በታች የረገጠችና በራሷም ላይ ዐሥራ ሁለት ከዋክብት ያሉት አክሊል የደፋች አንዲት ሴት ታየች። 2እርሷም ነፍሰ ጡር ነበረች፤ ልትወልድ ስትል ምጥ ይዟት ተጨንቃ ጮኸች። 3ከዚያም ሌላ ምልክት በሰማይ ታየ፤ እነሆ፤ ሰባት ራሶችና ዐሥር ቀንዶች የነበሩት፣ በራሶቹም ላይ ሰባት አክሊል የደፋ ታላቅ ቀይ ዘንዶ ታየ። 4ጅራቱ የከዋክብትን አንድ ሦስተኛ ከሰማይ ስቦ ወደ ምድር ጣላቸው፤ እርሷም በወለደች ጊዜ ልጇን ለመዋጥ ፈልጎ ዘንዶው ልትወልድ በተቃረበችው ሴት ፊት ቆመ። 5ሕዝቦችን ሁሉ በብረት በትር የሚገዛውን ወንድ ልጅ ወለደች፤ ልጇም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ። 6ሴቲቱም አንድ ሺሕ ሁለት መቶ ስድሳ ቀን ክብካቤ እንዲደረግላት እግዚአብሔር ወዳዘጋጀላት ስፍራ ወደ በረሓ ሸሸች።

7በሰማይም ጦርነት ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ከዘንዶው ጋር ተዋጉ፤ ዘንዶውና መላእክቱም መልሰው ተዋጓቸው፤ 8ነገር ግን ድል ተመቱ፤ በሰማይም የነበራቸውን ስፍራ ዐጡ። 9ታላቁ ዘንዶ፣ የጥንቱ እባብ ተጣለ፤ እርሱም ዲያብሎስ ወይም ሰይጣን ተብሎ የሚጠራው፣ ዓለምን ሁሉ የሚያስተው ነው፤ እርሱ ወደ ምድር ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።

10ከዚህ በኋላ ታላቅ ድምፅ በሰማይ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“አሁን የአምላካችን ማዳን፣ ኀይልና

መንግሥት፣

የእርሱ ክርስቶስ ሥልጣንም መጥቷል።

ቀንና ሌሊት በአምላካችን ፊት ሲከስሳቸው

የነበረው፣

የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሏልና።

11እነርሱም በበጉ ደም፣

በምስክርነታቸውም ቃል፣

ድል ነሡት፤

እስከ ሞት ድረስ እንኳ፣

ለነፍሳቸው አልሳሱም።

12ስለዚህ ሰማያት ሆይ፣

በውስጣቸውም የምትኖሩ ሆይ፣

ደስ ይበላችሁ፤

ምድርና ባሕር ግን ወዮላችሁ! ምክንያቱም ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን ብቻ

እንደ ቀረው ስላወቀ፣

በታላቅ ቍጣ ተሞልቶ ወደ እናንተ ወርዷል።”

13ዘንዶው ወደ ምድር እንደ ተጣለ ባየ ጊዜ፣ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሳደዳት። 14ሴቲቱም በበረሓ ወደ ተዘጋጀላት ስፍራ በርራ መሄድ እንድትችል ሁለት የታላቁ ንስር ክንፎች ተሰጣት፤ ይህም የሆነው በዚያ ከእባቡ ፊት ርቃ ለአንድ ዘመን፣ ለዘመናትና ለዘመን እኩሌታ በክብካቤ እንድትኖር ነው። 15እባቡም ሴቲቱ በጐርፍ እንድትወሰድ፣ እንደ ወንዝ ያለ ውሃ ከአፉ ተፋ። 16ምድር ግን ሴቲቱን ረዳቻት፤ አፏንም ከፍታ ዘንዶው ከአፉ ያፈሰሰውን ወንዝ ዋጠች። 17ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጣ፤ ከቀሩት ልጆቿም ጋር ሊዋጋ ሄደ፤ እነርሱ የእግዚአብሔርን ትእዛዞች የሚጠብቁና የኢየሱስን ምስክር አጥብቀው የያዙ ናቸው።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

התגלות 12:1-17

1עתה נראה בשמים חזיון נבואי מסתורי: אישה לבושה בשמש, הירח תחת רגליה ועל ראשה כתר בעל שנים־עשר כוכבים, 2כרעה ללדת וזעקה מכאבים וצירי לידה.

3לפתע הופיע תנין גדול שצבעו אדום כאש, בעל שבעה ראשים, עשר קרניים ועל ראשיו שבעה כתרים. 4בזנבו גרר אחריו התנין שליש מכוכבי השמים והשליכם ארצה. הוא עמד לפני האישה הכורעת ללדת, מוכן לבלוע את התינוק מיד עם הולדתו.

5האישה ילדה בן זכר שנועד לשלוט ביד חזקה על כל העמים. מיד נלקח הבן אל האלוהים ואל כיסאו, 6ואילו האישה ברחה אל המדבר, שם הכין לה אלוהים מקום מבטחים וכלכלה למשך 1260 יום.

7לאחר מכן פרצה מלחמה בשמים; מיכאל ומלאכיו נלחמו נגד התנין ומלאכיו הרעים. 8התנין ומלאכיו הובסו בקרב וגורשו מהשמים. 9התנין הנורא הזה – הנחש הקדמוני שנקרא מלשין ושטן, והמתעה את העולם כולו – הושלך ארצה עם מלאכיו.

10ואז שמעתי קול אדיר בשמים: ”סוף־סוף הגיעה ישועת אלוהים! אכן, גבורת אלוהים, מלכותו וסמכות משיחו הגיעו, כי השטן אשר קטרג על אחינו לפני אלוהים, יומם ולילה, הושלך ארצה! 11הם ניצחוהו בדם השה ובעדותם הנאמנה, כי לא חסו על חייהם והיו מוכנים להקריב את עצמם למוות.

12”על כן שמחו שמים והשוכנים בהם! אך אוי לכם יושבי הארץ, כי השטן ירד אליכם בזעם גדול ובידיעה שזמנו קצר!“

13כאשר נוכח התנין כי הושלך ארצה, רדף אחרי האישה שילדה את בן הזכר.

14אולם לאישה ניתן זוג כנפי־נשר ענק כדי שתעוף אל המדבר, אל המקום שהוכן למענה. שם, הרחק מהנחש, מהתנין, יסופק לה כל מחסורה לתקופה של שלוש שנים וחצי.

15הנחש, שהמשיך לרדוף אחרי האישה, הוציא מפיו נהר מים שזרם לעבר האישה בניסיון להטביעה, 16אך הארץ באה לעזרת האישה; האדמה פתחה את פיה ובלעה את המים! 17והתנין, מרוגז מאוד על האישה, הלך להילחם נגד שאר ילדיה – הלא הם כל אלה ששומרים את דבר אלוהים ומעידים על ישוע המשיח. (התנין עמד על חוף הים והמתין).