ራእይ 1 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ራእይ 1:1-20

1ቶሎ መሆን የሚገባውን ነገር ለአገልጋዮቹ እንዲያሳይ፣ እግዚአብሔር ለእርሱ የሰጠው የኢየሱስ ክርስቶስ ራእይ ይህ ነው፤ ኢየሱስም መልአኩን ልኮ ለአገልጋዩ ለዮሐንስ ገለጠለት፤ 2እርሱም ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምስክርነት ያየውን ሁሉ መሰከረ። 3ዘመኑ ቀርቧል፤ እንግዲህ ይህን የትንቢት ቃል የሚያነብብ ብፁዕ ነው፤ የሚሰሙትና የተጻፈውንም የሚጠብቁ ብፁዓን ናቸው።

ሰላምታና ውዳሴ

4ከዮሐንስ፤

በእስያ አውራጃ ለሚገኙ ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት፤

ካለው፣ ከነበረውና ከሚመጣው፣ በዙፋኑም ፊት ካሉት ከሰባቱ መናፍስት፣1፥4 ወይም ሰባት ዕጥፍ መንፈስ 5እንዲሁም ታማኝ ምስክር፣ ከሙታን በኵርና የምድር ነገሥታት ገዥ ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስም ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።

ለወደደንና ከኀጢአታችንም በደሙ ነጻ ላወጣን፣ 6አምላኩንና አባቱን እንድናገለግልም መንግሥትና ካህናት ላደረገን፣ ለእርሱ ክብርና ኀይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ይሁን! አሜን።

7እነሆ፤ በደመና ይመጣል፤

የወጉት እንኳ ሳይቀሩ፣

ዐይን ሁሉ ያየዋል፤

የምድርም ሕዝቦች ሁሉ ከእርሱ የተነሣ ዋይ ዋይ ይላሉ።

አዎ! ይህ ሁሉ ይሆናል፤ አሜን።

8“ያለውና የነበረው፣ የሚመጣውም፣ ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ፣ አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ” ይላል።

የሰውን ልጅ የሚመስለው

9እኔ ወንድማችሁ ዮሐንስ፣ ከእናንተ ጋር አብሬ በኢየሱስ መከራውንና መንግሥቱን፣ ትዕግሥቱንም ተካፋይ የሆንሁ፣ ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ኢየሱስ ምስክርነት ፍጥሞ በምትባል ደሴት ነበርሁ። 10በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርሁ፤ የመለከትን ድምፅ የሚመስል ታላቅ ድምፅ ከበስተ ኋላዬ ሰማሁ፤ 11ድምፁም፣ “የምታየውን በጥቅልል መጽሐፍ ጽፈህ በኤፌሶን፣ በሰምርኔስ፣ በጴርጋሞን፣ በትያጥሮን፣ በሰርዴስ፣ በፊላድልፍያና በሎዶቅያ ወደሚገኙት ወደ ሰባቱ የእስያ አብያተ ክርስቲያናት ላክ” አለ።

12እኔም የሚናገረኝን ድምፅ ለማየት ዞር አልሁ፤ ዞር ባልሁም ጊዜ ሰባት የወርቅ መቅረዞችን አየሁ፤ 13በመቅረዞቹም መካከል “የሰው ልጅ የሚመስል” አየሁ፤ እርሱም እስከ እግሩ የሚደርስ መጐናጸፊያ የለበሰ፣ ደረቱንም በወርቅ መታጠቂያ የታጠቀ ነበር። 14ራሱና ጠጕሩም እንደ ነጭ የበግ ጠጕር፣ እንደ በረዶም ነጭ ነበሩ፤ ዐይኖቹም የእሳት ነበልባል ይመስሉ ነበር። 15እግሮቹ በእቶን እሳት የጋለ ናስ ይመስሉ ነበር፤ ድምፁም እንደ ብዙ ወራጅ ውሃ ድምፅ ነበረ። 16በቀኝ እጁ ሰባት ከዋክብት ይዞ ነበር፤ ከአፉም በሁለት በኩል የተሳለ ሰይፍ ይወጣ ነበር፤ ፊቱም በሙሉ ድምቀቱ እንደሚያበራ ፀሓይ ነበረ።

17ባየሁት ጊዜ እንደ ሞተ ሰው ሆኜ በእግሩ ሥር ወደቅሁ። እርሱም ቀኝ እጁን በላዬ ጭኖ እንዲህ አለኝ፤ “አትፍራ፤ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም እኔ ነኝ፤ 18እኔ ሕያው ነኝ፤ ሞቼ ነበር፤ እነሆ፤ አሁን ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፤ የሞትና የሲኦል መክፈቻም በእጄ ነው።

19“ስለዚህ ያየኸውን፣ አሁን ያለውንና በኋላም የሚሆነውን ጻፍ። 20በቀኝ እጄ ያየሃቸው የሰባቱ ከዋክብትና የሰባቱ የወርቅ መቅረዞች ምስጢር ይህ ነው፤ ሰባቱ ከዋክብት የሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት መላእክት1፥20 ወይም መልእክተኞች ናቸው፤ ሰባቱ መቅረዞች ደግሞ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው።

Knijga O Kristu

Otkrivenje 1:1-20

Uvod

1Ovo je otkrivenje Isusa Krista, koje mu je Bog dao da pokaže svojim slugama što se ima uskoro dogoditi. Bog je poslao anđela svojemu sluzi Ivanu da bi mogao otkrivenje prenijeti drugima. 2Ivan izvješćuje o Božjoj riječi i svjedočanstvu Isusa Krista—o svemu što je vidio.

3Blago onome koji čita ovo proroštvo i onima koji slušaju njegove riječi te vrše što je u njemu napisano. Jer vrijeme kad će se ono ispuniti je blizu.

Ivan pozdravlja sedam crkava

4Ovo pismo piše Ivan sedmerim crkvama u Maloj Aziji. Neka vam je milost i mir od onoga koji jest, koji je oduvijek bio i koji će doći; od sedam duhova pred njegovim prijestoljem 5te od Isusa Krista koji vjerno svjedoči o tomu, koji je prvi ustao od mrtvih i vladar je nad svim zemaljskim kraljevima.

Neka je slava njemu koji nas ljubi i koji nas je oslobodio od grijeha prolivši za nas svoju krv. 6Učinio nas je kraljevstvom i svećenstvom Boga, svojega Oca. Neka mu je slava i vlast uvijeke! On vlada zauvijek. Amen.

7Gle! On dolazi s oblacima nebeskim. I vidjet će ga svi, čak i oni koji su ga proboli. Svi će narodi na zemlji proplakati zbog njega. Da. Amen.

8“Ja sam Alfa i Omega, Početak i Svršetak”, kaže Gospodin Bog. “Ja sam Svemogući, onaj koji jest, koji je oduvijek bio i koji će doći.”

Viđenje Sina Čovječjega

9Ja, Ivan, vaš brat, kao i vi u Kristu sam dionik patnji i kraljevstva te postojanosti. Izgnan sam na otok Patmos zbog propovijedanja Božje riječi i svjedočenja o Isusu. 10Bio je Dan Gospodnji. Ponio me Duh i odjednom sam iza sebe začuo glas snažan poput zvuka trublje. 11“Zapiši što ti kažem”, reče mi glas, “i pošalji sedmerim crkvama: u Efez, Smirnu, Pergam, Tijatiru, Sard, Filadelfiju i Laodiceju.”

12Okrenem se da vidim tko mi govori, ali ugledam sedam zlatnih svijećnjaka, 13a među svijećnjacima nekoga sličnog čovjeku.1:13 U grčkome: sličnoga sinu čovječjemu. Ne odnosi se na Isusa Krista, već znači sličan ljudskome biću, čovjeku. Bio je odjeven u dugu haljinu, sa zlatnim pasom oko prsa. 14Kosa mu je bila bijela poput bijele vune, poput snijega, oči kao ognjeni plamen, 15noge sjajne poput mjedi u peći užarene, a glas poput šuma golemih morskih valova. 16U desnoj je ruci držao sedam zvijezda, a u ustima oštar dvosjekli mač. Lice mu je blistalo poput sunca u punome sjaju.

17Kad sam ga opazio, pao sam do njegovih nogu kao mrtav. Ali on stavi na mene desnu ruku i reče mi: “Ne boj se! Ja sam Prvi i Posljednji. 18Živ sam! Bio sam mrtav, ali živim zauvijek. Imam ključeve smrti i podzemlja. 19Zapiši što si vidio: što se sada događa i što će se dogoditi poslije. 20Evo što znače sedam zvijezda koje si vidio u mojoj desnoj ruci i sedam zlatnih svijećnjaka: sedam su zvijezda anđeli1:20 Ili: glasnici. sedam crkava, a sedam svijećnjaka sedam crkava.