ምሳሌ 8 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 8:1-36

የጥበብ ጥሪ

1ጥበብ ጮኻ አትጣራምን?

ማስተዋልስ ድምፅዋን ከፍ አድርጋ አታሰማምን?

2በመንገድ አጠገብ ባሉ ኰረብቶች፣

መንገዶቹ በሚገናኙበትም ላይ ትቆማለች፤

3ወደ ከተማዪቱ በሚያስገቡት በሮች አጠገብ፣

በመግቢያዎቹ ላይ፣ ድምፅዋን ከፍ አድርጋ እንዲህ ስትል ትጮኻለች፤

4“ሰዎች ሆይ፤ የምጠራው እኮ እናንተን ነው፤

ለሰው ልጆች ሁሉ ድምፄን ከፍ አደርጋለሁ።

5እናንተ ብስለት የጐደላችሁ፤ ጠንቃቃነትን ገንዘብ አድርጉ፤

እናንተ ተላሎች፤ ማስተዋልን አትርፉ።

6የምናገረው ጠቃሚ ነገር ስላለኝ አድምጡኝ፤

ቀና ነገር ለመናገር ከንፈሮቼን እከፍታለሁ።

7አንደበቴ እውነትን ይናገራል፤

ከንፈሮቼ ክፋትን ይጸየፋሉና።

8ከአንደበቴ የሚወጡት ቃሎች ሁሉ ጽድቅ ናቸው፤

አንዳቸውም ጠማማና ግራ የሚያጋቡ አይደሉም።

9በጥልቅ ለሚያስተውሉ ሁሉም ቀና ናቸው፤

ዕውቀት ላላቸውም ስሕተት የለባቸውም።

10ከብር ይልቅ ምክሬን፣

ከንጹሕ ወርቅ ይልቅ ዕውቀትን ምረጡ፤

11ጥበብ ከቀይ ዕንይበልጥ ውድ ናትና፤

ከምትመኙት ነገር ሁሉ አንዳች የሚስተካከላት የለም።

12“እኔ ጥበብ ከማስተዋል ጋር አብሬ እኖራለሁ፤

ዕውቀትና ልባምነት ገንዘቦቼ ናቸው።

13እግዚአብሔርን መፍራት ክፋትን መጥላት ነው፤

እኔም ትዕቢትንና እብሪትን፣

ክፉ ጠባይንና ጠማማ ንግግርን እጠላለሁ።

14ምክርና ትክክለኛ ፍርድ የእኔ ናቸው፤

ማስተዋል አለኝ፤ ብርታት አለኝ።

15ነገሥታት በእኔ ይነግሣሉ፤

ገዦችም ትክክል የሆነውን ሕግ ይደነግጋሉ፤

16መሳፍንት በእኔ ይገዛሉ፤

በምድር ላይ የሚገዙ መኳንንትም ሁሉ በእኔ ያስተዳድራሉ።8፥16 አያሌ የዕብራይስጥ ቅጆችና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ ብዙ የዕብራይስጥ ቅጆች በምድር ላይ በጽድቅ የሚገዙ ይላሉ።

17የሚወድዱኝን እወድዳቸዋለሁ፤

ተግተው የሚሹኝም ያገኙኛል።

18ሀብትና ክብር፣

ዘላቂ ብልጽግናና ስኬት በእኔ ዘንድ አሉ።

19ፍሬዬ ከንጹሕ ወርቅ ይበልጣል፤

ስጦታዬም ከነጠረ ብር።

20እኔ በጽድቅ መንገድ እሄዳለሁ፤

በፍትሕም ጐዳና እጓዛለሁ፤

21ለሚወድዱኝ ብልጽግና እሰጣለሁ፤

ግምጃ ቤታቸውንም እሞላለሁ።

22እግዚአብሔር ከቀድሞ ሥራዎቹ በፊት፣

የተግባሮቹ8፥22 ወይም የመንገዱ፣ የግዛቱ መጀመሪያ አድርጎ አመጣኝ፤8፥22 ወይም እግዚአብሔር በሥራው መጀመሪያ ያዘኝ ወይም እግዚአብሔር በሥራው መጀመሪያ አመጣኝ

23ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ፣

ከጥንት ከዘላለም ተሾምሁ።8፥23 ወይም ተሠራ?

24ከውቅያኖሶች በፊት፣

የውሃ ምንጮች ከመፍለቃቸው በፊት ተወለድሁ፤

25ተራሮች ገና ሳይመሠረቱ፣

ከኰረብቶችም በፊት ተወለድሁ፤

26ምድርን ወይም ሜዳዎቿን፣

ወይም ምንም ዐይነት የዓለም ትቢያን ከመፍጠሩ በፊት እኔ ተወለድሁ።

27ሰማያትን በዘረጋ ጊዜ፣

በውቅያኖስ ላይ የአድማስ ምልክት ባደረገ ጊዜ እኔ እዚያ ነበርሁ፤

28ደመናትን በላይ ባጸና ጊዜ፣

የውቅያኖስን ምንጮች በመሠረተ ጊዜ፣

29ለባሕር ድንበርን በከለለ ጊዜ፣

ውሆችም የእርሱን ትእዛዝ እንዳያልፉ፣

የምድርንም መሠረቶች ወሰን ባበጀ ጊዜ፣

30በዚያን ጊዜ ከጐኑ ዋና ባለሙያ ነበርሁ።

ሁልጊዜ በፊቱ ሐሤት እያደረግሁ፣

ዕለት ተዕለት በደስታ እሞላ ነበር፤

31የእርሱ በሆነው መላው ዓለም ሐሤት እያደረግሁ፣

በሰው ልጆች ደስ እሰኝ ነበር።

32“እንግዲህ፣ ልጆቼ ሆይ፤ አድምጡኝ፤

መንገዴን የሚጠብቁ ቡሩካን ናቸው።

33ምክሬን አድምጡ፤ ጥበበኞች ሁኑ፤

ቸልም አትበሉት።

34በየዕለቱ ደጃፌ ላይ የሚጠብቅ፣

በበራፌ ላይ የሚጠባበቅ፣

የሚያዳምጠኝ ሰው ቡሩክ ነው።

35የሚያገኘኝ ሁሉ ሕይወትን ያገኛልና፤

ከእግዚአብሔርም ዘንድ ሞገስን ይቀበላል።

36የሚያጣኝ ሁሉ ግን ራሱ ይጐዳል፤

የሚጠሉኝም ሁሉ ሞትን ይወድዳሉ።”

Persian Contemporary Bible

امثال 8:1-36

ندای حكمت

1آيا ندای حكمت را نمی‌شنويد؟ 2‏-3حكمت دم دروازه‌های شهر و سر چهارراه‌ها و جلو در هر خانه‌ای ايستاده، می‌گويد: 4‏-5«ای انسانهای جاهل و نادان به ندای من گوش دهيد و زيركی و فهم كسب كنيد. 6‏-7به من گوش دهيد، زيرا سخنان من گرانبهاست. من حقيقت و راستی را بيان می‌كنم و از ناراستی نفرت دارم. 8سخنان من بر حق است و كسی را گمراه نمی‌كند. 9حرفهای من برای كسی كه گوش شنوا داشته باشد واضح و روشن است. 10تعليمی كه من می‌دهم از طلا و نقره گرانبهاتر است. 11ارزش من از ياقوت بيشتر است و هيچ چيز را نمی‌توان با من مقايسه كرد. 12من حكمتم و از زيركی و دانايی و بصيرت برخوردار می‌باشم. 13اگر كسی خداترس باشد، از بدی نفرت خواهد داشت. من از غرور و تكبر، رفتار و گفتار نادرست متنفرم.

14‏-15«من هدايت می‌كنم و فهم و بصيرت می‌بخشم. به نيروی من پادشاهان سلطنت می‌كنند و قضات به عدل و انصاف قضاوت می‌نمايند. 16تمام رهبران و بزرگان جهان به كمک من حكمرانی می‌كنند. 17من كسانی را كه مرا دوست دارند، دوست دارم. آنانی كه در جستجوی من باشند مرا خواهند يافت. 18ثروت و حرمت، اموال و موفقيت در اختيار من است. 19بخشش‌های من از طلای ناب و نقرهٔ خالص بهتر است. 20راههای من عدل و حق است. 21ثروت حقيقی از آن كسانی است كه مرا دوست دارند، زيرا من خزانه‌های ايشان را پر می‌سازم.

22«خداوند در ابتدا، قبل از آفرينش عالم هستی، مرا با خود داشت. 23از ازل، پيش از به وجود آمدن جهان من به وجود آمدم. 24قبل از پيدايش اقيانوسها و چشمه‌های پر آب، 25قبل از آنكه كوهها و تپه‌ها به وجود آيند، 26قبل از آنكه خدا زمين و صحراها و حتی خاک را بيافريند من به وجود آمدم.

27«وقتی خدا آسمان را استوار ساخت و افق را بر سطح آبها كشيد من آنجا بودم. 28وقتی ابرها را در آسمان گسترانيد و چشمه‌ها را از اعماق جاری نمود، 29وقتی حدود درياها را تعيين كرد تا آبها از آن تجاوز نكنند و وقتی اساس زمين را بنياد نهاد، 30من نزد او معمار بودم. موجب شادی هميشگی او بودم و در حضورش شادی می‌كردم. 31دنيا و انسانهايی كه او آفريده بود مايهٔ خوشی من بودند. 32پس ای جوانان به من گوش دهيد، زيرا همهٔ كسانی كه از دستورات من پيروی می‌كنند سعادتمندند.

33«به نصيحت من گوش كنيد؛ عاقل باشيد و نصيحت مرا رد نكنيد. 34خوشا به حال كسی كه به من گوش دهد و هر روز جلو در خانهٔ من انتظار مرا بكشد، 35زيرا هر كه مرا بيابد حيات را يافته و خداوند را خشنود ساخته است؛ 36اما كسی كه مرا از دست بدهد به جانش لطمه می‌زند، آنانی كه از من متنفر باشند مرگ را دوست دارند.»