ምሳሌ 31 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 31:1-31

ንጉሥ ልሙኤል የተናገራቸው ምሳሌዎች

1ንጉሥ ልሙኤልን እናቱ ያስተማረችው ቃል ይህ ነው፤

2“ልጄ ሆይ፤ የማሕፀኔ ልጅ ሆይ፤

የስእለቴ ልጅ ሆይ፤31፥2 ወይም የጸሎቴ መልስ ሆይ

3ጕልበትህን በሴት አትጨርስ፤

ብርታትህንም ነገሥታትን ለሚያጠፉ አታውል።

4“ልሙኤል ሆይ፤ ነገሥታት ይህን ማድረግ የለባቸውም፤

ነገሥታት የወይን ጠጅ ሊጠጡ፣

ገዦችም የሚያሰክር መጠጥ ሊያስጐመጃቸው አይገባም፤

5አለዚያ ጠጥተው የሕጉን ድንጋጌ ይረሳሉ፤

የተጨቈኑትን ሁሉ መብት ይገፍፋሉ።

6ለሚጠፉት የሚያሰክር መጠጥ፣

በሥቃይ ላሉትም የወይን ጠጅ ስጧቸው፤

7ጠጥተው ድኽነታቸውን ይርሱ፤

ችግራቸውንም ከእንግዲህ አያስቡ።

8“ስለ ራሳቸው መናገር ለማይችሉት፣

ለችግረኞችም ሁሉ መብት ተሟገት።

9ተናገር፤ በቅንነትም ፍረድ፤

የምስኪኖችንና የድኾችን መብት አስከብር።”

መዝጊያ ክፍል፤ ጠባየ መልካም ሚስት

10ጠባየ መልካምን ሚስት ማን ያገኛታል?31፥10 ከ10-31 ያለው እያንዳንዱ ቍጥር የሚጀምረው በዕብራይስጡ ሆህያት ቅደም ተከተል መሠረት ነው።

ከቀይ ዕንእጅግ ትበልጣለች።

11ባሏ ሙሉ በሙሉ ይተማመንባታል፤

የሚጐድልበትም ነገር የለም።

12በሕይወት ዘመኗ ሁሉ፣

መልካም ታደርግለታለች እንጂ አትጐዳውም።

13የበግ ጠጕርና የተልባ እግር መርጣ፣

ሥራ በሚወዱ እጆቿ ትፈትላቸዋለች።

14እንደ ንግድ መርከብ፣

ምግቧን ከሩቅ ትሰበስባለች።

15ገና ሳይነጋ ትነሣለች፤

ለቤተ ሰቧ ምግብ፣

ለሴት አገልጋዮቿም ድርሻቸውን ትሰጣለች።

16ራሷ አስባ የዕርሻ መሬት ትገዛለች፤

በምታገኘውም ገንዘብ ወይን ትተክላለች።

17ብርታትን ታጥቃ ሥራዋን ታከናውናለች፤

ክንዶቿም ለሥራ ብርቱ ናቸው።

18ሥራዋ ትርፋማ መሆኑን ታስተውላለች፤

በሌሊትም መብራቷ አይጠፋም።

19በእጇ እንዝርት ትይዛለች፤

በጣቶቿም ዘንጉን ታሾራለች።

20ክንዶቿን ለድኾች ትዘረጋለች፣

እጆቿንም ለችግረኞች ፈታ ታደርጋለች።

21በረዶ ቢጥል ለቤተ ሰዎቿ አትሠጋም፤

ሁሉም ቀይ ልብስ ለብሰዋልና።

22ለመኝታዋ የዐልጋ ልብስ ትሠራለች፤

ቀጭን በፍታና ሐምራዊ ልብስ ለብሳለች።

23ባሏ በአገር ሽማግሌዎች መካከል

በአደባባይ በተቀመጠ ጊዜ የተከበረ ነው።

24የበፍታ መጐናጸፊያዎችን ሠርታ ትሸጣለች፤

ለነጋዴዎችም ድግ ታቀርባለች።

25ብርታትንና ሞገስን ተጐናጽፋለች፤

መጭውን ጊዜ በደስታ ትቀበላለች።

26በጥበብ ትናገራለች፤

በአንደበቷም ቀና ምክር አለ።

27የቤተ ሰቦቿን ጕዳይ በትጋት ትከታተላለች፤

የስንፍና እንጀራ አትበላም።

28ልጆቿ ተነሥተው ቡርክት ይሏታል፤

ባሏም እንዲሁ፣ ሲያመሰግናትም እንዲህ ይላል፤

29“ብዙ ሴቶች መልካም አድርገዋል፤

አንቺ ግን ሁሉንም ትበልጫለሽ።”

30ቍንጅና አታላይ ነው፤ ውበትም ይረግፋል፤

እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን የተመሰገነች ናት።

31የሚገባትን ሽልማት ስጧት፤

ሥራዋም በየአደባባዩ ያስመስግናት።

Thai New Contemporary Bible

สุภาษิต 31:1-31

คำสอนของกษัตริย์เลมูเอล

1นี่คือคำสอนของกษัตริย์เลมูเอล เป็นถ้อยคำที่ได้รับการดลใจ31:1 หรือเลมูเอลแห่งมัสสาซึ่งมารดาของพระองค์ทรงสอนไว้

2“ฟังให้ดี ลูกของแม่ ฟังให้ดี ลูกจากครรภ์ของแม่!

ฟังให้ดี ลูกของแม่ ผู้เป็นคำตอบคำอธิษฐานของแม่!

3อย่าเสียแรงกับเหล่าอิสตรี31:3 หรือทรัพย์สิน

อย่าเสียกำลังให้แก่บรรดาผู้ที่ทำลายกษัตริย์

4“เลมูเอลเอ๋ย มันไม่เหมาะสำหรับกษัตริย์ ไม่เหมาะสำหรับกษัตริย์ที่จะดื่มเหล้าองุ่น

ไม่เหมาะสำหรับชนชั้นปกครองที่จะกระหายหาของมึนเมา

5เพราะเมื่อดื่มแล้ว จะลืมสิ่งที่ตราไว้ในตัวบทกฎหมาย

และจะเปลี่ยนบทบัญญัติทำให้ผู้ที่ถูกกดขี่ข่มเหงเดือดร้อน

6สุรามีไว้ให้คนที่กำลังพินาศ

เหล้าองุ่นมีไว้เพื่อผู้ที่ทุกข์ใจ

7ให้เขาดื่มจะได้ลืมความอับจน

และไม่นึกถึงทุกข์เข็ญของตนอีก

8“จงเป็นปากเป็นเสียงให้ผู้ที่ไม่อาจปริปากเพื่อตนเอง

เพื่อสิทธิ์ของผู้ที่สิ้นไร้ไม้ตอก

9จงเป็นปากเป็นเสียงให้พวกเขาและตัดสินอย่างยุติธรรม

จงออกบทบัญญัติเพื่อประโยชน์ของผู้ยากไร้และขัดสน”

บทส่งท้าย

1031:10-31 ในภาษาฮีบรู แต่ละข้อขึ้นต้นด้วยตัวอักษรฮีบรูเรียงตามลำดับใครจะพบภรรยาที่ดีเลิศ?

นางล้ำค่ายิ่งกว่าทับทิมมากนัก

11สามีของนางไว้ใจนางอย่างเต็มที่

และไม่ขาดสิ่งล้ำค่าอันใดเลย

12นางนำสิ่งดีมาสู่เขาไม่ใช่สิ่งร้าย

ตลอดวันเวลาของนาง

13นางเลือกหาขนสัตว์และใยป่าน

และสองมือทำงานอย่างขยันขันแข็ง

14นางเป็นดั่งเรือสินค้า

ที่บรรทุกอาหารมาจากแดนไกล

15นางตื่นขึ้นตั้งแต่ก่อนรุ่งสาง

เพื่อจัดเตรียมอาหารสำหรับคนในครัวเรือน

และแบ่งอาหารให้บรรดาสาวใช้

16นางออกไปสำรวจไร่นาแล้วซื้อไว้

และลงทุนทำสวนองุ่นด้วยเงินที่นางหามาได้

17นางทำงานอย่างขยันขันแข็ง

แขนของนางแข็งแกร่งสู้งานต่างๆ

18นางดูแลกิจการให้ผลกำไรงอกเงย

และกลางคืนตะเกียงของนางก็ไม่ดับ

19มือของนางจับไน

นิ้วของนางจับกระสวย

20นางหยิบยื่นให้คนยากจน

และยื่นมือช่วยคนขัดสน

21เมื่อหิมะตก นางไม่วิตกกังวลเกี่ยวกับคนในครัวเรือน

เพราะทุกคนสวมเสื้อผ้าอย่างดีและอบอุ่น31:21 ภาษาฮีบรูว่าเพราะทุกคนสวมเสื้อผ้าสีแดง

22นางทำผ้าปูที่นอนเอง

เสื้อผ้าของนางทำด้วยผ้าลินินเนื้อดีและผ้าขนสัตว์สีม่วงราคาแพง

23สามีของนางเป็นที่นับหน้าถือตาที่ประตูเมือง

ที่ซึ่งเขานั่งอยู่ในหมู่ผู้อาวุโสของแผ่นดิน

24นางยังได้ทำเครื่องนุ่งห่มด้วยผ้าลินินไว้ขาย

และส่งผ้าคาดเอวให้แก่พ่อค้า

25พลังและศักดิ์ศรีคืออาภรณ์ที่นางสวม

ดังนั้นนางจึงหัวเราะกับอนาคตที่จะมาถึงได้

26ปากของนางเอื้อนเอ่ยสติปัญญา

ลิ้นของนางสอนสิ่งดีงาม

27นางคอยดูแลกิจการทั้งสิ้นในครัวเรือน

และไม่เคยเกียจคร้าน

28ลูกๆ ของนางยืนขึ้นกล่าวยกย่อง

สามีของนางก็ชมเชยนางว่า

29“สตรีจำนวนมากทำสิ่งดีเลิศ

แต่เธอล้ำเลิศยิ่งกว่าพวกเขาทั้งหมด”

30เสน่ห์เป็นสิ่งหลอกลวง และความสวยงามไม่จีรังยั่งยืน

แต่สตรีที่ยำเกรงองค์พระผู้เป็นเจ้าจะได้รับการสรรเสริญ

31จงยกย่องนางเพราะทุกสิ่งที่นางทำ

ให้ประชาชนที่ประตูเมืองสรรเสริญนางเพราะการงานของนาง