ምሳሌ 31 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 31:1-31

ንጉሥ ልሙኤል የተናገራቸው ምሳሌዎች

1ንጉሥ ልሙኤልን እናቱ ያስተማረችው ቃል ይህ ነው፤

2“ልጄ ሆይ፤ የማሕፀኔ ልጅ ሆይ፤

የስእለቴ ልጅ ሆይ፤31፥2 ወይም የጸሎቴ መልስ ሆይ

3ጕልበትህን በሴት አትጨርስ፤

ብርታትህንም ነገሥታትን ለሚያጠፉ አታውል።

4“ልሙኤል ሆይ፤ ነገሥታት ይህን ማድረግ የለባቸውም፤

ነገሥታት የወይን ጠጅ ሊጠጡ፣

ገዦችም የሚያሰክር መጠጥ ሊያስጐመጃቸው አይገባም፤

5አለዚያ ጠጥተው የሕጉን ድንጋጌ ይረሳሉ፤

የተጨቈኑትን ሁሉ መብት ይገፍፋሉ።

6ለሚጠፉት የሚያሰክር መጠጥ፣

በሥቃይ ላሉትም የወይን ጠጅ ስጧቸው፤

7ጠጥተው ድኽነታቸውን ይርሱ፤

ችግራቸውንም ከእንግዲህ አያስቡ።

8“ስለ ራሳቸው መናገር ለማይችሉት፣

ለችግረኞችም ሁሉ መብት ተሟገት።

9ተናገር፤ በቅንነትም ፍረድ፤

የምስኪኖችንና የድኾችን መብት አስከብር።”

መዝጊያ ክፍል፤ ጠባየ መልካም ሚስት

10ጠባየ መልካምን ሚስት ማን ያገኛታል?31፥10 ከ10-31 ያለው እያንዳንዱ ቍጥር የሚጀምረው በዕብራይስጡ ሆህያት ቅደም ተከተል መሠረት ነው።

ከቀይ ዕንእጅግ ትበልጣለች።

11ባሏ ሙሉ በሙሉ ይተማመንባታል፤

የሚጐድልበትም ነገር የለም።

12በሕይወት ዘመኗ ሁሉ፣

መልካም ታደርግለታለች እንጂ አትጐዳውም።

13የበግ ጠጕርና የተልባ እግር መርጣ፣

ሥራ በሚወዱ እጆቿ ትፈትላቸዋለች።

14እንደ ንግድ መርከብ፣

ምግቧን ከሩቅ ትሰበስባለች።

15ገና ሳይነጋ ትነሣለች፤

ለቤተ ሰቧ ምግብ፣

ለሴት አገልጋዮቿም ድርሻቸውን ትሰጣለች።

16ራሷ አስባ የዕርሻ መሬት ትገዛለች፤

በምታገኘውም ገንዘብ ወይን ትተክላለች።

17ብርታትን ታጥቃ ሥራዋን ታከናውናለች፤

ክንዶቿም ለሥራ ብርቱ ናቸው።

18ሥራዋ ትርፋማ መሆኑን ታስተውላለች፤

በሌሊትም መብራቷ አይጠፋም።

19በእጇ እንዝርት ትይዛለች፤

በጣቶቿም ዘንጉን ታሾራለች።

20ክንዶቿን ለድኾች ትዘረጋለች፣

እጆቿንም ለችግረኞች ፈታ ታደርጋለች።

21በረዶ ቢጥል ለቤተ ሰዎቿ አትሠጋም፤

ሁሉም ቀይ ልብስ ለብሰዋልና።

22ለመኝታዋ የዐልጋ ልብስ ትሠራለች፤

ቀጭን በፍታና ሐምራዊ ልብስ ለብሳለች።

23ባሏ በአገር ሽማግሌዎች መካከል

በአደባባይ በተቀመጠ ጊዜ የተከበረ ነው።

24የበፍታ መጐናጸፊያዎችን ሠርታ ትሸጣለች፤

ለነጋዴዎችም ድግ ታቀርባለች።

25ብርታትንና ሞገስን ተጐናጽፋለች፤

መጭውን ጊዜ በደስታ ትቀበላለች።

26በጥበብ ትናገራለች፤

በአንደበቷም ቀና ምክር አለ።

27የቤተ ሰቦቿን ጕዳይ በትጋት ትከታተላለች፤

የስንፍና እንጀራ አትበላም።

28ልጆቿ ተነሥተው ቡርክት ይሏታል፤

ባሏም እንዲሁ፣ ሲያመሰግናትም እንዲህ ይላል፤

29“ብዙ ሴቶች መልካም አድርገዋል፤

አንቺ ግን ሁሉንም ትበልጫለሽ።”

30ቍንጅና አታላይ ነው፤ ውበትም ይረግፋል፤

እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን የተመሰገነች ናት።

31የሚገባትን ሽልማት ስጧት፤

ሥራዋም በየአደባባዩ ያስመስግናት።

New International Version – UK

Proverbs 31:1-31

Sayings of King Lemuel

1The sayings of King Lemuel – an inspired utterance his mother taught him.

2Listen, my son! Listen, son of my womb!

Listen, my son, the answer to my prayers!

3Do not spend your strength31:3 Or wealth on women,

your vigour on those who ruin kings.

4It is not for kings, Lemuel –

it is not for kings to drink wine,

not for rulers to crave beer,

5lest they drink and forget what has been decreed,

and deprive all the oppressed of their rights.

6Let beer be for those who are perishing,

wine for those who are in anguish!

7Let them drink and forget their poverty

and remember their misery no more.

8Speak up for those who cannot speak for themselves,

for the rights of all who are destitute.

9Speak up and judge fairly;

defend the rights of the poor and needy.

Epilogue: the wife of noble character

1031:10 Verses 10-31 are an acrostic poem, the verses of which begin with the successive letters of the Hebrew alphabet. A wife of noble character who can find?

She is worth far more than rubies.

11Her husband has full confidence in her

and lacks nothing of value.

12She brings him good, not harm,

all the days of her life.

13She selects wool and flax

and works with eager hands.

14She is like the merchant ships,

bringing her food from afar.

15She gets up while it is still night;

she provides food for her family

and portions for her female servants.

16She considers a field and buys it;

out of her earnings she plants a vineyard.

17She sets about her work vigorously;

her arms are strong for her tasks.

18She sees that her trading is profitable,

and her lamp does not go out at night.

19In her hand she holds the distaff

and grasps the spindle with her fingers.

20She opens her arms to the poor

and extends her hands to the needy.

21When it snows, she has no fear for her household;

for all of them are clothed in scarlet.

22She makes coverings for her bed;

she is clothed in fine linen and purple.

23Her husband is respected at the city gate,

where he takes his seat among the elders of the land.

24She makes linen garments and sells them,

and supplies the merchants with sashes.

25She is clothed with strength and dignity;

she can laugh at the days to come.

26She speaks with wisdom,

and faithful instruction is on her tongue.

27She watches over the affairs of her household

and does not eat the bread of idleness.

28Her children arise and call her blessed;

her husband also, and he praises her:

29‘Many women do noble things,

but you surpass them all.’

30Charm is deceptive, and beauty is fleeting;

but a woman who fears the Lord is to be praised.

31Honour her for all that her hands have done,

and let her works bring her praise at the city gate.