ምሳሌ 31 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 31:1-31

ንጉሥ ልሙኤል የተናገራቸው ምሳሌዎች

1ንጉሥ ልሙኤልን እናቱ ያስተማረችው ቃል ይህ ነው፤

2“ልጄ ሆይ፤ የማሕፀኔ ልጅ ሆይ፤

የስእለቴ ልጅ ሆይ፤31፥2 ወይም የጸሎቴ መልስ ሆይ

3ጕልበትህን በሴት አትጨርስ፤

ብርታትህንም ነገሥታትን ለሚያጠፉ አታውል።

4“ልሙኤል ሆይ፤ ነገሥታት ይህን ማድረግ የለባቸውም፤

ነገሥታት የወይን ጠጅ ሊጠጡ፣

ገዦችም የሚያሰክር መጠጥ ሊያስጐመጃቸው አይገባም፤

5አለዚያ ጠጥተው የሕጉን ድንጋጌ ይረሳሉ፤

የተጨቈኑትን ሁሉ መብት ይገፍፋሉ።

6ለሚጠፉት የሚያሰክር መጠጥ፣

በሥቃይ ላሉትም የወይን ጠጅ ስጧቸው፤

7ጠጥተው ድኽነታቸውን ይርሱ፤

ችግራቸውንም ከእንግዲህ አያስቡ።

8“ስለ ራሳቸው መናገር ለማይችሉት፣

ለችግረኞችም ሁሉ መብት ተሟገት።

9ተናገር፤ በቅንነትም ፍረድ፤

የምስኪኖችንና የድኾችን መብት አስከብር።”

መዝጊያ ክፍል፤ ጠባየ መልካም ሚስት

10ጠባየ መልካምን ሚስት ማን ያገኛታል?31፥10 ከ10-31 ያለው እያንዳንዱ ቍጥር የሚጀምረው በዕብራይስጡ ሆህያት ቅደም ተከተል መሠረት ነው።

ከቀይ ዕንእጅግ ትበልጣለች።

11ባሏ ሙሉ በሙሉ ይተማመንባታል፤

የሚጐድልበትም ነገር የለም።

12በሕይወት ዘመኗ ሁሉ፣

መልካም ታደርግለታለች እንጂ አትጐዳውም።

13የበግ ጠጕርና የተልባ እግር መርጣ፣

ሥራ በሚወዱ እጆቿ ትፈትላቸዋለች።

14እንደ ንግድ መርከብ፣

ምግቧን ከሩቅ ትሰበስባለች።

15ገና ሳይነጋ ትነሣለች፤

ለቤተ ሰቧ ምግብ፣

ለሴት አገልጋዮቿም ድርሻቸውን ትሰጣለች።

16ራሷ አስባ የዕርሻ መሬት ትገዛለች፤

በምታገኘውም ገንዘብ ወይን ትተክላለች።

17ብርታትን ታጥቃ ሥራዋን ታከናውናለች፤

ክንዶቿም ለሥራ ብርቱ ናቸው።

18ሥራዋ ትርፋማ መሆኑን ታስተውላለች፤

በሌሊትም መብራቷ አይጠፋም።

19በእጇ እንዝርት ትይዛለች፤

በጣቶቿም ዘንጉን ታሾራለች።

20ክንዶቿን ለድኾች ትዘረጋለች፣

እጆቿንም ለችግረኞች ፈታ ታደርጋለች።

21በረዶ ቢጥል ለቤተ ሰዎቿ አትሠጋም፤

ሁሉም ቀይ ልብስ ለብሰዋልና።

22ለመኝታዋ የዐልጋ ልብስ ትሠራለች፤

ቀጭን በፍታና ሐምራዊ ልብስ ለብሳለች።

23ባሏ በአገር ሽማግሌዎች መካከል

በአደባባይ በተቀመጠ ጊዜ የተከበረ ነው።

24የበፍታ መጐናጸፊያዎችን ሠርታ ትሸጣለች፤

ለነጋዴዎችም ድግ ታቀርባለች።

25ብርታትንና ሞገስን ተጐናጽፋለች፤

መጭውን ጊዜ በደስታ ትቀበላለች።

26በጥበብ ትናገራለች፤

በአንደበቷም ቀና ምክር አለ።

27የቤተ ሰቦቿን ጕዳይ በትጋት ትከታተላለች፤

የስንፍና እንጀራ አትበላም።

28ልጆቿ ተነሥተው ቡርክት ይሏታል፤

ባሏም እንዲሁ፣ ሲያመሰግናትም እንዲህ ይላል፤

29“ብዙ ሴቶች መልካም አድርገዋል፤

አንቺ ግን ሁሉንም ትበልጫለሽ።”

30ቍንጅና አታላይ ነው፤ ውበትም ይረግፋል፤

እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን የተመሰገነች ናት።

31የሚገባትን ሽልማት ስጧት፤

ሥራዋም በየአደባባዩ ያስመስግናት።

Ketab El Hayat

الأمثال 31:1-31

أقوال الملك لموئيل

1هَذِهِ أَقْوَالُ لَمُوئِيلَ مَلِكِ مَسَّا الَّتِي تَلَقَّنَهَا عَنْ أُمِّهِ: 2مَاذَا يَا ابْنِي يَا ابْنَ أَحْشَائِي، يَا ابْنَ نُذُورِي؟ 3لَا تُنْفِقْ قُوَّتَكَ عَلَى النِّسَاءِ، وَلا تَسْتَسْلِمْ لِمَنْ يُهْلِكْنَ الْمُلُوكَ. 4لَيْسَ لِلْمُلُوكِ يَا لَمُوئِيلُ، لَيْسَ لِلْمُلُوكِ أَنْ يُدْمِنُوا الْخَمْرَ، وَلا لِلْعُظَمَاءِ أَنْ يَجْرَعُوا الْمُسْكِرَ. 5لِئَلّا يَسْكَرُوا فَيَنْسَوْا الشَّرِيعَةَ، وَيَجُورُوا عَلَى حُقُوقِ الْبَائِسِينَ. 6أَعْطُوا الْمُسْكِرَ لِلْهَالِكِ، وَالْخَمْرَ لِذَوِي النُّفُوسِ التَّعِسَةِ، 7فَيَثْمَلُوا وَيَنْسَوْا فَقْرَهُمْ، وَلا يَذْكُرُوا بُؤْسَهُمْ بَعْدُ.

8افْتَحْ فَمَكَ مُدَافِعاً عَنِ الأَخْرَسِ، وَفِي دَعْوَى كُلِّ مَنْبُوذٍ. 9افْتَحْ فَمَكَ قَاضِياً بِالْعَدْلِ، وَدَافِعْ عَنْ حُقُوقِ الْفُقَرَاءِ وَالْمُحْتَاجِينَ.

خاتمة: المرأة الفاضلة

10مَنْ يَعْثُرُ عَلَى الْمَرْأَةِ الْفَاضِلَةِ؟ إِنَّ قِيمَتَهَا تَفُوقُ اللَّآلِئَ. 11بِها يَثِقُ قَلْبُ زَوْجِهَا فَلا يَحْتَاجُ إِلَى مَا هُوَ نَفِيسٌ. 12تُسْبِغُ عَلَيْهِ الْخَيْرَ دُونَ الشَّرِّ كُلَّ أَيَّامِ حَيَاتِهَا. 13تَلْتَمِسُ صُوفاً وَكَتَّاناً وَتَشْتَغِلُ بِيَدَيْنِ رَاضِيَتَيْنِ، 14فَتَكُونُ كَسُفُنِ التَّاجِرِ الَّتِي تَجْلِبُ طَعَامَهَا مِنْ بِلادٍ نَائِيَةٍ. 15تَنْهَضُ وَاللَّيْلُ مَا بَرِحَ مُخَيِّماً، لِتُعِدَّ طَعَاماً لأَهْلِ بَيْتِهَا، وَتُدَبِّرَ أَعْمَالَ جَوَارِيهَا 16تَتَفَحَّصُ حَقْلاً وَتَشْتَرِيهِ، وَمِنْ مَكْسَبِ يَدَيْهَا تَغْرِسُ كَرْماً 17تُنَطِّقُ حَقَوَيْهَا بِالْقُوَّةِ وَتُشَدِّدُ ذِرَاعَيْهَا. 18وَتُدْرِكُ أَنَّ تِجَارَتَهَا رَابِحَةٌ، وَلا يَنْطَفِئُ سِرَاجُهَا فِي اللَّيْلِ. 19تَقْبِضُ بِيَدَيْهَا عَلَى الْمِغْزَلِ وَتُمْسِكُ كَفَّاهَا بِالْفَلَكَةِ. 20تَبْسُطُ كَفَّيْهَا لِلْفَقِيرِ وَتَمُدُّ يَدَيْهَا لإِغَاثَةِ الْبَائِسِ. 21لَا تَخْشَى عَلَى أَهْلِ بَيْتِهَا مِنَ الثَّلْجِ، لأَنَّ جَمِيعَهُمْ يَرْتَدُونَ الْحُلَلَ الْقِرْمِزِيَّةَ. 22تَصْنَعُ لِنَفْسِهَا أَغْطِيَةً مُوَشَّاةً، وَثِيَابُهَا مُحَاكَةٌ مِنْ كَتَّانٍ وَأُرْجُوَانٍ. 23زَوْجُهَا مَعْرُوفٌ فِي مَجَالِسِ بَوَّابَاتِ الْمَدِينَةِ، حَيْثُ يَجْلِسُ بَيْنَ وُجَهَاءِ الْبِلادِ. 24تَصْنَعُ أَقْمِصَةً كَتَّانِيَّةً وَتَبِيعُهَا، وَتُزَوِّدُ التَّاجِرَ الْكَنْعَانِيَّ بِمَنَاطِقَ. 25كِسَاؤُهَا الْعِزَّةُ وَالشَّرَفُ، وَتَبْتَهِجُ بِالأَيَّامِ الْمُقْبِلَةِ. 26يَنْطِقُ فَمُهَا بِالْحِكْمَةِ، وَفِي لِسَانِهَا سُنَّةُ الْمَعْرُوفِ. 27تَرْعَى بِعِنَايَةٍ شُؤُونَ أَهْلِ بَيْتِهَا، وَلا تَأْكُلُ خُبْزَ الْكَسَلِ. 28يَقُومُ أَبْنَاؤُهَا وَيَغْبِطُونَهَا، وَيُطْرِيهَا زَوْجُهَا أَيْضاً قَائِلاً: 29«نِسَاءٌ كَثِيرَاتٌ قُمْنَ بِأَعْمَالٍ جَلِيلَةٍ، وَلَكِنَّكِ تَفَوَّقْتِ عَلَيْهِنَّ جَمِيعاً». 30الْحُسْنُ غِشٌّ وَالْجَمَالُ بَاطِلٌ، أَمَّا الْمَرْأَةُ الْمُتَّقِيَّةُ الرَّبَّ فَهِيَ الَّتِي تُمْدَحُ. 31أَعْطُوهَا مِنْ ثَمَرِ يَدَيْهَا، وَلْتَكُنْ أَعْمَالُهَا مَصْدَرَ الثَّنَاءِ عَلَيْهَا.