ምሳሌ 30 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 30:1-33

አጉር የተናገራቸው ምሳሌዎች

1የያቄ ልጅ የአጉር ቃል ይህ ነው፤30፥1 ወይም የማሳው ያቄ

ይህ ሰው ለኢቲኤል፣

ለኢቲኤልና ለኡካል ተናገረ፤30፥1 የማስሬቲክ ጽሑፍ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የዕብራይስጡ ግን ተናገረ፤ አቤቱ እግዚአብሔር፤ እኔ ደክሜአለሁ፣ ነገር ግን እጸናለሁ ይላል።

2“እኔ ከሰው ሁሉ ይልቅ ጅል ነኝ፤

ሰው ያለው ማስተዋል የለኝም።

3ጥበብን አልተማርሁም፤

ስለ ቅዱሱም ዕውቀት የለኝም።

4ወደ ሰማይ የወጣ፣ የወረደስ ማነው?

ነፋስን በእጁ ሰብስቦ የያዘ ማነው?

ውሆችንስ በመጐናጸፊያው የጠቀለለ ማነው?

የምድርን ዳርቻዎች ሁሉ የወሰነ ማነው?

ስሙ ማን ነው? የልጁስ ስም ማን ይባላል?

የምታውቅ ከሆነ እስቲ ንገረኝ!

5“የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንከን የለበትም፤

እርሱ ለሚታመኑበት ሁሉ ጋሻቸው ነው።

6በእርሱ ቃል ላይ አንዳች አትጨምር፤

አለዚያ ይዘልፍሃል፤ ሐሰተኛም ያደርግሃል።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ሁለት ነገር እለምንሃለሁ፤

እነዚህንም ከመሞቴ በፊት አትከልክለኝ፤

8ሐሰትንና ሐሰት መናገርን ከእኔ አርቅልኝ፤

ድኽነትንም ሆነ ብልጽግናን አትስጠኝ፤

ብቻ የዕለት እንጀራዬን ስጠኝ።

9አለዚያ ግን ያለ ልክ እጠግብና እክድሃለሁ፤

እግዚአብሔር ማን ነው?’ እላለሁ፤

ወይም ድኻ እሆንና እሰርቃለሁ፤

የአምላኬንም ስም አሰድባለሁ።

10“አገልጋይን በጌታው ፊት በክፉ አታንሣው፤

አለዚያ ይረግምህና ጕዳት ያገኝሃል።

11“አባቱን የሚረግም፣

እናቱን የማይባርክ ትውልድ አለ፤

12ራሳቸውን ንጹሓን አድርገው የሚቈጥሩ፣

ሆኖም ከርኩሰታቸው ያልነጹ አሉ፤

13ዐይናቸው ትዕቢተኛ የሆነ፣ አስተያያቸው ንቀት የሞላበት፣

14ድኾችን ከምድር፣

ችግረኞችንም ከሰው ዘር መካከል ለማጥፋት፣

ጥርሳቸው ሰይፍ የሆነ፣

መንጋጋቸውም ካራ የሆነ አሉ።

15“አልቅት ሁለት ሴት ልጆች አሉት፤

‘ስጡን! ስጡን!’ እያሉ ይጮኻሉ፤

“ፈጽሞ የማይጠግቡ ሦስት ነገሮች አሉ፤

‘በቃኝን’ ከቶ የማያውቁ አራት ናቸው፤

16እነርሱም መቃብር፣30፥16 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል። መካን ማሕፀን፣

ውሃ ጠጥታ የማትረካ ምድር፣

‘በቃኝ’ የማይል እሳት ናቸው።

17“በአባት ላይ የምታፌዝ ዐይን፣

የእናትንም ትእዛዝ የምትንቅ፣

የሸለቆ ቍራዎች ይጐጠጕጧታል፤

ጆፌ አሞሮችም ይበሏታል።

18“እጅግ የሚያስደንቁኝ ሦስት ነገሮች አሉ፤

የማላስተውላቸውም አራት ናቸው፤

19የንስር መንገድ በሰማይ፣

የእባብ መንገድ በቋጥኝ፣

የመርከብ መንገድ በባሕር፣

የሰውም መንገድ ከሴት ልጅ ጋር ናቸው።

20“የአመንዝራዪቱ መንገድ ይህ ነው፤

በልታ አፏን በማበስ፣

‘ምንም የሠራሁት ጥፋት የለም’ ትላለች።

21“ምድር በሦስት ነገር ትናወጣለች፤

እንዲያውም መሸከም የማትችላቸው አራት ነገሮች ናቸው፤

22ባሪያ ሲነግሥ፣

ሰነፍ እንጀራ ሲጠግብ፣

23የተጠላች ሴት ባል ስታገባ፣

ሴት ባሪያ በእመቤቷ እግር ስትተካ።

24“በምድር ላይ አራት ነገሮች ትንንሽ ናቸው፤

ሆኖም እጅግ ጠቢባን ናቸው፤

25ጕንዳኖች ደካማ ፍጡራን ናቸው፤

ሆኖም ምግባቸውን በበጋ ያከማቻሉ።

26ሽኮኮዎች ዐቅመ ደካማ ናቸው፤

ሆኖም መኖሪያቸውን በቋጥኞች መካከል ይሠራሉ፤

27አንበጦች ንጉሥ የላቸውም፤

ሆኖም ቅደም ተከተል ይዘው ይጓዛሉ፤

28እንሽላሊት በእጅ ትያዛለች፤

ሆኖም በቤተ መንግሥት ትገኛለች።

29“አረማመዳቸው ግርማዊ የሆነ ሦስት ነገሮች አሉ፤

እንዲያውም በሞገስ የሚጐማለሉ አራት ናቸው፤

30ከአራዊት መካከል ኀይለኛ የሆነው፣

ከምንም ነገር ፊት ግንባሩን የማያጥፈው አንበሳ፤

31ጐርደድ ጐርደድ የሚል አውራ ዶሮ፣ አውራ ፍየል፣

እንዲሁም በሰራዊቱ የታጀበ ንጉሥ ናቸው።30፥31 ወይም ከተቃውሞ የተጠበቀ ንጉሥ

32“ተላላ ሆነህ ራስህን ከፍ ከፍ ካደረግህ፣

ወይም ክፉ ነገር ካቀድህ፣

እጅህን በአፍህ ላይ አድርግ።

33ወተት ሲናጥ ቅቤ እንደሚወጣው፣

አፍንጫን ሲያሹት እንደሚደማ፣

ቍጣን ማነሣሣትም ጥልን ይፈጥራል።”

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 30:1-33

30

アグルのことば

1次に挙げるのは、マサの人(アラビヤ半島の中央部以東に住む、イシュマエルの子孫)でヤケの子アグルが、イティエルとウカルに教えたことです。

2私は疲れ果て、今にも死にそうです。

そのうえ、人間の資格さえないような愚か者です。

3神はもとより、

人間というものがわかりません。

それがわかるのは神だけです。

4神のほかにだれが、

天と地の間を上り下りしたでしょう。

だれが風や海を思いのまま造り、治めているでしょう。

神のほかにだれが、世界を造ったというのでしょう。

いるとしたら、どこのだれで、

子どもは何という名前ですか。

5神のことばはすべて真実で、

神は頼ってくる者をみな守ってくださいます。

6だから、神の言うことに何かを付け加えて、

うそをついたと言われないようにしなさい。

7ああ、神よ。最後の二つの願いを聞いてください。

8私が決してうそをつきませんように。

それから、私を特に貧乏にも金持ちにもせず、

ただ生きるのにどうしても必要なものだけを

与えてください。

9ぜいたくに慣れすぎて主を忘れたり、

貧しさのあまり盗みを働いて

神の名を汚したりしたくないのです。

10主人にしもべの悪口を言ってはいけません。

そんなことをすれば恨まれるだけです。

11-12親をのろい、悪いことばかりしているくせに、

自分は少しも欠点がないとすましている者がいます。

13-14彼らは自分のことを鼻にかけ、

人を人とも思いません。

貧しい人を陥れようと、

いつも歯を研ぎすましているのです。

15-16蛭のようにしつこく、

いつまでも満足しないものが二つ、三つ、

いいえ四つあります。

地獄、不妊の胎、乾ききった荒野、それに火です。

17父親をあざけり、母親を軽蔑するような者は、

からすに目をほじくられ、はげたかの餌になるのです。

18-19どんなに考えてもわからないことが三つ、

いいえ四つあります。

どのようにしてわしは大空を飛び、

どのようにして蛇は岩の上をはい、

どのようにして船は海を横切る道を見つけ、

どのようにして若い二人の間に

愛情が芽生えるのでしょう。

20わからないことがもう一つあります。

どうして悪い女は、悪いことをしながら厚かましく、

「いったい、どこがいけないの」と言えるのでしょう。

21-23地も震えるほどいやなことが三つ、

いいえ四つあります。

奴隷が王になり、反逆者が成功し、

きらわれた女が結婚し、

女中が女主人に取って代わることです。

24-28体は小さくても、

頭の良さでは何にも負けないものが四つあります。

力はなくても、冬の食糧を集める蟻、

弱くても、岩の間に住んで身を守る岩だぬき、

指導者がなくても、いっしょに行動するいなご、

簡単に捕まるけれど、王宮にでも住みつくやもりです。

29-31地上に堂々としたものが三つ、いいえ四つあります。

怖いもののない百獣の王ライオン、

くじゃく、雄やぎ、軍隊を指揮する王です。

32得意になって悪いことをするのは愚か者です。

少しは恥ずかしいと思うべきです。

33クリームをかきまぜるとバターができ、

鼻をなぐられると血が出るように、

人を怒らせると争いが起きます。