ምሳሌ 30 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 30:1-33

አጉር የተናገራቸው ምሳሌዎች

1የያቄ ልጅ የአጉር ቃል ይህ ነው፤30፥1 ወይም የማሳው ያቄ

ይህ ሰው ለኢቲኤል፣

ለኢቲኤልና ለኡካል ተናገረ፤30፥1 የማስሬቲክ ጽሑፍ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የዕብራይስጡ ግን ተናገረ፤ አቤቱ እግዚአብሔር፤ እኔ ደክሜአለሁ፣ ነገር ግን እጸናለሁ ይላል።

2“እኔ ከሰው ሁሉ ይልቅ ጅል ነኝ፤

ሰው ያለው ማስተዋል የለኝም።

3ጥበብን አልተማርሁም፤

ስለ ቅዱሱም ዕውቀት የለኝም።

4ወደ ሰማይ የወጣ፣ የወረደስ ማነው?

ነፋስን በእጁ ሰብስቦ የያዘ ማነው?

ውሆችንስ በመጐናጸፊያው የጠቀለለ ማነው?

የምድርን ዳርቻዎች ሁሉ የወሰነ ማነው?

ስሙ ማን ነው? የልጁስ ስም ማን ይባላል?

የምታውቅ ከሆነ እስቲ ንገረኝ!

5“የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንከን የለበትም፤

እርሱ ለሚታመኑበት ሁሉ ጋሻቸው ነው።

6በእርሱ ቃል ላይ አንዳች አትጨምር፤

አለዚያ ይዘልፍሃል፤ ሐሰተኛም ያደርግሃል።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ሁለት ነገር እለምንሃለሁ፤

እነዚህንም ከመሞቴ በፊት አትከልክለኝ፤

8ሐሰትንና ሐሰት መናገርን ከእኔ አርቅልኝ፤

ድኽነትንም ሆነ ብልጽግናን አትስጠኝ፤

ብቻ የዕለት እንጀራዬን ስጠኝ።

9አለዚያ ግን ያለ ልክ እጠግብና እክድሃለሁ፤

እግዚአብሔር ማን ነው?’ እላለሁ፤

ወይም ድኻ እሆንና እሰርቃለሁ፤

የአምላኬንም ስም አሰድባለሁ።

10“አገልጋይን በጌታው ፊት በክፉ አታንሣው፤

አለዚያ ይረግምህና ጕዳት ያገኝሃል።

11“አባቱን የሚረግም፣

እናቱን የማይባርክ ትውልድ አለ፤

12ራሳቸውን ንጹሓን አድርገው የሚቈጥሩ፣

ሆኖም ከርኩሰታቸው ያልነጹ አሉ፤

13ዐይናቸው ትዕቢተኛ የሆነ፣ አስተያያቸው ንቀት የሞላበት፣

14ድኾችን ከምድር፣

ችግረኞችንም ከሰው ዘር መካከል ለማጥፋት፣

ጥርሳቸው ሰይፍ የሆነ፣

መንጋጋቸውም ካራ የሆነ አሉ።

15“አልቅት ሁለት ሴት ልጆች አሉት፤

‘ስጡን! ስጡን!’ እያሉ ይጮኻሉ፤

“ፈጽሞ የማይጠግቡ ሦስት ነገሮች አሉ፤

‘በቃኝን’ ከቶ የማያውቁ አራት ናቸው፤

16እነርሱም መቃብር፣30፥16 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል። መካን ማሕፀን፣

ውሃ ጠጥታ የማትረካ ምድር፣

‘በቃኝ’ የማይል እሳት ናቸው።

17“በአባት ላይ የምታፌዝ ዐይን፣

የእናትንም ትእዛዝ የምትንቅ፣

የሸለቆ ቍራዎች ይጐጠጕጧታል፤

ጆፌ አሞሮችም ይበሏታል።

18“እጅግ የሚያስደንቁኝ ሦስት ነገሮች አሉ፤

የማላስተውላቸውም አራት ናቸው፤

19የንስር መንገድ በሰማይ፣

የእባብ መንገድ በቋጥኝ፣

የመርከብ መንገድ በባሕር፣

የሰውም መንገድ ከሴት ልጅ ጋር ናቸው።

20“የአመንዝራዪቱ መንገድ ይህ ነው፤

በልታ አፏን በማበስ፣

‘ምንም የሠራሁት ጥፋት የለም’ ትላለች።

21“ምድር በሦስት ነገር ትናወጣለች፤

እንዲያውም መሸከም የማትችላቸው አራት ነገሮች ናቸው፤

22ባሪያ ሲነግሥ፣

ሰነፍ እንጀራ ሲጠግብ፣

23የተጠላች ሴት ባል ስታገባ፣

ሴት ባሪያ በእመቤቷ እግር ስትተካ።

24“በምድር ላይ አራት ነገሮች ትንንሽ ናቸው፤

ሆኖም እጅግ ጠቢባን ናቸው፤

25ጕንዳኖች ደካማ ፍጡራን ናቸው፤

ሆኖም ምግባቸውን በበጋ ያከማቻሉ።

26ሽኮኮዎች ዐቅመ ደካማ ናቸው፤

ሆኖም መኖሪያቸውን በቋጥኞች መካከል ይሠራሉ፤

27አንበጦች ንጉሥ የላቸውም፤

ሆኖም ቅደም ተከተል ይዘው ይጓዛሉ፤

28እንሽላሊት በእጅ ትያዛለች፤

ሆኖም በቤተ መንግሥት ትገኛለች።

29“አረማመዳቸው ግርማዊ የሆነ ሦስት ነገሮች አሉ፤

እንዲያውም በሞገስ የሚጐማለሉ አራት ናቸው፤

30ከአራዊት መካከል ኀይለኛ የሆነው፣

ከምንም ነገር ፊት ግንባሩን የማያጥፈው አንበሳ፤

31ጐርደድ ጐርደድ የሚል አውራ ዶሮ፣ አውራ ፍየል፣

እንዲሁም በሰራዊቱ የታጀበ ንጉሥ ናቸው።30፥31 ወይም ከተቃውሞ የተጠበቀ ንጉሥ

32“ተላላ ሆነህ ራስህን ከፍ ከፍ ካደረግህ፣

ወይም ክፉ ነገር ካቀድህ፣

እጅህን በአፍህ ላይ አድርግ።

33ወተት ሲናጥ ቅቤ እንደሚወጣው፣

አፍንጫን ሲያሹት እንደሚደማ፣

ቍጣን ማነሣሣትም ጥልን ይፈጥራል።”

Het Boek

Spreuken 30:1-33

1Dit zijn de woorden van Agur, de zoon van Jake—het zijn woorden van God. De strijder zegt: ‘God, ik heb zoveel moeite gedaan, ik kan niet meer!

2Ik schiet tegenover iedereen tekort en het ontbreekt mij aan verstand.

3Ik heb geen wijsheid verkregen en begrijp ook niets van alles wat heilig is.’

4Wie ging er naar de hemel en kwam weer terug? Wie houdt de wind stevig vast? Wie heeft al het water in een mantel gebonden? Wie gaf de aarde haar vorm en omtrek? Hoe heet Hij en hoe heet zijn Zoon? Zeg het mij als u het weet.

5Gods woorden zijn puur en zuiver, Hij beschermt ieder die op Hem vertrouwt.

6Voeg niets aan zijn woorden toe, want dan straft Hij u, omdat u een leugenaar bent.

7God, ik heb twee dingen aan U gevraagd en geef mij die alstublieft voordat ik sterf:

8houd ongeloof en leugens bij mij weg, geef mij armoe noch rijkdom, maar alleen wat ik nodig heb.

9Want als ik verzadigd zou zijn, zou ik U misschien verloochenen door te zeggen: ‘Wie is de Here?’ En als ik arm was, zou ik misschien gaan stelen en daardoor uw naam oneer aandoen.

10Klaag een knecht niet aan bij zijn meester, anders vervloekt hij u misschien en beschouwt God u als schuldig.

11Er zijn mensen die hun ouders vervloeken,

12mensen die zichzelf goed vinden, maar in werkelijkheid zondig zijn,

13mensen die hooghartig om zich heen kijken en anderen verachten,

14mensen die hun tanden als zwaarden en hun kiezen als messen gebruiken, om daarmee de noodlijdenden en de armen te vermalen.

15De bloedzuiger heeft twee dochters: ze zijn onverzadigbaar en willen steeds meer. Drie dingen zijn absoluut niet te verzadigen, voor de volgende vier dingen is het nooit genoeg:

16het graf, een onvruchtbare baarmoeder, de aarde die nooit genoeg water heeft, en het vuur. Geen van die vier zegt ooit: ‘Nu is het genoeg.’

17Het oog waaruit minachting voor een vader spreekt of dat opstandig kijkt naar een moeder, wordt uitgepikt door de raven bij de beek, wordt voedsel voor de jonge adelaars.

18Veel dingen zijn voor mij onbegrijpelijk, de volgende vier kan ik niet bevatten:

19een adelaar die hoog aan de hemel zweeft, een slang die moeiteloos over een gladde rots kruipt, een schip dat veilig door de golven vaart en wat gebeurt tussen een man en zijn jonge vrouw.

20En minstens zo onbegrijpelijk is het gedrag van een vrouw die overspel pleegt: zij zondigt, kleedt zich weer aan en zegt: ‘Ik heb niets verkeerds gedaan.’

21Mensen hebben een afschuw van veel dingen en de volgende vier dingen zijn onverdraaglijk:

22een knecht die macht krijgt, een dwaas die in weelde leeft,

23een verbitterde vrouw die toch trouwt en een dienares die de plaats van haar meesteres inneemt.

24De volgende vier zijn weliswaar klein, maar hebben van God grote wijsheid gekregen:

25de mieren hebben weliswaar geen verstand, maar zijn toch zo verstandig in de zomer hun voedsel te verzamelen,

26klipdassen mogen dan redeloze dieren zijn, maar hebben wel hun hol in de rotsen,

27hoewel sprinkhanen geen leider hebben, trekken zij op in geordende groepen,

28de hagedis is met de hand te pakken, maar leeft zelfs in koninklijke paleizen.

29Er zijn veel indrukwekkende dingen op aarde, de volgende vier bijvoorbeeld:

30een oude leeuw, een bejaarde koning der dieren die voor niemand aan de kant gaat,

31een soepel rennende windhond, een trotse bok en een onoverwinnelijke koning.

32Hebt u in uw woede dwaas gehandeld of hebt u kwaad in de zin, zwijg dan en voer uw plan niet uit!

33Want door melk te karnen ontstaat boter, door te hard op de neus te drukken ontstaat een bloedneus en door woede op te wekken ontstaat ruzie.