ምሳሌ 3 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 3:1-35

ከጥበብ የሚገኝ ተጨማሪ በረከት

1ልጄ ሆይ፤ ትምህርቴን አትርሳ፤

ትእዛዞቼን በልብህ ጠብቅ፤

2ቀኖችን ይጨምሩልሃል፤ ዓመቶችንም ያረዝሙልሃል፤

ሕይወት፣ ሀብትንና ሰላምን ያበዙልሃል።

3ፍቅርና ታማኝነት ከቶ አይለዩህ፤

በዐንገትህ ዙሪያ እሰራቸው፤

በልብህም ጽላት ላይ ጻፋቸው።

4በዚያን ጊዜ ሞገስንና መልካም ስምን፣

በእግዚአብሔርና በሰው ዘንድ ታገኛለህ።

5በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፤

በራስህ ማስተዋል አትደገፍ፤

6በመንገድህ ሁሉ እርሱን ዕወቅ፤

እርሱም ጐዳናህን ቀና ያደርገዋል።3፥6 ወይም ጐዳናህን ያቀናልሃል

7በራስህ አስተያየት ጠቢብ ነኝ አትበል፤

እግዚአብሔርን ፍራ፤ ከክፉም ራቅ።

8ይህም ለሰውነትህ ጤንነትን፣

ለዐጥንትህም ልምላሜን ያመጣልሃል።

9እግዚአብሔርን በሀብትህ፣

ከምርትህ ሁሉ በኵራት አክብረው፤

10ይህን ብታደርግ፣ ጎተራህ ሞልቶ ይትረፈረፋል፤

መጥመቂያህም በአዲስ የወይን ጠጅ ቲፍ ብሎ ይሞላል።

11ልጄ ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ተግሣጽ አትናቅ፤

በዘለፋውም አትመረር፤

12አባት ደስ የሚሰኝበትን ልጁን እንደሚቀጣ3፥12 ወይም እንደሚገሥጽ ሁሉ፣

እግዚአብሔርም የሚወድደውን ይገሥጻልና።

13ጥበብን የሚያገኛት፣

ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርጋት ሰው ቡሩክ ነው፤

14እርሷ ከብር ይልቅ ትርፍ የምታመጣ፣

ከወርቅም ይልቅ ጥቅም የምታስገኝ ናትና።

15ከቀይ ዕንይበልጥ ውድ ናት፤

አንተ ከምትመኘውም ሁሉ የሚስተካከላት የለም።

16በቀኝ እጇ ረዥም ዕድሜ አለ፤

በግራ እጇም ሀብትና ክብር ይዛለች።

17መንገዷ ደስ የሚያሰኝ ነው፤

ጐዳናዋም ሁሉ ሰላም ነው።

18ለሚያቅፏት የሕይወት ዛፍ ናት፤

የሚይዟትም ይባረካሉ።

19እግዚአብሔር በጥበብ ምድርን መሠረተ፤

በማስተዋል ሰማያትን በየስፍራቸው አጸና፤

20በዕውቀቱ ቀላያት ተከፈሉ፤

ደመናትም ጠልን አንጠበጠቡ።

21ልጄ ሆይ፤ ትክክለኛ ፍርድንና አስተውሎ መለየትን ጠብቅ፤

እነዚህ ከእይታህ አይራቁ፤

22ለነፍስህ ሕይወት፣

ለዐንገትህም ጌጥ ይሆናሉ።

23ከዚያም መንገድህን በሰላም ትሄዳለህ፤

እግርህም አይሰናከልም፤

24ስትተኛ አትፈራም፤

ትተኛለህ እንቅልፍህም ጣፋጭ ይሆናል።

25ድንገተኛን መከራ፣

በክፉዎች ላይ የሚደርሰውንም ጥፋት አትፍራ፤

26እግዚአብሔር መታመኛህ ይሆናልና፤

እግርህንም በወጥመድ ከመያዝ ይጠብቃል።

27ማድረግ እየቻልህ

ለሚገባቸው መልካም ነገር ከማድረግ አትቈጠብ።

28አሁን በእጅህ እያለ፣

ጎረቤትህን፣ “ቈይተህ ተመለስ፤ ነገ እሰጥሃለሁ” አትበለው።

29አንተን ተማምኖ በአጠገብህ በተቀመጠ፣

በጎረቤትህ ላይ ክፉ አትምከርበት።

30ምንም ጕዳት ሳያደርስብህ፣

ያለ ምክንያት ሰውን አትክሰስ።

31በክፉ ሰው አትቅና፤

የትኛውንም መንገዱን አትምረጥ፤

32እግዚአብሔር ጠማማን ሁሉ ይጸየፋልና፤

ለቅን ሰው ግን ምስጢሩን ይገልጥለታል።

33የእግዚአብሔር ርግማን በክፉዎች ቤት ላይ ነው፤

የጻድቃንን ቤት ግን ይባርካል።

34እርሱ በዕቡያን ፌዘኞች ላይ ያፌዛል፤

ለትሑታን ግን ሞገስን ይሰጣል።

35ጠቢባን ክብርን ይወርሳሉ፤

ሞኞችን ግን ለውርደት ያጋልጣቸዋል።

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 3:1-35

3

知恵は繁栄をもたらす

1-2わが子よ。私の教えたことを忘れてはいけません。

充実した生涯を送りたければ、

私の命令を忠実に守りなさい。

3いつも正しい生活をし、人には親切にしなさい。

この二つが心から行えるように、

しっかり身につけなさい。

4-5神にも人にも喜ばれ、

正しい判断力と英知を得たいなら、

とことん主に信頼しなさい。

決して自分に頼ってはいけません。

6何をするにも、主を第一にしなさい。

主がどうすればよいか教えてくださり、

それを成功させてくださいます。

7-8自分の知恵を過信してはいけません。

むしろ主に信頼して、

悪の道から離れなさい。

心も体もみずみずしく元気がみなぎります。

9-10収入があったなら、まずその一部をささげて、

主をあがめなさい。

そうすれば、倉には食べ物があふれ、

酒蔵は極上の酒で満たされます。

11-12主に懲らしめられても、腹を立ててはいけません。

あなたを愛していればこそ、そうするのです。

父親がかわいい子どもの将来を思って

罰するのと同じです。

13-15善悪の区別がつき、

正しい判断力と英知を持った人は、

大金持ちよりも幸せです。

高価な宝石も、このような知恵に比べたら

取るに足りません。

16-17知恵が与えるものは、

長く良き人生、財産、名誉、楽しみ、平安です。

18知恵はいのちの木、

いつもその実を食べる人は幸せです。

19主の知恵によって地球は造られ、

宇宙全体ができました。

20神の知恵によって、泉は地中深くからわき上がり、

空は雨を降らせるのです。

21二つのものを求めなさい。

善悪を見分ける知恵と良識です。

この二つを見失ってはいけません。

22それらはあなたを生きる力で満たし、

あなたの誉れです。

23挫折や失敗からあなたを守ります。

24-26それらがあなたを見張ってくれるので、

安心して眠れます。

また、主があなたとともにいて守ってくださるので、

みじめな思いをすることも、

悪者の悪だくみを恐れることもありません。

27-28人に何か頼まれたら、すぐにしてあげなさい。

「いつかそのうち」などと、先に延ばしてはいけません。

29あなたを信じきっている隣人を陥れてはいけません。

30意味のないことで争うのはやめなさい。

31暴力をふるう者たちをうらやんで、

彼らの手口をまねてはいけません。

32主はそのような者たちをきらいます。

しかし、神の前に正しく生きる人には

親しくしてくださいます。

33悪者は主にのろわれ、正しい人は祝福されます。

34あざける者はあざけられ、謙遜な人は助けられ、

35知恵ある人はたたえられ、愚か者は恥を見るのです。