ምሳሌ 22 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 22:1-29

1መልካም ስም ከብዙ ብልጽግና ይመረጣል፤

መከበርም ከብርና ከወርቅ ይበልጣል።

2ባለጠጋና ድኻ የሚጋሩት ነገር፣

እግዚአብሔር የሁላቸውም ፈጣሪ መሆኑ ነው።

3አስተዋይ ሰው አደጋ ሲያይ መጠጊያ ይሻል፤

ብስለት የጐደለው ግን በዚያው ይቀጥላል፤ መከራም ያገኘዋል።

4ትሕትናና እግዚአብሔርን መፍራት፣

ሀብትን፣ ክብርንና ሕይወትን ያስገኛል።

5በክፉዎች መንገድ ላይ እሾኽና ወጥመድ አለ፤

ነፍሱን የሚጠብቅ ግን ከእነዚህ ይርቃል።

6ልጅን የሚሄድበትን መንገድ አስተምረው፤22፥6 ወይም አስጀምረው

በሚሸመግልበት ጊዜ ከዚያ ፈቀቅ አይልም።

7ባለጠጋ ድኻን ይገዛል፤

ተበዳሪም የአበዳሪ ባሪያ ነው።

8ክፋትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፤

የቍጣውም በትር ይጠፋል።

9ቸር ሰው ራሱ ይባረካል፤

ምግቡን ከድኾች ጋር ይካፈላልና።

10ፌዘኛን አስወጣው፤ ጠብ ይወገዳል፤

ጥልና ስድብም ያከትማል።

11የልብ ንጽሕናን ለሚወድድና ንግግሩም ሞገስ ላለው ሰው፣

ንጉሥ ወዳጁ ይሆናል።

12የእግዚአብሔር ዐይኖች ዕውቀትን ይጠብቃሉ፤

የማይታመኑትን ሰዎች ቃል ግን እርሱ ከንቱ ያደርጋል።

13ሰነፍ፣ “አንበሳ ውጭ አለ፤

መንገድ ላይ እገደላለሁ” ይላል።

14የአመንዝራ ሴት አፍ ጥልቅ ጕድጓድ ነው፤

እግዚአብሔር የተቈጣውም ይገባበታል።

15ሞኝነት በሕፃን ልብ ታስሯል፤

የተግሣጽ በትር ግን ከእርሱ ያርቅለታል።

16ሀብቱን ለማካበት ድኻን የሚበድል፣

ለባለጠጋም ስጦታ የሚያቀርብ፣ ሁለቱም ይደኸያሉ።

የጠቢባን ምክር

17የጠቢባንን ቃል ልብ ብለህ ስማ፤

ልብህም ወደ ትምህርቴ ያዘንብል፤

18በልብህ ስትጠብቃቸው፣

ሁሉም በከንፈሮችህ ላይ የተዘጋጁ ሲሆኑ ደስ ይላልና።

19ስለዚህ እምነትህ በእግዚአብሔር ላይ እንዲሆን፣

ዛሬ አንተን ራስህን አስተምርሃለሁ።

20የምክርና የዕውቀት ቃል የሆኑ፣

መልካም ትምህርቶችን22፥20 ወይም ሠላሳ ትምህርቶችን አልጻፍሁልህምን?

21ለላከህ ተገቢውን መልስ ትሰጥ ዘንድ፣

እውነተኛና የታመኑ ቃሎችን እንዳስተምርህ አይደለምን?

22ድኾች በመሆናቸው ብቻ ድኾችን አትበዝብዛቸው፤

ችግረኛውንም በአደባባይ አታንገላታው፤

23እግዚአብሔር ይፋረድላቸዋልና፤

የሚቀሟቸውንም ይቀማቸዋል።

24ከግልፍተኛ ጋር ወዳጅ አትሁን፤

በቀላሉ ቱግ ከሚልም ሰው ጋር አትወዳጅ፤

25አለዚያ መንገዱን ትማራለህ፤

ራስህም ትጠመድበታለህ።

26በዋስትና ቃል እጅ አትምታ፤

ለብድር ተያዥ አትሁን፤

27የምትከፍለው ካጣህ፣

የምትተኛበት ዐልጋ ከሥርህ ይወሰድብሃል።

28የቀድሞ አባቶችህ ያስቀመጡትን፣

የጥንቱን የወሰን ምልክት አታፋልስ።

29በሙያው ሥልጡን የሆነውን ሰው አይተሃልን?

በነገሥታት ዘንድ ባለሟል ይሆናል፤

አልባሌ ሰዎችን አያገለግልም።

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 22:1-29

22

1富よりも名誉を大事にしなさい。

金や銀で名声は買えません。

2金持ちも貧しい人も、神の前では同じです。

すべての人を主が造ったからです。

3注意深い人は先まで見通しを立て、

失敗しないように準備します。

考えの足りない者はむやみやたらに進み、

あとで苦しみます。

4謙遜で主を敬う人は、富も名誉も長寿も与えられます。

5神の教えに背く者の道には、

危険な罠が待ち受けています。

自分を大切にする人は、決してそこに近寄りません。

6子どもの時に正しい生き方を教えておけば、

年をとってからも変わりません。

7貧しい人が金持ちに押さえつけられるように、

金を借りる者は貸してくれた人の奴隷になります。

8悪い支配者は必ず災いに会い、権力を失います。

9親切な人は貧しい人に食べ物を分けて喜ばれます。

10人をさげすむ者を追い出せば、

みんなうちとけて、争いも口げんかもなくなります。

11きよい心を愛し、良いことを語る人は、

王のほうから友になってくれます。

12主は正しい人を守り、悪者の計画を葬り去ります。

13怠け者は「仕事になんかとても行けない。

外に出たらライオンに食い殺されるかもしれない」と

言いわけをします。

14売春婦は危険な罠、主にのろわれた者は、

その罠に簡単に引っかかります。

15若者は反抗心でいっぱいですが、

正しく罰すれば素直になります。

16貧しい人からせしめたり、

金持ちにわいろを贈ったりして財産を作っても、

結局は貧しくなります。

知恵のことば(1)

17-19主を信じて任せなさい。

知恵のことばを聞いて忘れずに守りなさい。

そうすれば、自分の益になるばかりでなく、

人にも教えることができるようになります。

20-21私は間違ったことを言ったことはないから、

私の言うことを信じて、そのとおり人にも教えなさい。

22-23貧しい人や病人のものを横取りしてはいけません。

神が見ています。

そんなことをする者は必ず罰せられます。

24-25すぐに腹を立てる愚か者には

近づかないようにしなさい。

安易に近寄ると罠に陥ります。

26-27手もとに余分な金もないのに、

人の保証人になってはいけません。

他人の借金のかたに、

寝具まで

取り上げられてしまいます。

28昔からある境界線を勝手に変えるのは、

どろぼうと同じことです。

29まじめに良い仕事をする人は、必ず成功します。