ምሳሌ 10 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 10:1-32

የሰሎሞን ምሳሌዎች

1የሰሎሞን ምሳሌዎች፤

ጠቢብ ልጅ አባቱን ደስ ያሰኛል፤

ተላላ ልጅ ግን ለእናቱ ሐዘንን ያተርፋል።

2ያላግባብ የተገኘ ሀብት አይጠቅምም፤

ጽድቅ ግን ከሞት ይታደጋል።

3እግዚአብሔር ጻድቁ እንዲራብ አያደርግም፤

የክፉዎችን ምኞት ግን ያጨናግፋል።

4ሰነፍ እጆች ሰውን ያደኸያሉ፤

ትጉህ እጆች ግን ብልጽግናን ያመጣሉ።

5ሰብሉን በበጋ የሚሰበስብ ጠቢብ ልጅ ነው፤

በመከር ጊዜ የሚተኛ ግን ውርደት ይከተለዋል።

6በረከት በጻድቃን ራስ ላይ ነው፤

መዓት ግን የክፉዎችን አፍ ይዘጋል።10፥6 ወይም የክፉዎች አፍ ግን መዓትን ይሰውራል፤ እንዲሁም 11 ይመ።

7የጻድቃን መታሰቢያቸው በረከት ነው፤

የክፉዎች ስም ግን እንደ ጠፋ ይቀራል።

8በልቡ ጠቢብ የሆነ ትእዛዝ ይቀበላል፤

ለፍላፊ ተላላ ግን ወደ ጥፋት ያመራል።

9ሐቀኛ ሰው ያለ ሥጋት ይራመዳል፤

በጠማማ ጐዳና የሚሄድ ግን ይጋለጣል።

10በተንኰለኛ ዐይን የሚጠቅስ ሐዘን ያስከትላል፤

ለፍላፊ ተላላም ወደ ጥፋት ያመራል።

11የጻድቅ አንደበት የሕይወት ምንጭ ናት፤

መዓት ግን የክፉዎችን አፍ ይዘጋል።

12ጥላቻ ጠብን ያነሣሣል፤

ፍቅር ግን ስሕተትን ሁሉ ይሸፍናል።

13ጥበብ በአስተዋይ ሰው ከንፈር ትገኛለች፤

በትር ግን ማመዛዘን ለጐደለው ሰው ጀርባ ነው።

14ጠቢባን ዕውቀት ያከማቻሉ፤

የተላላ አንደበት ግን ጥፋትን ይጋብዛል።

15የባለጠጎች ሀብት የተመሸገ ከተማቸው ነው፤

ድኽነት ግን የድኾች መጥፊያ ናት።

16የጻድቃን ደመወዝ ሕይወት ታስገኝላቸዋለች፤

የክፉዎች ትርፍ ግን ቅጣትን ታመጣባቸዋለች።

17ተግሣጽን ነቅቶ የሚጠብቅ የሕይወትን መንገድ ያሳያል፤

ዕርምትን የማይቀበል ግን ሌሎችን ወደ ስሕተት ይመራል።

18ጥላቻውን የሚሸሽግ ሐሰተኛ አንደበት ያለው ነው፤

ሐሜትን የሚዘራ ሁሉ ተላላ ነው።

19ከቃላት ብዛት ኀጢአት አይታጣም፤

አንደበቱን የሚገታ ግን ጠቢብ ነው።

20የጻድቅ አንደበት የነጠረ ብር ነው፤

የክፉ ሰው ልብ ግን ርባና የለውም።

21የጻድቃን ከንፈሮች ብዙዎችን ያንጻሉ፤

ተላሎች ግን ከማመዛዘን ጕድለት ይሞታሉ።

22የእግዚአብሔር በረከት ብልጽግናን ታመጣለች፤

መከራንም አያክልባትም።

23ተላላ ሰው በክፉ ተግባር ይደሰታል፤

አስተዋይ ሰው ግን በጥበብ ደስ ይለዋል።

24ክፉ ሰው የፈራው ይደርስበታል፤

ጻድቅ የሚመኘው ይፈጸምለታል።

25ዐውሎ ነፋስ ሲነሣ ክፉዎች ተጠራርገው ይወሰዳሉ፤

ጻድቃን ግን ለዘላለም ጸንተው ይኖራሉ።

26ሆምጣጤ ጥርስን፣ ጢስ ዐይንን እንደሚጐዳ፣

ሰነፍም ለሚልኩት እንዲሁ ነው።

27እግዚአብሔርን መፍራት ዕድሜን ያረዝማል፤

የክፉዎች ዕድሜ ግን በዐጭር ይቀጫል።

28የጻድቃን አለኝታ ደስታ ነው፤

የክፉዎች ተስፋ ግን ከንቱ ሆኖ ይቀራል።

29የእግዚአብሔር መንገድ ለጻድቃን መጠጊያ፣

ክፉ ለሚያደርጉ ግን መጥፊያቸው ነው።

30ጻድቃን ፈጽሞ አይነቀሉም፤

ክፉዎች ግን በምድር አይኖሩም።

31የጻድቃን አንደበት ጥበብን ያፈልቃል፤

ጠማማ ምላስ ግን ትቈረጣለች።

32የጻድቃን ከንፈሮች ተገቢውን ነገር ያውቃሉ፤

የክፉዎች አንደበት ግን የሚያውቀው ጠማማውን ብቻ ነው።

King James Version

Proverbs 10:1-32

1The proverbs of Solomon. A wise son maketh a glad father: but a foolish son is the heaviness of his mother.

2Treasures of wickedness profit nothing: but righteousness delivereth from death. 3The LORD will not suffer the soul of the righteous to famish: but he casteth away the substance of the wicked.10.3 the substance…: or, the wicked for their wickedness 4He becometh poor that dealeth with a slack hand: but the hand of the diligent maketh rich. 5He that gathereth in summer is a wise son: but he that sleepeth in harvest is a son that causeth shame. 6Blessings are upon the head of the just: but violence covereth the mouth of the wicked. 7The memory of the just is blessed: but the name of the wicked shall rot. 8The wise in heart will receive commandments: but a prating fool shall fall.10.8 a prating…: Heb. a fool of lips10.8 fall: Heb. be beaten 9He that walketh uprightly walketh surely: but he that perverteth his ways shall be known. 10He that winketh with the eye causeth sorrow: but a prating fool shall fall.10.10 fall: Heb. be beaten 11The mouth of a righteous man is a well of life: but violence covereth the mouth of the wicked. 12Hatred stirreth up strifes: but love covereth all sins. 13In the lips of him that hath understanding wisdom is found: but a rod is for the back of him that is void of understanding.10.13 of understanding: Heb. of heart 14Wise men lay up knowledge: but the mouth of the foolish is near destruction. 15The rich man’s wealth is his strong city: the destruction of the poor is their poverty. 16The labour of the righteous tendeth to life: the fruit of the wicked to sin. 17He is in the way of life that keepeth instruction: but he that refuseth reproof erreth.10.17 erreth: or, causeth to err 18He that hideth hatred with lying lips, and he that uttereth a slander, is a fool. 19In the multitude of words there wanteth not sin: but he that refraineth his lips is wise.

20The tongue of the just is as choice silver: the heart of the wicked is little worth. 21The lips of the righteous feed many: but fools die for want of wisdom.10.21 of wisdom: Heb. of heart 22The blessing of the LORD, it maketh rich, and he addeth no sorrow with it. 23It is as sport to a fool to do mischief: but a man of understanding hath wisdom.

24The fear of the wicked, it shall come upon him: but the desire of the righteous shall be granted. 25As the whirlwind passeth, so is the wicked no more: but the righteous is an everlasting foundation. 26As vinegar to the teeth, and as smoke to the eyes, so is the sluggard to them that send him.

27The fear of the LORD prolongeth days: but the years of the wicked shall be shortened.10.27 prolongeth: Heb. addeth 28The hope of the righteous shall be gladness: but the expectation of the wicked shall perish.

29The way of the LORD is strength to the upright: but destruction shall be to the workers of iniquity. 30The righteous shall never be removed: but the wicked shall not inhabit the earth.

31The mouth of the just bringeth forth wisdom: but the froward tongue shall be cut out. 32The lips of the righteous know what is acceptable: but the mouth of the wicked speaketh frowardness.10.32 frowardness: Heb. frowardnesses