ማቴዎስ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 5:1-48

የተራራው ስብከት

5፥3-12 ተጓ ምብ – ሉቃ 6፥20-23

1ብዙ ሕዝብ እንደ ተሰበሰበ ባየ ጊዜ፣ ወደ ተራራ ወጣና ተቀመጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ መጡ። 2እንዲህም እያለ ያስተምራቸው ጀመር፤

3“በመንፈስ ድኾች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፤

መንግሥተ ሰማይ የእነርሱ ናትና።

4የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፤

መጽናናትን ያገኛሉና።

5የዋሆች ብፁዓን ናቸው፤

ምድርን ይወርሳሉና።

6ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፤

ይጠግባሉና።

7ምሕረት የሚያደርጉ ብፁዓን ናቸው፤

ምሕረትን ያገኛሉና።

8ልባቸው ንጹሕ የሆነ ብፁዓን ናቸው፤

እግዚአብሔርን ያዩታልና።

9ሰላምን የሚያወርዱ ብፁዓን ናቸው፤

የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው ይጠራሉና።

10ስለ ጽድቅ ብለው የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፤

መንግሥተ ሰማይ የእነርሱ ናትና።

11“ሰዎች በእኔ ምክንያት ቢሰድቧችሁ፣ ቢያሳድዷችሁና ክፉውን ሁሉ በሐሰት ቢያስወሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። 12በሰማይ የምትቀበሉት ዋጋ ታላቅ ስለሆነ ደስ ይበላችሁ፤ ሐሤት አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያት እንደዚሁ አሳድደዋቸዋልና።

ጨውና ብርሃን

13“እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው የጨውነት ጣዕሙን ቢያጣ ጣዕሙን መልሶ ሊያገኝ ይችላልን? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ጥቅም አይኖረውም።

14“እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ፤ በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትደበቅ አትችልም፤ 15ሰዎችም መብራት አብርተው ከዕንቅብ ሥር አያስቀምጡትም፤ በቤት ውስጥ ላሉት ሁሉ እንዲያበራ በመቅረዝ ላይ ያስቀምጡታል እንጂ። 16እንደዚሁም ሰዎች መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማይ ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ በሰዎች ፊት ይብራ።

የሕግ ፍጻሜ

17“ሕግንና የነቢያትን ቃል ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ለመፈጸም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም። 18እውነት እላችኋለሁ፤ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ ሕግ ሁሉ ይፈጸማል እንጂ ከሕግ አንዲት ፊደል ወይም አንዲት ነጥብ እንኳ አትሻርም። 19ስለዚህ ማንም ከእነዚህ ትእዛዞች አነስተኛዪቱን እንኳ ቢተላለፍ፣ ሌሎችንም እንዲተላለፉ ቢያስተምር፣ በመንግሥተ ሰማይ ታናሽ ተብሎ ይጠራል፤ ነገር ግን እነዚህን ትእዛዞች እየፈጸመ ሌሎችም እንዲፈጽሙ የሚያስተምር በመንግሥተ ሰማይ ታላቅ ይባላል። 20ጽድቃችሁ ከፈሪሳውያንና ከኦሪት ሕግ መምህራን ጽድቅ ልቆ ካልተገኘ መንግሥተ ሰማይ መግባት አትችሉም።

ነፍስ መግደል አይገባም

5፥2526 ተጓ ምብ – ሉቃ 12፥5859

21“ለቀደሙት ሰዎች፣ ‘አትግደል፤ የገደለ ይፈረድበታል’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ 22እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ወንድሙን ያለ አግባብ የሚቈጣ ይፈረድበታል፤ ማንም ወንድሙን ‘ጅል’ የሚል በሸንጎ ፊት ይጠየቅበታል፤ ‘ደደብ’ የሚለው ደግሞ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይጠብቀዋል።

23“ስለዚህ መባህን በመሠዊያው ላይ ለእግዚአብሔር በምታቀርብበት ጊዜ፣ ወንድምህ የተቀየመብህ ነገር መኖሩ ትዝ ቢልህ፣ 24መባህን በዚያው በመሠዊያው ፊት ተወው፤ በመጀመሪያ ሄደህ ከወንድምህ ጋር ተስማማ፤ ከዚያም ተመልሰህ መባህን ለእግዚአብሔር አቅርብ።

25“የከሰሰህ ባላጋራህ እንዳያስፈርድብህ፣ ዳኛውም ለአሳሪ አሳልፎ እንዳይሰጥህ፣ በወህኒም እንዳትጣል፣ በመንገድ ላይ ሳለህ ከባላጋራህ ጋር ፈጥነህ ተስማማ። 26እውነት እልሃለሁ፤ ካስፈረደብህ ግን የመጨረሻዋን ሳንቲም5፥26 ግሪኩ ኮድራንቴስ ይላል። እስክትከፍል ድረስ ከዚያ አትወጣም።

ማመንዘር አይገባም

27“ ‘አታመንዝር’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 28እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ሴትን በምኞት ዐይን የተመለከተ ሁሉ በልቡ ከእርሷ ጋር አመንዝሯል። 29ቀኝ ዐይንህ የኀጢአት ሰበብ ቢሆንብህ፣ አውጥተህ ወዲያ ጣለው፤ ሰውነትህ በሙሉ ወደ ገሃነም ከሚጣል ከሰውነትህ አንዱን ክፍል ብታጣ ይሻልሃል። 30ቀኝ እጅህ የኀጢአት ሰበብ ቢሆንብህ ቈርጠህ ወዲያ ጣለው፤ ሰውነትህ በሙሉ ወደ ገሃነም ከሚጣል ከሰውነትህ አንዱን ክፍል ብታጣ ይሻልሃል።

31“ ‘ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ የፍቺ ወረቀት መስጠት አለበት’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 32እኔ ግን እላችኋለሁ፤ በላዩ ላይ ስታመነዝር ካላገኛት በስተቀር፣ ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ እንድታመነዝር ያደርጋታል፤ በዚህ ሁኔታ የተፈታችውን ሴት ያገባም እንዳመነዘረ ይቈጠራል።

ስለ መሐላ

33“ለቀደሙት ሰዎች፣ ‘በሐሰት አትማል፤ በእግዚአብሔር ፊት የማልኸውንም ጠብቅ’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 34እኔ ግን ፈጽሞ አትማሉ እላችኋለሁ፤ በሰማይም ቢሆን አትማሉ፤ የእግዚአብሔር ዙፋን ነውና፤ 35በምድርም ቢሆን አትማሉ፤ የእግዚአብሔር የእግሩ ማረፊያ ናትና፤ በኢየሩሳሌምም አትማሉ፤ የታላቁ ንጉሥ ከተማ ናትና 36በራስህም ቢሆን አትማል፤ ከጠጕራችሁ መካከል አንዲቷን እንኳ ነጭ ወይም ጥቍር ማድረግ አትችሉምና። 37ስለዚህ ስትነጋገሩ ቃላችሁ፣ ‘አዎን’ ከሆነ፣ ‘አዎን’፤ አይደለም፣ ከሆነ ‘አይደለም’ ይሁን፤ ከዚህ ውጭ የሆነ ሁሉ ከክፉው የሚመጣ ነውና።

ስለ መበቀል

38“ ‘ዐይን ስለ ዐይን፣ ጥርስ ስለ ጥርስ’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 39እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ‘ክፉ አድራጊውን ሰው አትቃወሙት’፤ ነገር ግን ቀኝ ጕንጭህን ለሚመታህ ሌላውን ጕንጭህን ደግሞ አዙርለት። 40አንድ ሰው እጀ ጠባብህን ሊወስድ ቢከስስህ ካባህን ጨምረህ ስጠው። 41አንድ ሰው አንድ ኪሎ ሜትር ተኩል የሚያህል ርቀት እንድትሄድ ቢያስገድድህ ዕጥፉን መንገድ አብረኸው ሂድ። 42ለሚለምንህ ስጥ፤ ከአንተም ሊበደር የሚሻውን ፊት አትንሣው።

43“ ‘ወዳጅህን ውደድ፤ ጠላትህን ጥላ’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 44እኔ ግን ጠላቶቻችሁን ውደዱ፤5፥44 አንዳንድ የጥንት ቅጆች የሚረግሟችሁን መርቁ፤ ለሚጠሏችሁ መልካም አድርጉ ይላሉ። ለሚያሳድዷችሁም ጸልዩ እላችኋለሁ። 45እንደዚህም በማድረጋችሁ በሰማይ ላለው አባታችሁ ልጆች ትሆናላችሁ፤ እርሱ ፀሓዩን ለክፉዎችና ለደጎች ያወጣል፤ ዝናቡንም ለኀጢአተኞችና ለጻድቃን ያዘንባል። 46የሚወድዷችሁን ብቻ የምትወድዱ ከሆነ ምን ዋጋ ታገኛላችሁ? ቀራጮችስ ይህንኑ ያደርጉ የለምን? 47ወንድሞቻችሁን ብቻ እጅ የምትነሡ ከሆነ ከሌሎች በምን ትሻላላችሁ? አሕዛብስ ይህንኑ ያደርጉ የለምን? 48ስለዚህ የሰማይ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተም ፍጹማን ሁኑ።

Thai New Contemporary Bible

มัทธิว 5:1-48

คำเทศนาบนภูเขา

(ลก.6:20-23)

1เมื่อพระเยซูทอดพระเนตรเห็นฝูงชนมากมายก็เสด็จขึ้นเนินเขาและประทับนั่ง เหล่าสาวกของพระองค์พากันมาหาพระองค์ 2และพระองค์ทรงเริ่มต้นสั่งสอนพวกเขาว่า

3“ความสุขมีแก่ผู้ที่สำนึกว่าตนขัดสนฝ่ายจิตวิญญาณ

เพราะอาณาจักรสวรรค์เป็นของเขาแล้ว

4ความสุขมีแก่ผู้ที่โศกเศร้า

เพราะเขาจะได้รับการปลอบประโลม

5ความสุขมีแก่ผู้ที่ถ่อมสุภาพ

เพราะเขาจะได้รับแผ่นดินโลกเป็นมรดก

6ความสุขมีแก่ผู้ที่หิวกระหายความชอบธรรม

เพราะเขาจะได้อิ่มบริบูรณ์

7ความสุขมีแก่ผู้ที่เมตตากรุณา

เพราะเขาจะได้รับความเมตตากรุณาตอบแทน

8ความสุขมีแก่ผู้ที่มีจิตใจบริสุทธิ์

เพราะเขาจะได้เห็นพระเจ้า

9ความสุขมีแก่ผู้ที่สร้างสันติ

เพราะเขาจะได้ชื่อว่าบุตรของพระเจ้า

10ความสุขมีแก่ผู้ที่ถูกข่มเหงเพราะความชอบธรรม

เพราะอาณาจักรสวรรค์เป็นของเขาแล้ว

11“ความสุขมีแก่ท่านเมื่อคนทั้งหลายสบประมาท ข่มเหง และใส่ร้ายป้ายสีท่านเพราะเรา 12จงชื่นชมยินดีเถิดเพราะบำเหน็จของท่านในสวรรค์ยิ่งใหญ่นัก เพราะพวกเขาได้ข่มเหงบรรดาผู้เผยพระวจนะที่อยู่ก่อนท่านเหมือนกัน

เกลือและแสงสว่าง

13“ท่านทั้งหลายเป็นเกลือของโลก แต่ถ้าเกลือนั้นหมดความเค็มแล้วจะทำให้กลับเค็มอีกได้อย่างไร? มันก็ไม่มีประโยชน์อันใดอีกต่อไป มีแต่จะถูกสาดทิ้งให้คนเหยียบย่ำ

14“ท่านทั้งหลายเป็นแสงสว่างของโลก เมืองที่ตั้งอยู่บนภูเขาจะซ่อนไว้ไม่ได้ 15เช่นเดียวกัน เมื่อคนจุดตะเกียงแล้วย่อมไม่เอาฝาครอบ แต่จะตั้งไว้บนเชิงตะเกียงให้ส่องสว่างแก่ทุกคนในบ้าน 16ในทำนองเดียวกัน จงให้ความสว่างของท่านกระจ่างแจ้งต่อหน้าคนทั้งหลาย เพื่อเขาจะเห็นการดีของท่านและสรรเสริญพระบิดาของท่านผู้สถิตในสวรรค์

บทบัญญัติสำเร็จ

17“อย่าคิดว่าเรามาเพื่อล้มล้างหนังสือบทบัญญัติหรือหนังสือผู้เผยพระวจนะ เราไม่ได้มาล้มล้างแต่มาเพื่อทำให้สำเร็จครบถ้วน 18เราบอกความจริงแก่ท่านว่าตราบจนฟ้าและดินสูญสิ้นไป แม้อักษรที่เล็กที่สุดสักตัวหนึ่งหรือขีดๆ หนึ่งก็จะไม่มีทางสูญหายจากหนังสือบทบัญญัติจนกว่าทุกสิ่งทุกอย่างจะสำเร็จครบถ้วน 19ผู้ใดฝ่าฝืนบทบัญญัติเหล่านี้แม้ข้อเล็กน้อยที่สุดและสอนคนอื่นให้ทำเช่นเดียวกัน ผู้นั้นจะได้ชื่อว่าเป็นผู้เล็กน้อยที่สุดในอาณาจักรสวรรค์ ส่วนผู้ที่ปฏิบัติและสั่งสอนตามคำบัญชาเหล่านี้จะได้ชื่อว่าเป็นผู้ยิ่งใหญ่ในอาณาจักรสวรรค์ 20เพราะเราบอกท่านว่าหากความชอบธรรมของท่านไม่มากกว่าของพวกฟาริสีและเหล่าธรรมาจารย์แล้วท่านจะไม่ได้เข้าอาณาจักรสวรรค์อย่างแน่นอน

ฆาตกรรม

(ลก.12:58,59)

21“ท่านทั้งหลายได้ยินคำซึ่งกล่าวไว้แก่คนโบราณว่า ‘อย่าฆ่าคน5:21 อพย.20:13และถ้าผู้ใดฆ่าคนจะถูกตัดสินลงโทษ’ 22แต่เราบอกท่านว่าถ้าผู้ใดโกรธเคืองพี่น้องของตน5:22 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าพี่น้องของตนโดยไม่มีเหตุจะถูกตัดสินลงโทษ ถ้าผู้ใดพูดดูหมิ่น5:22 แปลตรงตัวว่า “รากา” ซึ่งเป็นคำแสดงการดูหมิ่นในภาษาอาราเมคพี่น้องของตนจะต้องถูกนำตัวขึ้นศาลแซนเฮดริน และถ้าผู้ใดพูดว่า ‘ไอ้โง่!’ อาจจะต้องโทษถึงไฟนรก

23“ดังนั้นถ้าท่านกำลังถวายเครื่องบูชาที่แท่นบูชาและนึกขึ้นได้ว่าพี่น้องมีเหตุขุ่นเคืองใดๆ กับท่าน 24จงละเครื่องบูชาไว้ที่หน้าแท่นแล้วไปคืนดีกับพี่น้องก่อน จึงค่อยกลับมาถวายเครื่องบูชา

25“จงปรองดองกับคู่ความโดยเร็วขณะที่เขากำลังพาท่านไปศาล มิฉะนั้นเขาอาจจะมอบท่านให้แก่ผู้พิพากษา และผู้พิพากษาจะมอบท่านให้แก่เจ้าหน้าที่ แล้วท่านอาจจะถูกขังในเรือนจำ 26เราบอกความจริงแก่ท่านว่าท่านจะออกมาไม่ได้จนกว่าจะใช้หนี้ครบถ้วนทุกบาททุกสตางค์5:26 ภาษากรีกว่าโคแดรนเทส

การล่วงประเวณี

27“ท่านทั้งหลายได้ยินคำซึ่งกล่าวไว้ว่า ‘อย่าล่วงประเวณี’5:27 อพย.20:14 28แต่เราบอกท่านว่าผู้ใดมองดูผู้หญิงด้วยใจกำหนัดก็ได้ล่วงประเวณีกับนางในใจของเขาแล้ว 29หากตาข้างขวาของท่านเป็นเหตุให้ทำบาป จงควักทิ้งเสีย ถึงจะเสียอวัยวะส่วนหนึ่งไปก็ยังดีกว่าทั้งตัวต้องตกนรก 30และถ้ามือขวาของท่านเป็นเหตุให้ทำบาปก็จงตัดทิ้งเสีย ถึงจะเสียอวัยวะส่วนหนึ่งไปก็ยังดีกว่าทั้งตัวต้องตกนรก

การหย่าร้าง

31“มีคำกล่าวไว้ว่า ‘ผู้ใดหย่าภรรยาของตนต้องเขียนหนังสือหย่าให้นาง’5:31 ฉธบ.24:1-4 32แต่เราบอกท่านว่าชายใดหย่าขาดจากภรรยาของตนด้วยเหตุอื่นนอกเหนือจากการผิดศีลธรรมทางเพศ ย่อมเป็นเหตุให้นางกลายเป็นคนล่วงประเวณี และผู้ใดแต่งงานกับผู้หญิงที่ถูกหย่าร้างเช่นนั้นก็ล่วงประเวณีด้วย

การสาบาน

33“อนึ่ง ท่านได้ยินคำซึ่งกล่าวไว้แก่คนในสมัยก่อนว่า ‘อย่าผิดคำสาบาน แต่จงทำตามที่ได้ถวายปฏิญาณแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า’ 34แต่เราบอกท่านว่าจงอย่าสาบานเลย ไม่ว่าจะอ้างสวรรค์เพราะสวรรค์เป็นพระที่นั่งของพระเจ้า 35หรืออ้างแผ่นดินโลกเพราะโลกเป็นแท่นวางพระบาทของพระองค์ หรืออ้างกรุงเยรูซาเล็มเพราะกรุงเยรูซาเล็มเป็นนครขององค์จอมราชัน 36และอย่าสาบานโดยอ้างศีรษะของตนเพราะท่านไม่สามารถทำให้ผมกลายเป็นสีขาวหรือดำได้แม้แต่เพียงเส้นเดียว 37ใช่ก็จงว่า ‘ใช่’ ไม่ก็จงว่า ‘ไม่’ พูดเกินนี้ไปก็มาจากมาร

ตาแทนตา

38“ท่านทั้งหลายได้ยินคำกล่าวไว้ว่า ‘ตาแทนตาและฟันแทนฟัน’5:38 อพย.21:24ลนต.24:20ฉธบ.19:21 39แต่เราบอกท่านว่าอย่าต่อสู้กับคนชั่ว ถ้าผู้ใดตบแก้มขวาของท่าน จงหันแก้มอีกข้างหนึ่งให้เขาด้วย 40และถ้าใครต้องการฟ้องร้องเอาเสื้อของท่าน จงให้เสื้อคลุมของท่านแก่เขาด้วย 41ถ้ามีผู้บังคับให้ท่านไปหนึ่งกิโลเมตรก็จงไปกับเขาสองกิโลเมตร 42จงให้แก่ผู้ที่ขอท่านและอย่าเมินหนีผู้ที่ต้องการจะขอยืมจากท่าน

รักศัตรู

43“ท่านทั้งหลายได้ยินคำกล่าวไว้ว่า ‘จงรักเพื่อนบ้าน5:43 ลนต.19:18และเกลียดชังศัตรู’ 44แต่เราบอกท่านว่าจงรักศัตรูของท่าน5:44 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าศัตรูของท่าน จงอวยพรบรรดาผู้ที่สาปแช่งท่าน จงทำดีต่อบรรดาผู้ที่เกลียดชังท่านและอธิษฐานเผื่อบรรดาผู้ที่ข่มเหงท่าน 45เพื่อท่านจะได้เป็นบุตรของพระบิดาของท่านในสวรรค์ พระองค์ทรงให้ดวงอาทิตย์ขึ้นแก่ทั้งคนชั่วและคนดี และทรงให้ฝนตกแก่ทั้งคนชอบธรรมและคนอธรรม 46ถ้าท่านรักแต่ผู้ที่รักท่านท่านจะได้บำเหน็จอะไร? แม้แต่คนเก็บภาษีก็ทำเช่นนั้นไม่ใช่หรือ? 47ถ้าท่านทักทายเฉพาะพวกพี่น้องของตนท่านทำอะไรมากกว่าคนอื่นเล่า? ถึงคนต่างศาสนาก็ทำเช่นนั้นไม่ใช่หรือ? 48เหตุฉะนั้นจงดีพร้อมเหมือนพระบิดาของท่านในสวรรค์ทรงดีพร้อม