ማቴዎስ 5 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 5:1-48

የተራራው ስብከት

5፥3-12 ተጓ ምብ – ሉቃ 6፥20-23

1ብዙ ሕዝብ እንደ ተሰበሰበ ባየ ጊዜ፣ ወደ ተራራ ወጣና ተቀመጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ መጡ። 2እንዲህም እያለ ያስተምራቸው ጀመር፤

3“በመንፈስ ድኾች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፤

መንግሥተ ሰማይ የእነርሱ ናትና።

4የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፤

መጽናናትን ያገኛሉና።

5የዋሆች ብፁዓን ናቸው፤

ምድርን ይወርሳሉና።

6ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፤

ይጠግባሉና።

7ምሕረት የሚያደርጉ ብፁዓን ናቸው፤

ምሕረትን ያገኛሉና።

8ልባቸው ንጹሕ የሆነ ብፁዓን ናቸው፤

እግዚአብሔርን ያዩታልና።

9ሰላምን የሚያወርዱ ብፁዓን ናቸው፤

የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው ይጠራሉና።

10ስለ ጽድቅ ብለው የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፤

መንግሥተ ሰማይ የእነርሱ ናትና።

11“ሰዎች በእኔ ምክንያት ቢሰድቧችሁ፣ ቢያሳድዷችሁና ክፉውን ሁሉ በሐሰት ቢያስወሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። 12በሰማይ የምትቀበሉት ዋጋ ታላቅ ስለሆነ ደስ ይበላችሁ፤ ሐሤት አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያት እንደዚሁ አሳድደዋቸዋልና።

ጨውና ብርሃን

13“እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው የጨውነት ጣዕሙን ቢያጣ ጣዕሙን መልሶ ሊያገኝ ይችላልን? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ጥቅም አይኖረውም።

14“እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ፤ በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትደበቅ አትችልም፤ 15ሰዎችም መብራት አብርተው ከዕንቅብ ሥር አያስቀምጡትም፤ በቤት ውስጥ ላሉት ሁሉ እንዲያበራ በመቅረዝ ላይ ያስቀምጡታል እንጂ። 16እንደዚሁም ሰዎች መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማይ ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ በሰዎች ፊት ይብራ።

የሕግ ፍጻሜ

17“ሕግንና የነቢያትን ቃል ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ለመፈጸም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም። 18እውነት እላችኋለሁ፤ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ ሕግ ሁሉ ይፈጸማል እንጂ ከሕግ አንዲት ፊደል ወይም አንዲት ነጥብ እንኳ አትሻርም። 19ስለዚህ ማንም ከእነዚህ ትእዛዞች አነስተኛዪቱን እንኳ ቢተላለፍ፣ ሌሎችንም እንዲተላለፉ ቢያስተምር፣ በመንግሥተ ሰማይ ታናሽ ተብሎ ይጠራል፤ ነገር ግን እነዚህን ትእዛዞች እየፈጸመ ሌሎችም እንዲፈጽሙ የሚያስተምር በመንግሥተ ሰማይ ታላቅ ይባላል። 20ጽድቃችሁ ከፈሪሳውያንና ከኦሪት ሕግ መምህራን ጽድቅ ልቆ ካልተገኘ መንግሥተ ሰማይ መግባት አትችሉም።

ነፍስ መግደል አይገባም

5፥2526 ተጓ ምብ – ሉቃ 12፥5859

21“ለቀደሙት ሰዎች፣ ‘አትግደል፤ የገደለ ይፈረድበታል’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ 22እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ወንድሙን ያለ አግባብ የሚቈጣ ይፈረድበታል፤ ማንም ወንድሙን ‘ጅል’ የሚል በሸንጎ ፊት ይጠየቅበታል፤ ‘ደደብ’ የሚለው ደግሞ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይጠብቀዋል።

23“ስለዚህ መባህን በመሠዊያው ላይ ለእግዚአብሔር በምታቀርብበት ጊዜ፣ ወንድምህ የተቀየመብህ ነገር መኖሩ ትዝ ቢልህ፣ 24መባህን በዚያው በመሠዊያው ፊት ተወው፤ በመጀመሪያ ሄደህ ከወንድምህ ጋር ተስማማ፤ ከዚያም ተመልሰህ መባህን ለእግዚአብሔር አቅርብ።

25“የከሰሰህ ባላጋራህ እንዳያስፈርድብህ፣ ዳኛውም ለአሳሪ አሳልፎ እንዳይሰጥህ፣ በወህኒም እንዳትጣል፣ በመንገድ ላይ ሳለህ ከባላጋራህ ጋር ፈጥነህ ተስማማ። 26እውነት እልሃለሁ፤ ካስፈረደብህ ግን የመጨረሻዋን ሳንቲም5፥26 ግሪኩ ኮድራንቴስ ይላል። እስክትከፍል ድረስ ከዚያ አትወጣም።

ማመንዘር አይገባም

27“ ‘አታመንዝር’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 28እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ሴትን በምኞት ዐይን የተመለከተ ሁሉ በልቡ ከእርሷ ጋር አመንዝሯል። 29ቀኝ ዐይንህ የኀጢአት ሰበብ ቢሆንብህ፣ አውጥተህ ወዲያ ጣለው፤ ሰውነትህ በሙሉ ወደ ገሃነም ከሚጣል ከሰውነትህ አንዱን ክፍል ብታጣ ይሻልሃል። 30ቀኝ እጅህ የኀጢአት ሰበብ ቢሆንብህ ቈርጠህ ወዲያ ጣለው፤ ሰውነትህ በሙሉ ወደ ገሃነም ከሚጣል ከሰውነትህ አንዱን ክፍል ብታጣ ይሻልሃል።

31“ ‘ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ የፍቺ ወረቀት መስጠት አለበት’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 32እኔ ግን እላችኋለሁ፤ በላዩ ላይ ስታመነዝር ካላገኛት በስተቀር፣ ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ እንድታመነዝር ያደርጋታል፤ በዚህ ሁኔታ የተፈታችውን ሴት ያገባም እንዳመነዘረ ይቈጠራል።

ስለ መሐላ

33“ለቀደሙት ሰዎች፣ ‘በሐሰት አትማል፤ በእግዚአብሔር ፊት የማልኸውንም ጠብቅ’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 34እኔ ግን ፈጽሞ አትማሉ እላችኋለሁ፤ በሰማይም ቢሆን አትማሉ፤ የእግዚአብሔር ዙፋን ነውና፤ 35በምድርም ቢሆን አትማሉ፤ የእግዚአብሔር የእግሩ ማረፊያ ናትና፤ በኢየሩሳሌምም አትማሉ፤ የታላቁ ንጉሥ ከተማ ናትና 36በራስህም ቢሆን አትማል፤ ከጠጕራችሁ መካከል አንዲቷን እንኳ ነጭ ወይም ጥቍር ማድረግ አትችሉምና። 37ስለዚህ ስትነጋገሩ ቃላችሁ፣ ‘አዎን’ ከሆነ፣ ‘አዎን’፤ አይደለም፣ ከሆነ ‘አይደለም’ ይሁን፤ ከዚህ ውጭ የሆነ ሁሉ ከክፉው የሚመጣ ነውና።

ስለ መበቀል

38“ ‘ዐይን ስለ ዐይን፣ ጥርስ ስለ ጥርስ’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 39እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ‘ክፉ አድራጊውን ሰው አትቃወሙት’፤ ነገር ግን ቀኝ ጕንጭህን ለሚመታህ ሌላውን ጕንጭህን ደግሞ አዙርለት። 40አንድ ሰው እጀ ጠባብህን ሊወስድ ቢከስስህ ካባህን ጨምረህ ስጠው። 41አንድ ሰው አንድ ኪሎ ሜትር ተኩል የሚያህል ርቀት እንድትሄድ ቢያስገድድህ ዕጥፉን መንገድ አብረኸው ሂድ። 42ለሚለምንህ ስጥ፤ ከአንተም ሊበደር የሚሻውን ፊት አትንሣው።

43“ ‘ወዳጅህን ውደድ፤ ጠላትህን ጥላ’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 44እኔ ግን ጠላቶቻችሁን ውደዱ፤5፥44 አንዳንድ የጥንት ቅጆች የሚረግሟችሁን መርቁ፤ ለሚጠሏችሁ መልካም አድርጉ ይላሉ። ለሚያሳድዷችሁም ጸልዩ እላችኋለሁ። 45እንደዚህም በማድረጋችሁ በሰማይ ላለው አባታችሁ ልጆች ትሆናላችሁ፤ እርሱ ፀሓዩን ለክፉዎችና ለደጎች ያወጣል፤ ዝናቡንም ለኀጢአተኞችና ለጻድቃን ያዘንባል። 46የሚወድዷችሁን ብቻ የምትወድዱ ከሆነ ምን ዋጋ ታገኛላችሁ? ቀራጮችስ ይህንኑ ያደርጉ የለምን? 47ወንድሞቻችሁን ብቻ እጅ የምትነሡ ከሆነ ከሌሎች በምን ትሻላላችሁ? አሕዛብስ ይህንኑ ያደርጉ የለምን? 48ስለዚህ የሰማይ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተም ፍጹማን ሁኑ።

New International Version

Matthew 5:1-48

Introduction to the Sermon on the Mount

1Now when Jesus saw the crowds, he went up on a mountainside and sat down. His disciples came to him, 2and he began to teach them.

The Beatitudes

He said:

3“Blessed are the poor in spirit,

for theirs is the kingdom of heaven.

4Blessed are those who mourn,

for they will be comforted.

5Blessed are the meek,

for they will inherit the earth.

6Blessed are those who hunger and thirst for righteousness,

for they will be filled.

7Blessed are the merciful,

for they will be shown mercy.

8Blessed are the pure in heart,

for they will see God.

9Blessed are the peacemakers,

for they will be called children of God.

10Blessed are those who are persecuted because of righteousness,

for theirs is the kingdom of heaven.

11“Blessed are you when people insult you, persecute you and falsely say all kinds of evil against you because of me. 12Rejoice and be glad, because great is your reward in heaven, for in the same way they persecuted the prophets who were before you.

Salt and Light

13“You are the salt of the earth. But if the salt loses its saltiness, how can it be made salty again? It is no longer good for anything, except to be thrown out and trampled underfoot.

14“You are the light of the world. A town built on a hill cannot be hidden. 15Neither do people light a lamp and put it under a bowl. Instead they put it on its stand, and it gives light to everyone in the house. 16In the same way, let your light shine before others, that they may see your good deeds and glorify your Father in heaven.

The Fulfillment of the Law

17“Do not think that I have come to abolish the Law or the Prophets; I have not come to abolish them but to fulfill them. 18For truly I tell you, until heaven and earth disappear, not the smallest letter, not the least stroke of a pen, will by any means disappear from the Law until everything is accomplished. 19Therefore anyone who sets aside one of the least of these commands and teaches others accordingly will be called least in the kingdom of heaven, but whoever practices and teaches these commands will be called great in the kingdom of heaven. 20For I tell you that unless your righteousness surpasses that of the Pharisees and the teachers of the law, you will certainly not enter the kingdom of heaven.

Murder

21“You have heard that it was said to the people long ago, ‘You shall not murder,5:21 Exodus 20:13 and anyone who murders will be subject to judgment.’ 22But I tell you that anyone who is angry with a brother or sister5:22 The Greek word for brother or sister (adelphos) refers here to a fellow disciple, whether man or woman; also in verse 23.5:22 Some manuscripts brother or sister without cause will be subject to judgment. Again, anyone who says to a brother or sister, ‘Raca,’5:22 An Aramaic term of contempt is answerable to the court. And anyone who says, ‘You fool!’ will be in danger of the fire of hell.

23“Therefore, if you are offering your gift at the altar and there remember that your brother or sister has something against you, 24leave your gift there in front of the altar. First go and be reconciled to them; then come and offer your gift.

25“Settle matters quickly with your adversary who is taking you to court. Do it while you are still together on the way, or your adversary may hand you over to the judge, and the judge may hand you over to the officer, and you may be thrown into prison. 26Truly I tell you, you will not get out until you have paid the last penny.

Adultery

27“You have heard that it was said, ‘You shall not commit adultery.’5:27 Exodus 20:14 28But I tell you that anyone who looks at a woman lustfully has already committed adultery with her in his heart. 29If your right eye causes you to stumble, gouge it out and throw it away. It is better for you to lose one part of your body than for your whole body to be thrown into hell. 30And if your right hand causes you to stumble, cut it off and throw it away. It is better for you to lose one part of your body than for your whole body to go into hell.

Divorce

31“It has been said, ‘Anyone who divorces his wife must give her a certificate of divorce.’5:31 Deut. 24:1 32But I tell you that anyone who divorces his wife, except for sexual immorality, makes her the victim of adultery, and anyone who marries a divorced woman commits adultery.

Oaths

33“Again, you have heard that it was said to the people long ago, ‘Do not break your oath, but fulfill to the Lord the vows you have made.’ 34But I tell you, do not swear an oath at all: either by heaven, for it is God’s throne; 35or by the earth, for it is his footstool; or by Jerusalem, for it is the city of the Great King. 36And do not swear by your head, for you cannot make even one hair white or black. 37All you need to say is simply ‘Yes’ or ‘No’; anything beyond this comes from the evil one.5:37 Or from evil

Eye for Eye

38“You have heard that it was said, ‘Eye for eye, and tooth for tooth.’5:38 Exodus 21:24; Lev. 24:20; Deut. 19:21 39But I tell you, do not resist an evil person. If anyone slaps you on the right cheek, turn to them the other cheek also. 40And if anyone wants to sue you and take your shirt, hand over your coat as well. 41If anyone forces you to go one mile, go with them two miles. 42Give to the one who asks you, and do not turn away from the one who wants to borrow from you.

Love for Enemies

43“You have heard that it was said, ‘Love your neighbor5:43 Lev. 19:18 and hate your enemy.’ 44But I tell you, love your enemies and pray for those who persecute you, 45that you may be children of your Father in heaven. He causes his sun to rise on the evil and the good, and sends rain on the righteous and the unrighteous. 46If you love those who love you, what reward will you get? Are not even the tax collectors doing that? 47And if you greet only your own people, what are you doing more than others? Do not even pagans do that? 48Be perfect, therefore, as your heavenly Father is perfect.