ማቴዎስ 27 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 27:1-66

ይሁዳ ራሱን ሰቀለ

1ጧት በማለዳ ላይ፣ የካህናት አለቆችና የሕዝብ ሽማግሌዎች ሁሉ ኢየሱስ ስለሚገደልበት ሁኔታ ተመካከሩ፤ 2ካሰሩትም በኋላ ወስደው ለገዥው ለጲላጦስ አሳልፈው ሰጡት።

3አሳልፎ የሰጠው ይሁዳም ኢየሱስ እንደ ተፈረደበት ባየ ጊዜ ተጸጸተ፤ የወሰደውን ሠላሳ ጥሬ ብር ለካህናት አለቆችና ለሕዝቡ ሽማግሌዎች መልሶ በመስጠት፣ 4“ንጹሕ ሰው አሳልፌ በመስጠቴ በድያለሁ” አለ።

እነርሱም፣ “ታዲያ እኛ ምን አገባን፤ የራስህ ጕዳይ ነው!” አሉት።

5ስለዚህ ይሁዳ ብሩን በቤተ መቅደስ ውስጥ ወርውሮ ወጣ፤ ሄዶም ራሱን ሰቅሎ ሞተ።

6የካህናት አለቆች ብሩን አንሥተው፣ “የደም ዋጋ ስለሆነ ወደ መባ ልንጨምረው አይፈቀድም” አሉ፤ 7ተመካክረውም ለእንግዶች የመቃብር ስፍራ እንዲሆን በገንዘቡ የሸክላ ሠሪውን ቦታ ገዙበት። 8ስለዚህም ያ ቦታ እስከ ዛሬ ድረስ “የደም መሬት” ተብሎ ይጠራል። 9በዚህም በነቢዩ ኤርምያስ እንዲህ ተብሎ የተነገረው ተፈጸመ፤ “ለእርሱ ዋጋ ይሆን ዘንድ የእስራኤል ልጆች የገመቱትን ሠላሳ ጥሬ ብር ተቀበሉ፤ 10እግዚአብሔርም ባዘዘኝ መሠረት ለሸክላ ሠሪው ቦታ ከፈሉ።”

ኢየሱስ በጲላጦስ ፊት

27፥11-26 ተጓ ምብ – ማር 15፥2-15ሉቃ 23፥2318-25ዮሐ 18፥29–19፥16

11በዚህ ጊዜ ኢየሱስ አገረ ገዥው ፊት ቀረበ፤ አገረ ገዥውም፣ “አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን?” በማለት ጠየቀው።

ኢየሱስም፣ “አንተው እንዳልኸው ነው” ሲል መለሰለት።

12የካህናት አለቆችና ሽማግሌዎች ሲከስሱት ግን ምንም መልስ አልሰጠም። 13በዚህ ጊዜ ጲላጦስ፣ “ስንት ነገር አቅርበው እንደሚከስሱህ አትሰማምን?” አለው። 14እርሱ ግን አገረ ገዥው እስኪገረም ድረስ ለቀረበበት ክስ አንዲት ቃል እንኳ አልመለሰም።

15አገረ ገዥው ሕዝቡ በበዓሉ እንዲፈታላቸው የሚጠይቁትን አንድ እስረኛ የመፍታት ልማድ ነበረው። 16በዚያን ጊዜ በዐመፅ የታወቀ በርባን የሚባል እስረኛ ነበር። 17ሕዝቡ እንደ ተሰበሰቡ ጲላጦስ፣ “ከበርባንና ክርስቶስ ከሚባለው ከኢየሱስ፣ ማንን እንድፈታላችሁ ትፈልጋላችሁ?” አላቸው፤ 18ጲላጦስም በቅናት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና።

19በፍርድ ወንበር ላይ ተቀምጦ ሳለ ሚስቱ፣ “በእርሱ ምክንያት ዛሬ በሕልም ብዙ ስለ ተሠቃየሁ፣ በዚያ ንጹሕ ሰው ላይ ምንም ነገር እንዳታደርግ” የሚል መልእክት ላከችበት።

20ነገር ግን የካህናት አለቆችና ሽማግሌዎች በርባን እንዲፈታላቸው ኢየሱስ ግን እንዲገደል ይለምኑ ዘንድ ሕዝቡን ያግባቡ ነበር።

21አገረ ገዥውም፣ “ከሁለቱ ማንን እንድፈታላችሁ ትፈልጋላችሁ?” በማለት ጠየቀ።

እነርሱም፤ “በርባንን!” በማለት መለሱ።

22ጲላጦስም፣ “ታዲያ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስንስ ምን ላድርገው?” አላቸው።

ሁሉም፣ “ይሰቀል!” አሉ።

23ጲላጦስም፣ “ለምን? ምን ክፉ ነገር አድርጓል?” በማለት ጠየቃቸው።

እነርሱ ግን አብዝተው እየጮኹ፣ “ይሰቀል!” አሉ።

24ጲላጦስ ሁኔታው ሽብር ከማስነሣት በስተቀር ምንም ፋይዳ የሌለው መሆኑን ተመልክቶ፣ “እኔ ከዚህ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ፤ ከእንግዲህ ኀላፊነቱ የራሳችሁ ነው” በማለት ውሃ አስመጥቶ በሕዝቡ ፊት እጆቹን ታጠበ።

25ሕዝቡም በሙሉ፣ “ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን!” ብለው መለሱ።

26በዚህ ጊዜ በርባንን ፈታላቸው፤ ኢየሱስን ግን ካስገረፈው በኋላ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠው።

ኢየሱስ በሮማውያን ወታደሮች እጅ

27፥27-31 ተጓ ምብ – ማር 15፥16-20

27ከዚያም የአገረ ገዥው ወታደሮች ኢየሱስን ወደ ገዥው ግቢ ወሰዱት፤ ሰራዊቱንም ሁሉ በዙሪያው አሰባሰቡ። 28ልብሱን ገፍፈው ቀይ ልብስ አጠለቁለት፤ 29እሾኽ ጐንጕነው አክሊል በመሥራት ራሱ ላይ ደፉበት፤ የሸንበቆ በትር በቀኝ እጁ በማስያዝ በፊቱ ተንበርክከው፣ “የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፤ ሰላም ለአንተ ይሁን” በማለት አሾፉበት፤ 30ተፉበትም፤ የሸንበቆ በትሩን ከእጁ ወስደው ራሱ ላይ በሸንበቆው ደግመው ደጋግመው መቱት፤ 31ካሾፉበት በኋላም ቀዩን ልብስ ገፍፈው የራሱን መጐናጸፊያ አለበሱት፤ ሊሰቅሉትም ይዘውት ሄዱ።

የኢየሱስ መሰቀል

27፥33-44 ተጓ ምብ – ማር 15፥22-32ሉቃ 23፥33-43ዮሐ 19፥17-24

32ይዘውትም ሲሄዱ ስምዖን ተብሎ የሚጠራ የቀሬና ሰው አገኙ፤ መስቀሉንም እንዲሸከም አስገደዱት። 33ትርጕሙ፣ “የራስ ቅል ስፍራ” ከሆነው ጎልጎታ ከተባለው ቦታ ሲደርሱ፣ 34ከሐሞት ጋር የተቀላቀለ የወይን ጠጅ እንዲጠጣ ሰጡት፤ እርሱ ግን ቀምሶ ሊጠጣው አልፈቀደም። 35ከሰቀሉትም በኋላ ዕጣ ጥለው ልብሱን ተካፈሉ፤27፥35 ጥቂት የጥንት ቅጆች “በነቢዩ ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉ፤ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ የተባለው ይፈጸም ዘንድ” የሚል አላቸው። 36በዚያም ተቀምጠው ይጠብቁት ነበር። ከራስጌውም፣ 37“ይህ የአይሁድ ንጉሥ ኢየሱስ ነው” የሚል የክስ ጽሑፍ አኖሩ። 38ሁለት ወንበዴዎች አንዱ በቀኙ፣ አንዱ በግራው አብረውት ተሰቅለው ነበር። 39መንገድ ዐላፊዎችም በኀይል እየተሳደቡና ራሳቸውን እየነቀነቁ፣ 40“ቤተ መቅደስን አፍርሰህ በሦስት ቀን ውስጥ የምትሠራው፤ እስቲ ራስህን አድን! የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ በል ከመስቀል ውረድ!” ይሉት ነበር።

41የካህናት አለቆችም ከኦሪት ሕግ መምህራንና ከሽማግሌዎች ጋር ሆነው እያሾፉበት እንዲህ ይሉ ነበር፤ 42“ሌሎችን አዳነ፤ ራሱን ግን ማዳን አይችልም! የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ አሁን ከመስቀል ይውረድ፤ እኛም እናምንበታለን። 43በእግዚአብሔር ታምኗል፤ ‘የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ’ ይል ስለ ነበር እስቲ ከወደደው አሁን ያድነው!” 44ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዴዎችም እንደዚሁ የስድብ ናዳ ያወርዱበት ነበር።

የኢየሱስ መሞት

27፥45-56 ተጓ ምብ – ማር 15፥33-41ሉቃ 23፥44-49

45ከቀኑ ስድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ። 46በዘጠኝ ሰዓት ገደማ፣ ኢየሱስ ድምፁን ከፍ አድርጎ፣ “ኤሎሄ! ኤሎሄ! ላማ ሰበቅታኒ?” እያለ ጮኸ፤ ትርጕሙም “አምላኬ፤ አምላኬ፤ ለምን ተውኸኝ?” ማለት ነው።

47በዚያ ቆመው ከነበሩት አንዳንዶቹ ጩኸቱን ሲሰሙ፣ “ኤልያስን እየተጣራ ነው!” አሉ።

48ወዲያውም ከእነርሱ አንዱ ሮጦ ሰፍነግ በመውሰድ የኮመጠጠ ወይን ጠጅ ውስጥ ነከረው፤ ሰፍነጉንም በሸንበቆ ዘንግ ጫፍ ላይ በማድረግ እንዲጠጣው ለኢየሱስ አቀረበለት። 49የቀሩት ግን፣ “ተዉት፤ እስቲ ኤልያስ መጥቶ ሲያድነው እናያለን!” አሉ።

50ኢየሱስ እንደ ገና ከፍ ባለ ድምፅ ጮኸ፤ መንፈሱንም አሳልፎ ሰጠ።

51በዚያን ጊዜ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለሁለት ተቀደደ፤ ምድር ተናወጠች፤ ዐለቶችም ተሰነጣጠቁ፤ 52መቃብሮች ተከፈቱ፤ አንቀላፍተው የነበሩትም ብዙዎች ቅዱሳን ተነሡ፤ 53ከመቃብርም በመውጣት ከኢየሱስ ትንሣኤ በኋላ ወደ ቅድስት ከተማ ገብተው ለብዙዎች ታዩ።

54የመቶ አለቃውና አብረውት ኢየሱስን ይጠብቁት የነበሩት የመሬት መናወጡንና የሆነውን ነገር ሁሉ ባዩ ጊዜ እጅግ ፈርተው፤ ይህስ፣ “በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበር!” አሉ። 55ከገሊላ የመጡና ኢየሱስን በሚያስፈልገው ነገር ለማገልገል የተከተሉት ብዙ ሴቶች ሁኔታውን ከርቀት እየተመለከቱ በአካባቢው ነበሩ። 56ከእነርሱም መካከል ማርያም መግደላዊት፣ ማርያም የያዕቆብና የዮሴፍ እናት እንዲሁም የዘብዴዎስ ልጆች እናት ነበሩ።

የኢየሱስ መቀበር

27፥57-61 ተጓ ምብ – ማር 15፥42-47ሉቃ 23፥50-56ዮሐ 19፥38-42

57ምሽት ላይ ዮሴፍ የሚባል ሀብታም ሰው ከአርማትያስ መጣ፤ እርሱ ራሱም የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ነበረ። 58ጲላጦስ ፊት ቀርቦ የኢየሱስን በድን ለመነው፤ ጲላጦስም እንዲሰጠው አዘዘ። 59ዮሴፍም በድኑን ወስዶ በንጹሕ የበፍታ ጨርቅ ከፈነው፤ 60ለራሱ ከዐለት አስፈልፍሎ ባዘጋጀው መቃብር ውስጥ አኖረው፤ ከዚያም ትልቅ ድንጋይ አንከባልሎ የመቃብሩን በር ዘግቶ ሄደ። 61በዚህ ጊዜ ማርያም መግደላዊትና ሌላዋ ማርያም ከመቃብሩ ትይዩ ተቀምጠው ነበር።

የመቃብሩ ጥበቃ

62በማግስቱም፣ ከሰንበት ዝግጅት በኋላ ባለው ቀን፣ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ጲላጦስ ፊት ቀርበው እንዲህ አሉት፤ 63“ክቡር ሆይ፤ ያ አሳች በሕይወት ሳለ፣ ‘ከሦስት ቀን በኋላ እነሣለሁ’ ያለው ትዝ ብሎናል፤ 64ስለዚህ ደቀ መዛሙርቱ አስከሬኑን ሰርቀው ለሕዝቡ፣ ‘ከሙታን ተነሥቷል’ ብለው እንዳያስወሩ መቃብሩ እስከ ሦስተኛው ቀን ድረስ እንዲጠበቅ ትእዛዝ ስጥልን፤ አለዚያ የኋለኛው ስሕተት ከፊተኛው የባሰ ይሆናል!”

65ጲላጦስም፣ “ጠባቂዎች አሏችሁ፤ ሄዳችሁ በምታውቁት መንገድ አስጠብቁ” አላቸው። 66እነርሱም ሄደው መቃብሩን በማኅተም አሽገው ጠባቂ አቆሙበት።

Thai New Contemporary Bible

มัทธิว 27:1-66

ยูดาสผูกคอตาย

1พอรุ่งเช้าบรรดาหัวหน้าปุโรหิตและผู้อาวุโสในหมู่ประชาชนได้ตกลงกันว่าจะประหารพระเยซู 2พวกเขามัดพระองค์พาไปมอบตัวแก่ผู้ว่าการปีลาต

3เมื่อยูดาสผู้ทรยศพระเยซูเห็นว่าพระองค์ถูกตัดสินลงโทษก็รู้สึกผิดจับใจ เขาจึงนำเงินสามสิบเหรียญมาคืนแก่พวกหัวหน้าปุโรหิตและเหล่าผู้อาวุโส 4และกล่าวว่า “ข้าพเจ้าได้ทำบาปไปแล้วด้วยการทรยศผู้บริสุทธิ์ ทำให้เขาถึงตาย”

พวกนั้นตอบว่า “แล้วเราเกี่ยวอะไรด้วย? นั่นเป็นความรับผิดชอบของเจ้า”

5ดังนั้นยูดาสจึงขว้างเงินนั้นเข้าไปในพระวิหาร แล้วออกไปผูกคอตาย

6พวกหัวหน้าปุโรหิตเก็บเงินมาแล้วกล่าวว่า “ผิดบทบัญญัติที่จะเก็บเงินนี้เข้าคลังพระวิหารเพราะเป็นเงินค่าโลหิต” 7เขาจึงตกลงกันว่าจะใช้เงินนั้นซื้อที่ดินซึ่งรู้จักกันว่า ทุ่งช่างปั้นหม้อ ไว้เป็นที่ฝังศพคนต่างด้าว 8ฉะนั้นทุ่งดังกล่าวจึงได้ชื่อว่า ทุ่งโลหิต มาจนถึงทุกวันนี้ 9แล้วก็เป็นจริงตามที่ผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์กล่าวไว้ว่า “เขาทั้งหลายนำเงินสามสิบเหรียญซึ่งเป็นค่าตัวของเขาตามที่ชนอิสราเอลตั้งให้ 10ไปซื้อที่ดินของช่างปั้นหม้อตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชาข้าพเจ้าไว้”27:10 ศคย. 11:12,13ยรม.19:1-13; 32:6-9

พระเยซูต่อหน้าปีลาต

(มก.15:2-15; ลก.23:2,3,18-25; ยน.18:29—19:16)

11ขณะเดียวกันพระเยซูทรงยืนอยู่ต่อหน้าผู้ว่าการและผู้ว่าการถามว่า “ท่านเป็นกษัตริย์ของชาวยิวหรือ?”

พระเยซูตรัสว่า “ใช่อย่างที่ท่านว่า”

12พระองค์ไม่ได้ทรงตอบข้อกล่าวหาของพวกหัวหน้าปุโรหิตและเหล่าผู้อาวุโสเลย 13ปีลาตจึงถามว่า “ท่านไม่ได้ยินข้อหาที่พวกเขาฟ้องท่านหรือ?” 14แต่พระองค์ไม่ตรัสตอบข้อกล่าวหาใดๆ เลยทำให้ผู้ว่าการประหลาดใจยิ่งนัก

15ในช่วงเทศกาลเป็นธรรมเนียมที่ผู้ว่าการจะปล่อยตัวนักโทษคนหนึ่งตามที่ประชาชนเลือก 16ครั้งนั้นมีนักโทษอุกฉกรรจ์ชื่อเยซูบารับบัส27:16 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาไม่มีคำว่าเยซูเช่นเดียวกับข้อ 17 17เมื่อประชาชนมารวมตัวกันแล้วปีลาตจึงถามว่า “พวกท่านต้องการให้เราปล่อยคนไหน เยซูบารับบัสหรือเยซูที่เรียกกันว่าพระคริสต์?” 18เพราะปีลาตรู้ว่าพวกเขาจับพระเยซูมาด้วยความอิจฉา

19ขณะปีลาตนั่งอยู่บนบัลลังก์พิพากษา ภรรยาของท่านส่งคนมาเรียนท่านว่า “อย่าไปเกี่ยวข้องกับผู้บริสุทธิ์คนนี้เลยเนื่องจากวันนี้ดิฉันฝันร้ายไม่สบายใจมากเพราะท่านผู้นี้”

20แต่พวกหัวหน้าปุโรหิตและเหล่าผู้อาวุโสยุยงประชาชนว่าให้พวกเขาขอปีลาตให้ปล่อยบารับบัสและให้ประหารพระเยซู

21ผู้ว่าการถามว่า “ท่านต้องการให้ปล่อยคนไหนในสองคนนี้?”

พวกเขาตอบว่า “บารับบัส”

22ปีลาตถามว่า “แล้วจะให้เราทำอย่างไรกับเยซูที่เรียกกันว่าพระคริสต์?”

พวกนั้นทั้งหมดพากันร้องว่า “ตรึงเขาที่ไม้กางเขน!”

23ปีลาตถามว่า “ทำไม? เขาทำผิดอะไร?”

แต่ทุกคนร้องตะโกนดังขึ้นอีกว่า “ตรึงเขาที่ไม้กางเขน!”

24เมื่อปีลาตเห็นว่าไม่ได้การมีแต่จะลุกฮือขึ้น เขาจึงเอาน้ำล้างมือต่อหน้าฝูงชนและกล่าวว่า “เราไม่มีความผิดเรื่องการตายของชายผู้นี้ เป็นความรับผิดชอบของพวกท่าน!”

25คนทั้งปวงตอบว่า “ให้เลือดของเขาตกอยู่กับเราและลูกหลานของเราเถิด!”

26แล้วปีลาตจึงปล่อยบารับบัสให้พวกเขา แต่ให้คนโบยตีพระเยซูและมอบตัวให้ไปตรึงที่ไม้กางเขน

พวกทหารเยาะเย้ยพระเยซู

(มก.15:16-20)

27จากนั้นทหารของผู้ว่าการนำพระเยซูเข้าไปในศาลปรีโทเรียมและระดมทหารทั้งกองมารายล้อมพระองค์ 28พวกเขาเปลื้องเสื้อผ้าของพระองค์ออก แล้วเอาเสื้อสีแดงเข้มมาสวมให้พระองค์ 29จากนั้นจึงสานมงกุฎหนามสวมที่พระเศียร หยิบไม้ใส่พระหัตถ์ขวา แล้วคุกเข่าต่อหน้าพระองค์และเยาะเย้ยว่า “ข้าแต่กษัตริย์ของชาวยิว ขอจงทรงพระเจริญ!” 30เขาถ่มน้ำลายรดพระองค์และเอาไม้นั้นตีพระเศียรครั้งแล้วครั้งเล่า 31หลังจากเยาะเย้ยพระองค์แล้ว ก็ถอดเสื้อนั้นออก เอาเสื้อผ้าของพระองค์เองมาสวมให้ แล้วนำพระองค์ออกไปเพื่อตรึงที่ไม้กางเขน

การตรึงที่ไม้กางเขน

(มก.15:22-32; ลก.23:33-43; ยน.19:17-24)

32ขณะออกไปก็พบชายคนหนึ่งจากไซรีนชื่อซีโมน พวกทหารจึงเกณฑ์ให้เขาแบกไม้กางเขนนั้น 33เมื่อพวกเขามาถึงที่ซึ่งเรียกว่า กลโกธา ซึ่งแปลว่า สถานแห่งหัวกะโหลก 34ก็เอาเหล้าองุ่นผสมน้ำดีมีรสขมมาถวาย พระเยซูทรงชิมแล้วก็ไม่เสวย 35เมื่อเขาตรึงพระองค์ที่ไม้กางเขนแล้ว ก็นำฉลองพระองค์มาจับฉลากแบ่งกัน27:35 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าแบ่งกัน ซึ่งเป็นจริงตามคำที่ผู้เผยพระวจนะได้กล่าวไว้ว่า “เสื้อผ้าของข้าพระองค์ เขาทั้งหลายเอามาจับฉลากแบ่งกัน” (สดด.22:18) 36และพวกเขานั่งเฝ้าพระองค์อยู่ที่นั่น 37เหนือพระเศียรมีข้อหาเขียนติดไว้ว่า “นี่คือเยซูกษัตริย์ของชาวยิว” 38โจรสองคนถูกตรึงที่ไม้กางเขนพร้อมกับพระองค์ คนหนึ่งอยู่ข้างซ้ายและอีกคนหนึ่งอยู่ข้างขวาของพระองค์ 39ผู้คนที่ผ่านไปมาต่างส่ายหน้าพูดสบประมาทพระองค์ 40และกล่าวว่า “เจ้าผู้จะทำลายพระวิหารแล้วสร้างขึ้นใหม่ในสามวัน จงช่วยตัวเองให้รอด! ลงมาจากกางเขนสิถ้าเจ้าเป็นพระบุตรของพระเจ้า!”

41เช่นเดียวกันพวกหัวหน้าปุโรหิต ธรรมาจารย์ และเหล่าผู้อาวุโส ก็เยาะเย้ยพระองค์ว่า 42“เขาช่วยคนอื่นให้รอด แต่ช่วยตัวเองให้รอดไม่ได้! เขาเป็นกษัตริย์ของอิสราเอล! ให้เขาลงมาจากกางเขนเดี๋ยวนี้สิแล้วเราจะเชื่อเขา 43เขาวางใจในพระเจ้าก็ให้พระเจ้าช่วยเขาตอนนี้สิถ้าพระองค์ยังต้องการเขาอยู่ เพราะเขาพูดว่า ‘เราเป็นพระบุตรของพระเจ้า’ ” 44พวกโจรที่ถูกตรึงพร้อมกับพระองค์ก็พากันพูดดูถูกดูหมิ่นพระองค์ต่างๆ นานาด้วย

พระเยซูสิ้นพระชนม์

(มก.15:33-41; ลก.23:44-49)

45แล้วเกิดความมืดมัวไปทั่วแผ่นดินตั้งแต่เที่ยงวันจนถึงบ่ายสามโมง 46ราวบ่ายสามโมงพระเยซูทรงร้องเสียงดังว่า “เอโลอี เอโลอี27:46 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าเอลี เอลี ลามา สะบักธานี?” ซึ่งแปลว่า “พระเจ้าของข้าพระองค์ พระเจ้าของข้าพระองค์ ทำไมทรงทอดทิ้งข้าพระองค์?”27:46 สดด.22:1

47บางคนซึ่งยืนอยู่ที่นั่นเมื่อได้ยินก็พูดว่า “เขาร้องเรียกเอลียาห์”

48ทันใดนั้นคนหนึ่งในพวกเขาก็วิ่งไปเอาฟองน้ำจุ่มเหล้าองุ่นเปรี้ยวเสียบไม้ส่งให้พระเยซูเสวย 49คนอื่นๆ พูดว่า “อย่าไปยุ่งกับเขา ให้เราดูซิว่าเอลียาห์จะมาช่วยเขาหรือไม่”

50และเมื่อพระเยซูทรงร้องเสียงดังอีกครั้ง พระองค์ก็สิ้นพระชนม์

51ขณะนั้นเองม่านในพระวิหารก็ขาดเป็นสองส่วนตั้งแต่บนจรดล่าง เกิดแผ่นดินไหว ศิลาแตกออกจากกัน 52อุโมงค์ฝังศพเปิดออกและร่างของวิสุทธิชนหลายคนที่ตายแล้วก็ฟื้นคืนชีวิต 53พวกเขาออกมาจากอุโมงค์และหลังจากพระเยซูคืนพระชนม์แล้ว พวกเขาก็เข้าสู่นครบริสุทธิ์และปรากฏแก่คนเป็นอันมาก

54ส่วนนายร้อยและทหารที่เฝ้าพระเยซูอยู่ด้วยกันเมื่อเห็นแผ่นดินไหวและทุกสิ่งที่เกิดขึ้นก็ตื่นตกใจร้องว่า “แท้จริงท่านผู้นี้เป็นพระบุตร27:54 หรือบุตรคนหนึ่งของพระเจ้า!”

55ผู้หญิงหลายคนอยู่ที่นั่นเฝ้าดูอยู่ห่างๆ พวกเขาติดตามพระเยซูมาจากกาลิลีเพื่อคอยปรนนิบัติพระองค์ 56ในพวกนั้นมีมารีย์ชาวมักดาลา มารีย์มารดาของยากอบกับโยเซฟ27:56 หรือ โยเสส และมารดาของบุตรเศเบดี

การฝังพระศพพระเยซู

(มก.15:42-47; ลก.23:50-56; ยน.19:38-42)

57เมื่อเวลาเย็นใกล้เข้ามาเศรษฐีคนหนึ่งมาจากอาริมาเธียชื่อโยเซฟ เขาเองก็เป็นสาวกของพระเยซู 58เขาไปพบปีลาตเพื่อขอพระศพพระเยซูและปีลาตก็สั่งให้มอบพระศพแก่เขา 59โยเซฟเชิญพระศพมา เอาผ้าลินินสะอาดพันพระศพ 60แล้วนำไปวางไว้ในอุโมงค์ใหม่ของตนซึ่งสกัดไว้ในศิลาและกลิ้งหินใหญ่ปิดทางเข้าอุโมงค์ แล้วเขาก็ไป 61มารีย์ชาวมักดาลากับมารีย์อีกคนหนึ่งนั่งอยู่ที่นั่นตรงข้ามอุโมงค์

ทหารยามที่อุโมงค์

62วันรุ่งขึ้นถัดจากวันเตรียมพวกหัวหน้าปุโรหิตและพวกฟาริสีไปพบปีลาต 63และเรียนว่า “ใต้เท้าขอรับ พวกข้าพเจ้าจำได้ว่าขณะที่เจ้านักล่อลวงคนนั้นยังมีชีวิตอยู่พูดว่า ‘หลังจากสามวันเราจะเป็นขึ้นมาอีก’ 64ฉะนั้นขอให้ใต้เท้าสั่งให้คนเฝ้าอุโมงค์อย่างแน่นหนาจนถึงวันที่สาม มิฉะนั้นแล้วสาวกของเขาอาจจะมาลักศพไปและบอกประชาชนว่าเขาเป็นขึ้นจากตายแล้ว การล่อลวงครั้งนี้จะเลวร้ายยิ่งกว่าครั้งแรก”

65ปีลาตบอกว่า “เอายามไปเถิด คอยเฝ้าอุโมงค์อย่างแน่นหนาตามที่พวกท่านทำได้” 66ดังนั้นพวกเขาจึงไปดูแลอุโมงค์ให้แน่นหนาโดยการประทับตราที่หินและวางยามประจำอยู่