ማቴዎስ 14 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 14:1-36

የመጥምቁ ዮሐንስ መሞት

14፥1-12 ተጓ ምብ – ማር 6፥14-29

1በዚያን ጊዜ የአራተኛው ክፍል ገዥ የነበረው፣ ሄሮድስ ስለ ኢየሱስ ዝና ሰማ፤ 2ባለሟሎቹንም፣ “እንዲህ ከሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ከሞት ተነሥቶ መጥቷል ማለት ነው፤ ይህ ሁሉ ድንቅ ታምራት በእርሱ የሚደረገውም ለዚህ ነው” አላቸው።

3ቀደም ሲል ሄሮድስ፣ በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮድያዳ ምክንያት ዮሐንስን አስይዞ ወህኒ አስገብቶት ነበር። 4ምክንያቱም ዮሐንስ፣ “እርሷን እንድታገባ ሕግ አይፈቅድልህም” ይለው ነበር። 5ሄሮድስም ዮሐንስን ሊገድለው ፈልጎ፣ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ይመለከተው ስለ ነበር ፈራ።

6ሄሮድስ የልደቱን ቀን ሲያከብር፣ የሄሮድያዳ ልጅ በዘፈን ደስ ስላሰኘችው፣ 7የምትጠይቀውን ሁሉ ሊሰጣት በመሐላ ቃል ገባላት። 8ልጅቷም በእናቷ ተመክራ፣ “የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ በሳሕን ላይ አድርገህ አሁኑኑ ስጠኝ” አለችው። 9በዚህ ጊዜ ንጉሡ ዐዘነ፤ ይሁን እንጂ ስለ መሐላውና ከእርሱ ጋር ስለ ነበሩ እንግዶች ሲል ጥያቄዋ እንዲፈጸምላት አዘዘ። 10ልኮም በወህኒ ውስጥ እንዳለ የዮሐንስን ራስ አስቈረጠ። 11የተቈረጠውንም ራስ በሳሕን ላይ አድርገው ለልጂቱ ሰጧት፤ ልጂቱም ወስዳ ለእናቷ ሰጠች። 12የዮሐንስ ደቀ መዛሙርትም አስከሬኑን ወስደው ቀበሩት፤ ከዚያም ሄደው ለኢየሱስ ነገሩት።

ኢየሱስም አምስት ሺሕ ሰዎችን በታምር መገበ

14፥13-21 ተጓ ምብ – ማር 6፥32-44ሉቃ 9፥10-17ዮሐ 6፥1-13

14፥13-21 ተጓ ምብ – ማቴ 15፥32-38

13ኢየሱስ የሆነውን ነገር በሰማ ጊዜ፣ ከነበረበት ተነሥቶ ወደ አንድ ገለልተኛ ስፍራ በጀልባ ሄደ። ሕዝቡም ይህን ሰምተው፣ ከየከተማው በእግር ተከተሉት። 14ኢየሱስም ከጀልባው ሲወርድ ብዙ ሕዝብ አይቶ ራራላቸው፤ ሕመምተኞቻቸውንም ፈወሰላቸው።

15እየመሸ በመሄዱም ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው፣ “ይህ ስፍራ ምንም የማይገኝበት ምድረ በዳ ነው፤ ጊዜው እየመሸ ስለሆነ፣ ወደ መንደሮች ሄደው የሚበሉት ምግብ እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብት” አሉት።

16ኢየሱስ ግን፣ “መሄድ አያስፈልጋቸውም፤ የሚበሉትን እናንተ ስጧቸው” አላቸው።

17እነርሱም፣ “በዚህ ያለን አምስት እንጀራና ሁለት ዓሣ ብቻ ነው” አሉት።

18እርሱም፣ “እስቲ ያለውን ወደ እኔ አምጡት” አላቸው። 19ከዚያም ሕዝቡ በሣሩ ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፤ አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ዐይኑን ወደ ሰማይ በማቅናት አመስግኖና ባርኮ እንጀራውን ቈረሰ፤ ለደቀ መዛሙርቱም ሰጠ፤ እነርሱም ለሕዝቡ ሰጡ። 20ሁሉም በልተው ጠገቡ፤ ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ የተረፈውን ቍርስራሽ ዐሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ አነሡ። 21የበሉትም ከሴቶችና ከሕፃናት ሌላ፣ አምስት ሺሕ ወንዶች ያህሉ ነበር።

ኢየሱስ በባሕር ላይ በእግሩ ሄደ

14፥22-33 ተጓ ምብ – ማር 6፥45-51ዮሐ 6፥15-21

14፥34-36 ተጓ ምብ – ማር 6፥53-56

22ወዲያውኑ ደቀ መዛሙርቱ በጀልባ ተሳፍረው ወደ ማዶ እንዲቀድሙት አዘዛቸውና እርሱ ሕዝቡን ለማሰናበት ወደ ኋላ ቀረት አለ። 23ሕዝቡን ካሰናበተ በኋላም ለመጸለይ ብቻውን ወደ ተራራ ወጣ፤ በጨለመም ጊዜ ብቻውን በዚያው ነበር፤ 24በዚያ ጊዜ ጀልባዋ ባሕሩን ዘልቃ14፥24 ግሪኩ ብዙ ምዕራፍ ይላል። እየተጓዘች ሳለች ነፋስ ተነሥቶ በማዕበል ትንገላታ ጀመር።

25ከሌሊቱ በአራተኛው ክፍል ኢየሱስ በባሕሩ ላይ እየተራመደ ደቀ መዛሙርቱ ወዳሉበት መጣ። 26ደቀ መዛሙርቱም በባሕሩ ላይ እየተራመደ ሲመጣ ባዩት ጊዜ ፈሩ፤ እነርሱም፣ “ምትሀት ነው!” በማለት በፍርሀት ጮኹ።

27ኢየሱስም ወዲያውኑ፣ “አይዟችሁ፤ እኔ ነኝ አትፍሩ” አላቸው።

28ጴጥሮስም፣ “ጌታ ሆይ፤ አንተ ከሆንህስ፣ በውሃው ላይ እየተራመድሁ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ” አለው።

29እርሱም፣ “ና” አለው።

ጴጥሮስም፣ ከጀልባው ወርዶ በውሃው ላይ እየተራመደ ወደ ኢየሱስ አመራ። 30ነገር ግን የነፋሱን ኀይል ባየ ጊዜ ፈራ፤ መስጠምም ሲጀምር፣ “ጌታ ሆይ፤ አድነኝ!” ብሎ ጮኸ።

31ኢየሱስም ወዲያውኑ እጁን ዘርግቶ ያዘውና፣ “አንተ እምነት የጐደለህ፤ ለምን ተጠራጠርህ?” አለው።

32ኢየሱስና ጴጥሮስ ጀልባው ላይ እንደ ወጡ ነፋሱ ጸጥ አለ። 33ከዚያም በጀልባው ውስጥ የነበሩት፣ “በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” ብለው ሰገዱለት።

ፈውስ በጌንሴሬጥ

34ባሕሩን ከተሻገሩ በኋላ ጌንሴሬጥ ወደ ተባለ ቦታ ደረሱ። 35ነዋሪዎቹም ኢየሱስ መሆኑን ባወቁ ጊዜ፣ በዙሪያው ወዳለ አካባቢ ሁሉ መልእክት ላኩ፤ የታመሙትን ሁሉ ወደ እርሱ በማስመጣት፣ 36በሽተኞቹ የልብሱን ጫፍ ብቻ ይነኩ ዘንድ እንዲፈቅድላቸው ለመኑት፤ የነኩትም ሁሉ ተፈወሱ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

馬太福音 14:1-36

施洗者約翰之死

1分封王希律聽見耶穌的名聲, 2就對臣僕說:「這個人是施洗者約翰!他從死裡復活了,所以能夠行這些神蹟。」

3原來希律為他兄弟腓力的妻子希羅底的緣故,拘捕了約翰,把他捆綁起來關在監裡。 4因為約翰曾多次對他說:「你娶這個婦人是不對的。」 5他想殺掉約翰,但怕觸怒百姓,因為他們都認為約翰是先知。

6希律的生日那天,希羅底的女兒出來在眾人面前跳舞。希律非常高興, 7就起誓答應她無論要什麼都可以。 8她受了母親的指使,說:「請把施洗者約翰的頭放在盤子裡送給我。」 9希律感到為難,但既然在眾賓客面前起了誓,只好下令給她。 10他派人到監裡砍了約翰的頭, 11放在盤子裡送給她,她轉送給她母親。 12約翰的門徒把屍體領回安葬後,就去告訴耶穌。

13耶穌聽見這個消息,就獨自坐船退到一處偏僻的地方。眾人得知後,就從各城步行來跟隨祂。

耶穌使五千人吃飽

14耶穌上了岸,看見一大群人,心裡憐憫他們,就治好了他們當中的病人。 15黃昏時,門徒過來對耶穌說:「這裡是荒郊野外,天又晚了,請遣散眾人,好讓他們到村莊去自己買些吃的。」

16耶穌回答說:「他們不用離開,你們給他們吃的吧。」

17門徒答道:「我們這裡只有五個餅和兩條魚。」

18耶穌說:「拿來給我。」

19於是,祂叫眾人坐在草地上,然後拿起那五個餅和兩條魚,舉目望著天祝謝後,就掰開餅遞給門徒,讓他們分給眾人。 20大家都吃飽了,把剩下的零碎收拾起來,竟裝滿了十二個籃子。 21當時吃飯的,除了婦女和小孩,約有五千男人。

耶穌在水上行走

22隨後,耶穌催門徒上船,叫他們先渡到湖對岸,祂則遣散眾人。 23待眾人都離開了,祂就獨自上山去禱告,在那裡一直待到晚上。

24那時,門徒的船離岸已遠,遇到逆風,船身被波浪撞擊得搖擺不定。 25天將破曉的時候,耶穌從水面上向門徒走去。 26門徒看見有人在湖面上走,都嚇壞了,說:「是幽靈!」他們害怕得又喊又叫。

27耶穌立刻對他們說:「放心吧!是我,不要怕。」

28彼得說:「主啊!如果真的是你,就叫我從水面上走到你那裡。」

29耶穌說:「好,你來吧!」

於是,彼得就從船上下去,走在湖面上,要去耶穌那裡。 30他看到風浪很大,就害怕起來,身體開始往下沉,便大喊:「主啊,救我!」

31耶穌馬上伸手拉住他,說:「你信心太小了!為什麼懷疑呢?」

32他們上了船,風浪就平靜了。 33船上的人都敬拜祂,說:「你真是上帝的兒子。」

34他們渡到湖對岸,來到革尼撒勒35當地的人認出是耶穌,就派人去把附近所有的病人都帶到祂面前, 36求耶穌讓他們摸一摸祂衣裳的穗邊,所有摸過的病人都好了。