ማቴዎስ 1 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 1:1-25

የኢየሱስ የትውልድ ሐረግ

1፥1-17 ተጓ ምብ – ሉቃ 3፥23-38

1፥3-6 ተጓ ምብ – ሩት 4፥18-22

1፥7-11 ተጓ ምብ – 1ዜና 3፥10-17

1የዳዊት ልጅ፣ የአብርሃም ልጅ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ሐረግ የሚከተለው ነው።

2አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤

ይስሐቅ ያዕቆብን ወለደ፤

ያዕቆብ ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ፤

3ይሁዳ ከትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ፤

ፋሬስ ኤስሮምን ወለደ፤

ኤስሮምም አራምን ወለደ፤

4አራም አሚናዳብን ወለደ፤

አሚናዳብ ነአሶንን ወለደ፤

ነአሶን ሰልሞንን ወለደ፤

5ሰልሞን ቦዔዝን ከረዓብ ወለደ፤

ቦዔዝ ከሩት ኢዮቤድን ወለደ፤

ኢዮቤድ እሴይን ወለደ፤

6እሴይ ንጉሥ ዳዊትን ወለደ።

ዳዊት የኦርዮ ሚስት ከነበረችው ሰሎሞንን ወለደ፤

7ሰሎሞን ሮብዓምን ወለደ፤

ሮብዓም አቢያን ወለደ፤

አቢያም አሣፍን ወለደ፤

8አሣፍ ኢዮሣፍጥን ወለደ፤

ኢዮሣፍጥ ኢዮሆራምን ወለደ፤

ኢዮሆራም ዖዝያንን ወለደ፤

9ዖዝያን ኢዮአታምን ወለደ፤

ኢዮአታም አካዝን ወለደ፤

አካዝ ሕዝቅያስን ወለደ፤

10ሕዝቅያስ ምናሴን ወለደ፤

ምናሴ አሞንን ወለደ፤

አሞንም ኢዮስያስን ወለደ፤ 11ኢዮስያስ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ፣

ኢኮንያንንና1፥11 ዮአኪን ማለት ነው፤ 12 ይመ ወንድሞቹን ወለደ።

12ከባቢሎን ምርኮ በኋላ፣

ኢኮንያን ሰላትያልን ወለደ፤

ሰላትያልም ዘሩባቤልን ወለደ፤

13ዘሩባቤል አብዩድን ወለደ፤

አብዩድ ኤልያቄምን ወለደ፤

ኤልያቄም አዛርን ወለደ፤

14አዛር ሳዶቅን ወለደ፤

ሳዶቅ አኪምን ወለደ፤

አኪምም ኤልዩድን ወለደ፤

15ኤልዩድ አልዓዛርን ወለደ፤

አልዓዛር ማታንን ወለደ፤

ማታን ያዕቆብን ወለደ፤

16ያዕቆብ ዮሴፍን ወለደ፤ ዮሴፍም የኢየሱስ ክርስቶስ እናት የማርያም ዕጮኛ ነበር።

17እንግዲህ ከአብርሃም እስከ ዳዊት ዐሥራ አራት ትውልድ፣ ከዳዊት እስከ ባቢሎን ምርኮ ዐሥራ አራት ትውልድ፣ ከባቢሎን ምርኮ እስከ ክርስቶስ1፥17 ወይም መሲሕ “ክርስቶስ” (በግሪክ) እና “መሲሕ” (በዕብራይስጥ) ሁለቱም “የተቀባው” የሚል ትርጕም አላቸው። ልደት ዐሥራ አራት ትውልድ ይሆናል።

የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት

18የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት ታሪክ እንዲህ ነው፤ እናቱ ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ሳይገናኙ፣ በመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች። 19ዕጮኛዋ ዮሴፍ ጻድቅ ሰው ስለ ነበርና ማርያምን በሰው ፊት ሊያጋልጣት ስላልፈለገ በስውር ሊተዋት ወሰነ።

20በዚህ ሐሳብ ሳለ፣ የጌታ መልአክ በሕልም ተገለጠለት፤ እንዲህም አለው፤ “የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፤ ዕጮኛህን ማርያምን ወደ ቤትህ ለመውሰድ አትፍራ፤ የፀነሰችው በመንፈስ ቅዱስ ነውና። 21ወንድ ልጅ ትወልዳለች፤ ስሙንም ኢየሱስ1፥21 ኢየሱስ በግሪኩ ሲሆን በዕብራይስጡ ኢያሱ ነው፤ ትርጕሙም እግዚአብሔር ያድናል ማለት ነው ብለህ ትጠራዋለህ፤ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው ያድናቸዋልና።”

22ጌታ በነቢዩ እንዲህ ሲል የተናገረው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆነ፤ 23“እነሆ፤ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፤ ስሙንም ዐማኑኤል ይሉታል፤” ትርጕሙም፣ “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” ማለት ነው።

24ዮሴፍም ከእንቅልፉ ነቃ፤ ከዚያም የጌታ መልአክ እንዳዘዘው ማርያምን ወደ ቤቱ ወሰዳት።1፥24 ወደ ቤቱ ወሰዳት የሚለው የግሪኩ ቃል ሚስቱ እንድትሆን ወሰዳት ይለዋል። 25ይሁን እንጂ የበኵር ልጇን እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም፤ የተወለደውንም ሕፃን፣ “ኢየሱስ” ብሎ ጠራው።

Japanese Contemporary Bible

マタイの福音書 1:1-25

1

イエスの系図

1これは、イエス・キリストの系図です。イエス・キリストはダビデ王の子孫、さらにさかのぼってアブラハムの子孫です。

2アブラハムはイサクの父、イサクはヤコブの父、ヤコブはユダとその兄弟たちの父です。

3ユダはパレスとザラの父〔彼らの母はタマル〕、パレスはエスロンの父、エスロンはアラムの父です。

4アラムはアミナダブの父、アミナダブはナアソンの父、ナアソンはサルモンの父です。

5サルモンはボアズの父〔母はラハブ〕、ボアズはオベデの父〔母はルツ〕、オベデはエッサイの父です。

6エッサイはダビデ王の父、ダビデはソロモンの父〔母はウリヤの妻でした〕です。

7ソロモンはレハブアムの父、レハブアムはアビヤの父、アビヤはアサの父です。

8アサはヨサパテの父、ヨサパテはヨラムの父、ヨラムはウジヤの父です。

9ウジヤはヨタムの父、ヨタムはアハズの父、アハズはヒゼキヤの父です。

10ヒゼキヤはマナセの父、マナセはアモンの父、アモンはヨシヤの父です。

11ヨシヤはエコニヤとその兄弟たちの父です〔彼らは、イスラエルの人たちがバビロンに移住していた時に生まれました〕。

12バビロンに移住してからは、エコニヤはサラテルの父、サラテルはゾロバベルの父です。

13ゾロバベルはアビウデの父、アビウデはエリヤキムの父、エリヤキムはアゾルの父です。

14アゾルはサドクの父、サドクはアキムの父、アキムはエリウデの父です。

15エリウデはエレアザルの父、エレアザルはマタンの父、マタンはヤコブの父です。

16そして、ヤコブはヨセフの父です〔このヨセフが、キリストと呼ばれるイエスの母マリヤの夫となった人です〕。

17こういう次第で、アブラハムからダビデ王までが十四代、ダビデ王からバビロン移住までが十四代、バビロン移住からキリストまでが十四代となります。

約束されていた救い主

18イエス・キリストの誕生は次のとおりです。母マリヤはヨセフと婚約していました。ところが結婚する前に、聖霊によってみごもったのです。 19婚約者のヨセフは、神の教えを堅く守る人でしたから、婚約を破棄しようと決心しました。しかし、人前にマリヤの恥をさらしたくなかったので、ひそかに縁を切ることにしました。

20ヨセフがこのことで悩んでいた時、天使が夢に現れて言いました。「ダビデの子孫ヨセフよ。ためらわないで、マリヤと結婚しなさい。マリヤは聖霊によってみごもったのです。 21彼女は男の子を産みます。その子をイエス(「主は救い」の意)と名づけなさい。この方こそ、ご自分を信じる人々を罪から救ってくださるからです。 22このことはみな、神が預言者(神に託されたことばを語る人)を通して語られた、次のことばが実現するためです。

23『見よ。処女がみごもって、男の子を産む。その子はインマヌエル〔神が私たちと共におられる〕と呼ばれる。』イザヤ7・14

24目が覚めるとヨセフは、天使の命じたとおり、マリヤと結婚しました。 25しかし、その子が生まれるまでは、マリヤに触れませんでした。そして、生まれた子をイエスと名づけました。