ማርቆስ 9 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 9:1-50

1ቀጥሎም፣ “እውነት እላችኋለሁ፤ እዚህ ከቆሙት መካከል የእግዚአብሔር መንግሥት በኀይል ስትመጣ እስከሚያዩ ድረስ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች አሉ” አላቸው።

የኢየሱስ መልክ አበራ

9፥2-8 ተጓ ምብ – ሉቃ 9፥28-36

9፥2-13 ተጓ ምብ – ማቴ 17፥1-13

2ከስድስት ቀን በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን አስከትሎ ወደ አንድ ረዥም ተራራ ይዟቸው ወጣ፤ ብቻቸውንም ነበሩ፤ በፊታቸውም ተለወጠ፤ 3ልብሱም በምድር ላይ ማንም ዐጣቢ ዐጥቦ ሊያነጣው በማይችልበት ሁናቴ እጅግ ነጭ ሆነ። 4ኤልያስና ሙሴም ከኢየሱስ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።

5ጴጥሮስም ኢየሱስን፣ “መምህር ሆይ፣ እዚህ ብንኖር ለእኛ መልካም ነው፤ አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ የሚሆኑ ሦስት ዳሶች እንሥራ” አለው። 6እጅግ ስለ ፈሩ የሚናገረውን አያውቅም ነበር።

7ከዚያም ደመና መጥቶ ጋረዳቸው፤ ከደመናውም ውስጥ፣ “ይህ የምወድደው ልጄ ነው፤ እርሱን ስሙት!” የሚል ድምፅ መጣ።

8ወዲያውም ዙሪያቸውን ሲመለከቱ ከኢየሱስ በቀር ማንም አብሯቸው አልነበረም።

9ከተራራው ላይ በሚወርዱበትም ጊዜ፣ የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ያዩትን ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው። 10እነርሱም የተናገራቸውን ቃል በልባቸው አሳደሩት፤ ነገር ግን፣ “ከሙታን መነሣት” ምን ማለት እንደ ሆነ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር።

11ከዚያም፣ “ጸሐፍት አስቀድሞ መምጣት ያለበት ኤልያስ ነው ለምን ይላሉ?” ሲሉ ጠየቁት።

12ኢየሱስም፣ እንዲህ አላቸው፤ “ኤልያስ በርግጥ አስቀድሞ መጥቶ ሁሉን ነገር እንደ ነበረ ያደርጋል፤ ታዲያ፣ የሰው ልጅ ብዙ መከራ መቀበልና መናቅ እንዳለበት የተጻፈው ለምን ይመስላችኋል? 13ነገር ግን እላችኋለሁ፤ ኤልያስማ መጥቶ ነበር፤ እነርሱም ስለ እርሱ በተጻፈው መሠረት ያሻቸውን ሁሉ አድርገውበታል።”

ርኩስ መንፈስ ያለበት ልጅ ተፈወሰ

9፥14-283032 ተጓ ምብ – ማቴ 17፥14-1922-23ሉቃ 9፥37-45

14ወደ ቀሩት ደቀ መዛሙርት ተመልሰው ሲመጡ፣ ብዙ ሕዝብ ከብበዋቸው፣ ጸሐፍት ከእነርሱ ጋር ሲከራከሩ አዩ። 15ሕዝቡ ሁሉ ሲያዩት ወዲያው ተደንቀው እጅ ሊነሡት ወደ እርሱ ሮጡ።

16እርሱም፣ “ከእነርሱ ጋር የምትከራከሩት ስለ ምን ጕዳይ ነበር” ሲል ጠየቃቸው።

17ከሕዝቡ መካከል አንድ ሰው እንዲህ አለው፤ “መምህር ሆይ፤ ርኩስ መንፈስ ዐድሮበት ድዳ የሆነውን ልጄን ወደ አንተ አምጥቼዋለሁ፤ 18በተነሣበት ጊዜ ሁሉ ይጥለዋል፤ ዐረፋ ይደፍቃል፤ ጥርሱንም ያፋጫል፤ ሰውነቱም ይደርቃል፤ ርኩስ መንፈሱን እንዲያስወጡት ደቀ መዛሙርትህን ጠየቅኋቸው፤ እነርሱ ግን አልቻሉም።”

19ኢየሱስም መልሶ፣ “የማታምን ትውልድ ሆይ፤ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ልጁን ወደ እኔ አምጡት!” አላቸው።

20ሰዎቹም ወደ እርሱ አመጡት፤ ርኩስ መንፈሱም ኢየሱስን ባየው ጊዜ ልጁን ወዲያውኑ አንዘፈዘፈው፤ እርሱም መሬት ላይ ወድቆ በመንፈራገጥም ዐረፋ ይደፍቅ ጀመር።

21ኢየሱስም የልጁን አባት፣ “ከያዘው ስንት ጊዜው ነው?” ብሎ ጠየቀው።

እርሱም እንዲህ አለው፤ “ከሕፃንነቱ ጀምሮ ነው፤ 22ሊገድለው ፈልጎ ብዙ ጊዜ እሳትም ውስጥ ውሃም ውስጥ፣ ይጥለዋል፤ የሚቻልህ ከሆነ ራራልን፤ ርዳንም።”

23ኢየሱስም፣ “የሚቻልህ ከሆነ አልህ? ለሚያምን ሰው ሁሉም ነገር ይቻላል” አለው።

24ወዲያውኑ የልጁ አባት፣ “አምናለሁ፤ አለማመኔን ርዳው!” በማለት ጮኸ።

25ኢየሱስም ሕዝቡ ወደዚያ እየተንጋጋ በሩጫ መምጣቱን ባየ ጊዜ፣ “አንተ ደንቈሮና ድዳ መንፈስ ከእርሱ ውጣ! ከእንግዲህም ተመልሰህ እንዳትገባበት አዝዝሃለሁ” ብሎ ርኩሱን9፥25 ወይም ክፉ መንፈስ ገሠጸው።

26ርኩሱም መንፈስ እየጮኸ ክፉኛ ካንፈራገጠው በኋላ ከልጁ ወጣ፤ ብዙዎቹ “ሞቷል” እስኪሉ ድረስ ልጁ እንደ በድን ሆነ። 27ኢየሱስ ግን እጁን ይዞ አስነሣው፤ ልጁም ተነሥቶ ቆመ።

28ኢየሱስ ወደ ቤት ከገባ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው፣ “እኛ ልናስወጣው ያልቻልነው ለምንድን ነው?” ብለው ጠየቁት።

29እርሱም፣ “የዚህ ዐይነቱ ሊወጣ የሚችለው በጸሎትና በጾም9፥29 አንዳንድ ቅጆች በጾም የሚለው የላቸውም። ብቻ ነው” አላቸው።

30ከዚያም ተነሥተው በገሊላ በኩል ዐለፉ፤ ኢየሱስም ያሉበትን ስፍራ ማንም እንዲያውቅ አልፈለገም፤ 31ለደቀ መዛሙርቱ፣ “የሰው ልጅ በሰዎች እጅ ዐልፎ ይሰጣል፤ እነርሱም ይገድሉታል፤ ከሦስት ቀንም በኋላ ይነሣል” እያለ ያስተምራቸው ነበር። 32እነርሱ ግን የሚላቸው አልገባቸውም፤ እንዳይጠይቁትም ፈሩ።

ከሁሉ የሚበልጥ ማን ነው?

9፥33-37 ተጓ ምብ – ማቴ 18፥1-5ሉቃ 9፥46-48

33ከዚህ በኋላ ወደ ቅፍርናሆም መጡ። ቤት ከገባ በኋላም፣ “በመንገድ ላይ የምትከራከሩት ስለ ምን ነበር?” ብሎ ጠየቃቸው። 34እነርሱ ግን በመንገድ ላይ የተከራከሩት ከሁሉ የሚበልጥ ማን ነው በሚል ስለ ነበር ዝም አሉ።

35ከተቀመጠ በኋላ ዐሥራ ሁለቱን ጠርቶ፣ “መጀመሪያ ለመሆን የሚፈልግ፣ ከሁሉ መጨረሻና የሁሉም አገልጋይ ይሁን” አላቸው።

36ትንሽ ልጅ አምጥቶም በመካከላቸው አቆመ፤ ዐቅፎትም፣ 37“ከእነዚህ ሕፃናት አንዱን በስሜ የሚቀበል ሁሉ እኔን ይቀበላል፤ እኔንም የሚቀበለኝ ሁሉ የሚቀበለው እኔን ሳይሆን የላከኝን ነው” አላቸው።

የማይቃወመን ሁሉ ከእኛ ጋር ነው

9፥38-40 ተጓ ምብ – ሉቃ 9፥4950

38ዮሐንስም፣ “መምህር ሆይ፤ አንድ ሰው በስምህ አጋንንት ሲያወጣ አየን፣ እኛን ስለማይከተልም ከለከልነው” አለው።

39ኢየሱስ ግን እንዲህ አለ፤ “አትከልክሉት፤ ማንም በስሜ ታምር ሠርቶ ወዲያውኑ በእኔ ላይ ክፉ መናገር አይችልም፤ 40የማይቃወመን ሁሉ ከእኛ ጋር ነውና፤ 41እውነት እላችኋለሁ፣ የክርስቶስ በመሆናችሁ በስሜ አንድ ኩባያ ውሃ የሚሰጣችሁ ሁሉ ዋጋውን አያጣም።

ለሌላው መሰናክል መሆን

42“በእኔ ከሚያምኑት ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ ከባድ የወፍጮ ድንጋይ በዐንገቱ ታስሮ ወደ ባሕር ቢጣል ይሻለዋል። 43ስለዚህ እጅህ ብታሰናክልህ ቍረጣት፤ ሁለት እጅ ኖሮህ ወደ ገሃነም ከመሄድ፣ ጕንድሽ ሆነህ ወደ ሕይወት መግባት ይሻልሃል፤ 44በገሃነም ትሉ አይሞትም፤ እሳቱ አይጠፋምና9፥44 እነዚህ ጥቅሶች በአንዳንድ ቅጆች አይገኙም። 45እግርህ ብታሰናክልህ ቍረጣት፤ ሁለት እግር ኖሮህ ወደ ገሃነም ከመጣል፣ ዐንካሳ ሆነህ ወደ ሕይወት መግባት ይሻልሃል፤ 46በገሃነም ትሉ አይሞትም፤ እሳቱ አይጠፋምና9፥46 እነዚህ ጥቅሶች በአንዳንድ ቅጆች አይገኙም። 47ዐይንህ ብታሰናክልህ ጐልጕለህ አውጣት፤ ሁለት ዐይን ኖሮህ ወደ ገሃነም ከመጣል፣ አንድ ዐይን ኖሮህ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት ይሻልሃል፤

48“በገሃነም ትሉ አይሞትም፤

እሳቱ አይጠፋምና፤

49ሰው ሁሉ በእሳት ይቀመማልና።

50“ጨው መልካም ነው፤ ነገር ግን ጨው ጨውነቱን ቢያጣ እንዴት መልሳችሁ ጣዕም እንዲኖረው ታደርጉታላችሁ? ጨው በውስጣችሁ ይኑራችሁ፤ እርስ በርሳችሁም ተስማሙ።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

馬可福音 9:1-50

1耶穌繼續說:「我實在告訴你們,有些站在這裡的人會在有生之年看見上帝的國帶著能力降臨。」

登山變象

2六天後,耶穌帶著彼得雅各約翰暗暗地登上一座高山。耶穌在他們面前改變了形像, 3衣服變得潔白放光,世上找不到漂得那麼白的布。 4這時,以利亞摩西在他們眼前出現,與耶穌談話。 5彼得對耶穌說:「老師,我們在這裡真好!我們搭三座帳篷吧,一座給你,一座給摩西,一座給以利亞。」

6其實彼得當時不知說什麼才好,因為他們都很害怕。 7就在這時候,有一朵雲彩飄來遮住他們,雲彩中有聲音說:「這是我的愛子,你們要聽從祂。」 8門徒立刻四處觀看,發現沒有其他人,只有耶穌和他們在那裡。

9下山的時候,耶穌叮囑他們在人子還沒有從死裡復活之前,不要把剛才看見的告訴別人。

10門徒把這話謹記在心,彼此議論「從死裡復活」這句話的意思。 11他們問耶穌:「律法教師為什麼說以利亞必須先來?」

12耶穌回答說:「以利亞固然要先來復興一切,但為什麼聖經上說人子一定會飽受痛苦、遭人蔑視呢? 13其實我告訴你們,以利亞已經來了,人們卻任意對待他,正如聖經的記載。」

治好污鬼附身的孩子

14他們與其他門徒會合時,看見一大群人圍住門徒,幾個律法教師正在跟他們辯論。 15大家一看到耶穌,都十分驚奇,立刻跑上去迎接祂。 16耶穌問門徒:「你們跟他們辯論什麼?」

17人群中有一個人說:「老師,我帶了我的兒子來找你,因為他被啞巴鬼附身。 18每次鬼控制他,把他摔在地上,他就口吐白沫,咬牙切齒,全身僵硬。我請你的門徒趕走那鬼,他們卻辦不到。」

19耶穌說:「唉,這不信的世代啊!我要跟你們在一起待多久,容忍你們多久呢?把他帶到我這裡吧。」

20他們把那孩子帶到耶穌面前。那鬼一見耶穌,就使孩子抽搐,倒在地上打滾,口吐白沫。 21耶穌問孩子的父親:「他這樣子多久了?」孩子的父親回答道:「他從小就這樣, 22鬼常常將他扔進火裡或水裡,要害他的命。如果你能,求你憐憫我們,幫助我們吧!」

23耶穌說:「如果你能?對於相信的人,凡事都有可能!」

24孩子的父親立刻喊著說:「我信!但我信心不足,求你幫助我!」

25耶穌看見人群都跑了過來,就斥責那污鬼:「你這個聾啞鬼,我命令你從他身上出來,不許再進去!」

26那鬼發出喊叫,使孩子劇烈地抽搐了一陣,就出來了。孩子躺在地上一動也不動,大家都以為他死了。 27但耶穌拉著他的手扶他起來,他就站了起來。

28耶穌進屋後,門徒悄悄問祂:「我們為什麼趕不走那鬼呢?」

29耶穌說:「要趕走這類鬼只有靠禱告9·29 禱告」有古卷作「禱告和禁食」。。」

再次預言受難

30他們離開那裡,途經加利利。耶穌不想任何人知道祂的行蹤, 31因為祂在教導門徒。祂說:「人子將被交在人的手中,被他們殺害,但三天之後,祂必復活。」 32門徒卻不明白這句話的意思,又不敢問祂。

誰最偉大

33他們回到迦百農的住所,耶穌問門徒:「你們一路上爭論些什麼?」

34他們都沉默不語,因為剛才他們在爭論誰最偉大。 35耶穌坐下,叫十二個門徒過來,對他們說:「誰想為首,就該在眾人中做最小的,作眾人的僕人。」 36祂領了一個小孩子來,叫他站在門徒中間,又抱起他,對他們說: 37「任何人為我的緣故接待這樣一個小孩子,就是接待我;凡接待我的,不單是接待我,也是接待差我來的那位。」

警戒犯罪

38約翰對耶穌說:「老師,我們看見有人奉你的名趕鬼,就阻止他,因為他不是跟從我們的。」

39耶穌說:「不要阻止他,因為沒有人奉我的名行過神蹟後,會很快毀謗我。 40不反對我們的,就是支持我們的。 41我實在告訴你們,若有人因為你們屬於基督而給你們一杯水喝,他也必得到賞賜。

42「但若有人使這樣一個小信徒失足犯罪,他的下場比把大磨石掛在他脖子上扔到海裡還要慘。 43如果你一隻手使你犯罪,就砍掉它! 44拖著殘廢的身體進入永生,勝過雙手健全卻落入地獄不滅的火中。 45倘若你一隻腳使你犯罪,就砍掉它!瘸著腿進入永生, 46勝過雙腳健全卻被丟進地獄! 47如果你的一隻眼睛使你犯罪,就剜掉它!獨眼進上帝的國,勝過雙目健全卻被丟進地獄。 48在那裡,

『蟲是不死的,

火是不滅的。』

49「每個人都要被火煉,像被鹽醃一樣。 50鹽是好東西,但如果失去鹹味,怎能使它再鹹呢?你們裡面要有鹽,要彼此和睦。」