ማርቆስ 16 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 16:1-20

ትንሣኤው

16፥1-8 ተጓ ምብ – ማቴ 28፥1-8ሉቃ 24፥1-10

1ሰንበት ካለፈ በኋላ መግደላዊት ማርያም፣ የያዕቆብ እናት ማርያምና ሰሎሜ ሄደው የኢየሱስን ሥጋ ለመቀባት ሽቱ ገዙ። 2በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን ጧት በማለዳ፣ ገና ፀሓይ እንደ ወጣች፣ ወደ መቃብሩ በመሄድ ላይ ሳሉ፣ 3“ድንጋዩን ከመቃብሩ ደጃፍ ላይ ማን ያንከባልልልናል?” በማለት እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር።

4ቀና ብለው ሲመለከቱ፣ በጣም ትልቅ የነበረው ድንጋይ ከደጃፉ ላይ ተንከባልሎ አዩ። 5ወደ መቃብሩ እንደ ገቡም፣ ነጭ ልብስ የለበሰ ጕልማሳ በቀኝ በኩል ተቀምጦ አዩና ደነገጡ።

6እርሱ ግን እንዲህ አላቸው፤ “አትደንግጡ፤ የምትፈልጉት የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ነው፤ እርሱ ተነሥቷል፤ እዚህ የለም፤ እርሱን ያኖሩበት ስፍራ ይኸውላችሁ። 7ነገር ግን ሄዳችሁ ለደቀ መዛሙርቱና ለጴጥሮስ፣ ‘ቀድሟችሁ ወደ ገሊላ ይሄዳል፤ እንደ ነገራችሁ እዚያ ታገኙታላችሁ’ ብላችሁ ንገሯቸው።”

8ሴቶቹም እየተንቀጠቀጡና እየተደነቁ ከመቃብሩ ሸሽተው ወጡ፤ ፈርተው ስለ ነበር ለማንም አንዳች አልተናገሩም።

9በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን ማለዳ ከሙታን ከተነሣ በኋላ፣ ሰባት አጋንንት ላወጣላት ለማርያም መግደላዊት በመጀመሪያ ታየ። 10እርሷም ሄዳ፣ ከእርሱ ጋር የነበሩት እያዘኑ ሲያለቅሱ አግኝታ፣ 11እርሱ ሕያው መሆኑንና ለእርሷም መታየቱን ነገረቻቸው፤ እነርሱ ግን አላመኗትም።

12ከዚህ በኋላ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱ ወደ ገጠር ሲሄዱ በሌላ መልክ ታያቸው። 13እነርሱም ተመልሰው ይህንኑ ለቀሩት ነገሯቸው፤ ይሁን እንጂ እነርሱንም አላመኗቸውም።

14ከዚያም ዐሥራ አንዱ በማእድ ላይ ሳሉ ተገለጠላቸው፤ ከተነሣ በኋላ ያዩት ሰዎች የነገሯቸውን ስላላመኗቸው፣ አለማመናቸውንና የልባቸውን ድንዳኔ ነቀፈ። 15እንዲህም አላቸው፤ “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፤ 16ያመነ የተጠመቀ ይድናል፤ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። 17የሚያምኑትን እነዚህ ምልክቶች ይከተሏቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ልሳንም ይናገራሉ፤ 18እባቦችን በእጃቸው ይይዛሉ፤ የሚገድል መርዝ ቢጠጡ እንኳ አይጐዳቸውም፤ እጃቸውንም በሕመምተኞች ላይ ይጭናሉ፤ እነርሱም ይፈወሳሉ።”

19ጌታ ኢየሱስ ይህን ከተናገራቸው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ። 20ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ወጥተው፣ በየስፍራው ሁሉ ሰበኩ፤ ጌታም ከእነርሱ ጋር ይሠራ ነበር፤ ትምህርታቸውንም ተከትለው በሚፈጸሙ ምልክቶች ቃሉን ያጸና ነበር።16፥20 አንዳንድ የጥንት ቅጆች ከ9-20 ያለው ክፍል የላቸውም።

Thai New Contemporary Bible

มาระโก 16:1-20

การคืนพระชนม์

(มธ.28:1-8; ลก.24:1-10)

1เมื่อวันสะบาโตผ่านไปมารีย์ชาวมักดาลา มารีย์มารดาของยากอบ และสะโลเมซื้อเครื่องหอมมาเพื่อชโลมพระศพพระเยซู 2เช้าตรู่วันต้นสัปดาห์พอดวงอาทิตย์ขึ้นพวกเขามายังอุโมงค์ 3และถามกันว่า “ใครจะช่วยกลิ้งหินจากปากอุโมงค์?”

4แต่เมื่อมองไปก็เห็นหินก้อนนั้นซึ่งใหญ่มากถูกกลิ้งออกไปแล้ว 5เมื่อเข้าไปในอุโมงค์ก็เห็นชายหนุ่มคนหนึ่งสวมชุดสีขาวนั่งอยู่ทางขวาพวกนางก็ตกใจกลัว

6ผู้นั้นกล่าวว่า “อย่าตื่นตกใจไปเลย พวกเจ้ามาหาพระเยซูแห่งนาซาเร็ธผู้ถูกตรึงตายบนไม้กางเขน พระองค์ทรงเป็นขึ้นแล้ว! พระองค์ไม่ได้อยู่ที่นี่ จงดูที่ที่เขาวางพระศพเถิด 7จงไปบอกพวกสาวกรวมทั้งเปโตรว่า ‘พระองค์กำลังเสด็จไปแคว้นกาลิลีก่อนหน้าพวกท่าน ท่านจะพบพระองค์ที่นั่นดังที่พระองค์ได้ตรัสไว้’ ”

8ผู้หญิงเหล่านั้นตกตะลึงกลัวจนตัวสั่น จึงพากันออกจากอุโมงค์อย่างรวดเร็ว พวกเขาไม่ได้พูดอะไรกับใครเพราะกลัว

(สำเนาต้นฉบับเก่าแก่ที่น่าเชื่อถือมากที่สุดและหลักฐานโบราณบางฉบับไม่มีพระธรรมมาระโก 16:9-20)

9เช้าตรู่วันต้นสัปดาห์เมื่อพระเยซูทรงเป็นขึ้น พระองค์ทรงปรากฏแก่มารีย์ชาวมักดาลาเป็นคนแรก คือมารีย์คนที่พระเยซูทรงขับผีออกเจ็ดตน 10มารีย์จึงไปบอกบรรดาผู้ที่อยู่กับพระองค์ พวกเขากำลังร้องไห้ทุกข์โศกอยู่ 11เมื่อพวกเขาได้ยินว่าพระองค์ทรงพระชนม์อยู่และมารีย์ได้เห็นพระองค์ พวกเขาก็ไม่เชื่อ

12ภายหลังพระเยซูทรงปรากฏในพระกายอีกรูปหนึ่งแก่สาวกสองคนขณะที่พวกเขาเดินอยู่นอกเมือง 13ทั้งสองกลับมาเล่าให้คนอื่นๆ ฟัง แต่พวกนั้นก็ไม่เชื่ออีกเหมือนกัน

14ต่อมาพระเยซูทรงปรากฏแก่สาวกสิบเอ็ดคนนั้นขณะที่พวกเขากำลังรับประทานอาหาร พระองค์ทรงตำหนิพวกเขาที่ขาดความเชื่อและดื้อรั้นไม่ยอมเชื่อผู้ที่เห็นพระองค์หลังจากพระองค์ทรงเป็นขึ้นมาแล้ว

15พระองค์ตรัสกับพวกเขาว่า “จงออกไปทั่วโลก ประกาศข่าวประเสริฐแก่คนทั้งปวง 16ผู้ใดเชื่อและรับบัพติศมาจะรอด ส่วนผู้ที่ไม่เชื่อจะถูกตัดสินโทษ 17ผู้ที่เชื่อจะมีหมายสำคัญดังนี้คือ เขาทั้งหลายจะขับผีออกโดยนามของเรา เขาจะพูดภาษาใหม่ๆ 18เขาจะจับงูด้วยมือเปล่า และเมื่อดื่มพิษร้ายเขาจะไม่เป็นอันตรายเลย เขาจะวางมือให้คนเจ็บคนป่วยและคนเหล่านั้นจะหายโรค”

19เมื่อองค์พระเยซูเจ้าตรัสจบแล้วพระองค์ก็ทรงถูกรับขึ้นสู่สวรรค์และประทับนั่งที่เบื้องขวาพระหัตถ์ของพระเจ้า 20ฝ่ายเหล่าสาวกออกไปเทศนาทุกหนทุกแห่ง องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงร่วมงานกับเขาและรับรองพระดำรัสของพระองค์โดยหมายสำคัญที่เกิดขึ้น