ማርቆስ 15 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 15:1-47

ኢየሱስ በጲላጦስ ፊት

15፥2-15 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥11-26ሉቃ 23፥2318-25ዮሐ 18፥29–19፥16

1ጧት በማለዳ የካህናት አለቆች ከሽማግሌዎች፣ ከጸሓፍትና ከመላው የሸንጎ አባላት ጋር ወዲያው ከተማከሩ በኋላ፣ ኢየሱስን አስረው ወሰዱት፤ ለጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት።

2ጲላጦስም፣ “አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን?”

ሲል ጠየቀው፤ ኢየሱስም፣ “አንተው አልኸው፣” በማለት መለሰለት።

3የካህናት አለቆችም በብዙ ነገር ከሰሱት። 4ጲላጦስም፣ “ለምን መልስ አትሰጥም? እነሆ፤ በብዙ ነገር ከስሰውሃል” ሲል እንደ ገና ጠየቀው።

5ኢየሱስ ግን ምንም አልመለሰም፤ ጲላጦስ ተገረመ።

6በበዓል ሕዝቡ እንዲፈታላቸው የሚጠይቁትን እስረኛ የመልቀቅ ልማድ ነበር። 7በዐመፃ ተነሣሥተው ነፍስ ከገደሉ ዐመፀኞች ጋር የታሰረ በርባን የሚባል አንድ ሰው ነበረ። 8ሕዝቡም መጥተው እንደተለመደው እንዲያደርግላቸው ጲላጦስን ለመኑት።

9ጲላጦስም፣ “የአይሁድን ንጉሥ እንድፈታላችሁ ትፈልጋላችሁን?” ሲል ጠየቃቸው፤ 10ምክንያቱም የካህናት አለቆች ኢየሱስን አሳልፈው የሰጡት በቅናት መሆኑን ያውቅ ነበር። 11የካህናት አለቆች ግን በርባንን በእርሱ ምትክ እንዲፈታላቸው እንዲጠይቁ ሕዝቡን አነሣሡ።

12ጲላጦስም እንደ ገና፣ “እንግዲያው የአይሁድ ንጉሥ የምትሉትን ምን እንዳደርገው ትፈልጋላችሁ?” አላቸው።

13እነርሱም እንደ ገና፣ “ስቀለው!” እያሉ ጮኹ።

14ጲላጦስም፣ “ለምን? ምን የፈጸመው ወንጀል አለ” አላቸው።

እነርሱ ግን፣ “ስቀለው!” እያሉ የባሰ ጮኹ።

15ጲላጦስም ሕዝቡን ደስ ለማሰኘት ሲል በርባንን ፈታላቸው፤ ኢየሱስን ግን ገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠው።

ወታደሮች በኢየሱስ ላይ አፌዙ

15፥16-20 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥27-31

16ወታደሮቹ ፕራይቶሪዮን ወደ ተባለ ወደ ገዥው ግቢ ወሰዱት፤ ሰራዊቱንም ሁሉ በአንድነት ሰበሰቡ። 17ቀይ ልብስም አለበሱት፤ የእሾኽ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ ደፉበት። 18ከዚያም፣ “የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፤ ሰላም ለአንተ ይሁን!” እያሉ እጅ ነሡት፤ 19ራሱንም በበትር መቱት፤ ተፉበትም፤ ተንበርክከውም ሰገዱለት። 20ካፌዙበት በኋላም ቀዩን ልብስ ገፈፉት፤ የገዛ ልብሱን አለበሱት፤ ሊሰቅሉትም ወሰዱት።

የኢየሱስ ስቅለት

15፥22-32 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥33-44ሉቃ 23፥33-43ዮሐ 19፥17-24

21የአሌክሳንድሮስና የሩፎስ አባት ስምዖን የተባለ አንድ የቀሬና ሰው ከገጠር ሲመጣ መስቀሉን እንዲሸከም አስገደዱት። 22ከዚያም ኢየሱስን፣ ትርጕሙ “የራስ ቅል ስፍራ” ወደ ተባለ ወደ ጎልጎታ ወሰዱት። 23ከከርቤ ጋር የተቀላቀለ የወይን ጠጅም ሰጡት፤ እርሱ ግን አልተቀበለም። 24ከዚያም ሰቀሉት፤ እያንዳንዱም ምን እንደሚደርሰው ለማወቅ ዕጣ ተጣጥለው ልብሱን ተከፋፈሉ።

25ሲሰቅሉትም ጊዜው ከጧቱ ሦስት ሰዓት ነበረ። 26የክሱ ጽሑፍም፣ “የአይሁድ ንጉሥ” የሚል ነበር። 27ከእርሱም ጋር ሁለት ወንበዴዎችን አንዱን በቀኙ አንዱን በግራው ሰቀሉ። 28መጽሐፍ፣ “ከዐመፀኞች ጋር ተቈጠረ” ያለውም በዚሁ ተፈጸመ።15፥28 አንዳንድ ቅጆች 28 የላቸውም (ኢሳ 53፥12)። 29በመንገድ የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ የስድብ ናዳ በማውረድ እንዲህ ይሉት ነበር፤ “አዬ! ቤተ መቅደስን አፍርሰህ በሦስት ቀን የምትሠራ አንተ ነህ፤ 30እስቲ አሁን ከመስቀል ውረድና ራስህን አድን።”

31እንዲሁም የካህናት አለቆችና ጸሐፍት በማሾፍ እርስ በርሳቸው እንዲህ አሉ፤ “ሌሎችን አዳነ፤ ራሱን ግን ማዳን አልቻለም፤ 32አይተን እናምን ዘንድ ይህ ክርስቶስ15፥32 ወይም መሲሕ፣ ይህ የእስራኤል ንጉሥ እስቲ ከመስቀል ይውረድ።” ከእርሱ ጋር የተሰቀሉትም እንደዚሁ የስድብ ናዳ ያወርዱበት ነበር።

የኢየሱስ መሞት

15፥33-41 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥45-56ሉቃ 23፥44-49

33ከስድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ። 34በዘጠኝም ሰዓት ኢየሱስ፣ “ኤሎሄ፣ ኤሎሄ፣ ላማ ሰበቅታኒ?” ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ትርጓሜውም “አምላኬ፣ አምላኬ፣ ለምን ተውኸኝ?” ማለት ነው።

35በዚያ ቆመው ከነበሩት አንዳንዶቹ ይህን ሲሰሙ፣ “ኤልያስን ይጣራል” አሉ።

36ከዚያም አንድ ሰው ፈጥኖ ሄዶ የሆመጠጠ የወይን ጠጅ በሰፍነግ ነከረ፤ በዘንግም ሰክቶ እንዲጠጣው ለኢየሱስ አቀረበለት፤ ከዚያም፣ “ተዉት፤ እስቲ ኤልያስ መጥቶ ሲያወርደው እናያለን” አለ።

37ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኾ፤ ነፍሱን ሰጠ።

38የቤተ መቅደሱም መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ። 39በኢየሱስ ትይዩ ቆሞ የነበረውም የመቶ አለቃ እንደዚህ ጮኾ15፥39 አንዳንድ ቅጆች እንደዚህ ጮኾ የሚለው ሐረግ የላቸውም። ነፍሱን ሲሰጥ ባየ ጊዜ፣ “ይህ ሰው በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበር” አለ።

40በዚህ ጊዜ ሴቶች ከሩቅ ሆነው ይመለከቱ ነበር፤ ከእነርሱም መካከል መግደላዊት ማርያም፣ የታናሹ ያዕቆብና የዮሳ እናት ማርያም፣ እንዲሁም ሰሎሜ ነበሩ፤ 41እነዚህ ሴቶች በገሊላ ሲከተሉትና ሲያገለግሉት የነበሩ ናቸው፤ ደግሞም አብረውት ወደ ኢየሩሳሌም የመጡ ሌሎች ብዙ ሴቶች ነበሩ።

የኢየሱስ መቀበር

15፥42-47 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥57-61ሉቃ 23፥50-56ዮሐ 19፥38-42

42ጊዜው እየመሸ መጥቶ የሰንበት ዋዜማ ይኸውም የመዘጋጀት ቀን ሆነ፤ 43የተከበረ የሸንጎ አባልና የእግዚአብሔርን መንግሥት ይጠባበቅ የነበረው የአርማትያሱ ዮሴፍ በድፍረት ወደ ጲላጦስ ሄዶ የኢየሱስን ሥጋ ለመነው። 44ጲላጦስም እንዲህ በቶሎ መሞቱን ሲሰማ ተደነቀ፤ የመቶ አለቃውንም ጠርቶ ከሞተ ምን ያህል ጊዜ እንደ ሆነ ጠየቀው፤ 45መሞቱንም ከመቶ አለቃው ካረጋገጠ በኋላ ሥጋውን ለዮሴፍ ሰጠው። 46ዮሴፍም በፍታ ገዛ፤ ሥጋውንም አውርዶ በበፍታው ከከፈነው በኋላ፣ ከዐለት በተወቀረ መቃብር አኖረው፤ የመቃብሩንም ደጃፍ በድንጋይ ገጠመው። 47ማርያም መግደላዊትና የዮሳ እናት ማርያም የት እንዳኖሩት ይመለከቱ ነበር።

Knijga O Kristu

Marko 15:1-47

Isus pred Pilatom

(Mt 27:1-2, 11-14; Lk 23:1-5; Iv 18:28-38)

1Već rano ujutro sastanu se svećenički poglavari, starješine i pismoznanci—cijelo Veliko vijeće—te Isusa svežu i odvedu rimskome upravitelju Pilatu.

2Pilat ga upita: “Jesi li ti kralj Židova?”

“Ti to kažeš”, odgovori mu Isus.

3Svećenički ga poglavari optuže za mnoge zločine. 4Pilat ga ponovno upita: “Zar nemaš ništa na to reći? Gledaj kako te optužuju!” 5Isus mu više ništa ne odgovori, što je Pilata veoma začudilo.

Isusa osuđuju na smrt

(Mt 27:15-26; Lk 23:13-25; Iv 18:39—19:16)

6Bio je, međutim, običaj da rimski upravitelj svake godine o blagdanu Pashe pusti na slobodu jednoga židovskog zatvorenika kojega narod zatraži. 7U to je vrijeme jedan od zatvorenika bio Baraba, osuđen s drugim prevratnicima za ubojstvo u pobuni. 8Svjetina se počne okupljati pred Pilatom tražeći da, prema običaju, oslobodi jednog zatvorenika.

9“Hoćete li da oslobodim židovskoga kralja?” upita Pilat. 10Znao je, naime, da su ga svećenički poglavari predali sudu iz zavisti. 11Ali svećenički poglavari podjare svjetinu da zatraži slobodu za Barabu.

12“A što da onda učinim s ovim kojega nazivate kraljem Židova?”

13A oni opet poviču: “Raspni ga!”

14“Zbog čega?” upita Pilat. “Kakvo je zlo učinio?”

Ali oni su samo još glasnije vikali: “Raspni ga!”

15I tako Pilat, želeći ugoditi svjetini, oslobodi Barabu, a Isusa izbičuje i preda da ga raspnu.

Vojnici se izruguju Isusu

(Mt 27:27-31; Iv 19:2-3)

16Vojnici ga odvedu u palaču, u takozvani pretorij, i sazovu cijelu četu. 17Obuku ga u grimiz i ispletu krunu od trnja te mu stave na glavu. 18Pozdravljali su ga povicima: “Živio kralj Židova!” 19Udarali su ga štapom po glavi, pljuvali po njemu i padali na koljena da mu se “klanjaju”. 20Kad su mu se izrugali, skinu s njega grimiz, odjenu ga u njegovu odjeću i odvedu da ga raspnu.

Isusa raspinju na križ

(Mt 27:32-44; Lk 23:26-43; Iv 19:16-27)

21Natjeraju nekog prolaznika, Šimuna iz Cirene,15:21 Grad u sjevernoj Africi. koji se baš tada vraćao iz polja, da ponese Isusov križ (Šimun bijaše Aleksandrov i Rufov otac). 22Dovedu tako Isusa do mjesta zvanoga Golgota (što znači: “Lubanjsko mjesto”). 23Ponude mu vino s opojnim gorkim travama,15:23 U grčkome: sa smirnom. ali on nije htio piti. 24Kad su ga raspeli, bace kocku te tako razdijele među sobom njegovu odjeću.15:24 Psalam 22:19.

25Raspeli su ga u devet sati ujutro.15:25 U grčkome: A bijaše treća ura i raspeli su ga. 26Iznad njega je stajao natpis o njegovoj krivnji: “Kralj Židova”. 27S njime su raspeli i dvojicu prevratnika, jednoga njemu zdesna, a drugoga slijeva.15:27 U nekim je rukopisima dodan i 28. stih: Time se ispunilo ono što je zapisano u Svetom pismu: Тиме се испунило оно што је записано у Светом писму: “i među zlikovce bio ubrojen” 29Prolaznici su ga ružili i odmahivali glavom govoreći: “Možeš srušiti Hram i sam ga opet izgraditi u tri dana, je li? 30Spasi onda sebe i siđi s križa!”

31Slično su mu se rugali i svećenički poglavari i pismoznanci: “Spasio je druge, a sebe ne može spasiti! 32Mesija! Kralj Izraelov! Neka sada siđe s križa da vidimo, pa da vjerujemo!” Vrijeđali su ga čak i prevratnici raspeti skupa s njim.

Isusova smrt

(Mt 27:45-56; Lk 23:44-49; Iv 19:28-30)

33O podnevu po svoj zemlji nastane tama i potraje do tri ure.15:33 U grčkome: od šestoga do devetog sata, po rimskome računanju vremena prema kojemu je dan počinjao u šest sati ujutro. 34U tri sata Isus glasno poviče: “Eloi, Eloi, lema sabahtani!”, (što znači: “Bože moj, Bože moj, zašto si me ostavio?”)15:34 Vidjeti Psalam 22:1.

35“Zove Iliju!” rekoše neki od nazočnih kad su to čuli. 36A neki čovjek otrči uzeti spužvu te ju namoči u ocat i natakne na trsku te mu pruži piti. “Da vidimo hoće li doći Ilija i skinuti ga”, reče.

37A Isus još jedanput glasno krikne i izdahne.

38Nato se zastor u Hramu razdere napola od vrha do dna. 39Kad je rimski stotnik koji je stajao nasuprot Isusu vidio kako je izdahnuo, reče: “Ovaj je čovjek zaista bio Božji Sin!”

40Bile su tu i žene koje su promatrale izdaleka—Marija iz Magdale, Marija, majka Jakova mlađega i Josije, te Saloma, 41koje su ga pratile i služile mu dok je bio u Galileji. S njim su došle u Jeruzalem.

Isusov ukop

(Mt 27:57-61; Lk 23:50-56; Iv 19:38-42)

42Sve se to događalo u petak, na dan Priprave, dan uoči Subote. Kad je pala večer, 43Josip iz Arimateje, ugledan član Velikoga vijeća koji je također iščekivao Božje kraljevstvo, odvaži se te uđe k Pilatu zatražiti Isusovo tijelo. 44Pilat se veoma začudi da je Isus već umro, pa pozove dežurnoga rimskog stotnika da ga upita je li mrtav. 45Stotnik odgovori da jest, pa Pilat preda Josipu Isusovo mrtvo tijelo. 46Josip kupi platna, skine Isusovo tijelo s križa, umota ga u platno i položi u grob isklesan u stijeni te na ulaz navali kamen. 47Marija iz Magdale i Marija majka Josijina gledale su kamo ga polažu.