ማርቆስ 12 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 12:1-44

የወይን ስፍራ የተከራዩ ገበሬዎች ምሳሌ

12፥1-12 ተጓ ምብ – ማቴ 21፥33-46ሉቃ 20፥9-19

1ከዚያም እንዲህ እያለ በምሳሌ ይነግራቸው ጀመር፤ “አንድ ሰው ወይን ተከለ፤ ዙሪያውን ዐጠረ፤ ለመጭመቂያው ጕድጓድ ቈፈረ፤ የመጠበቂያም ማማ ሠራለት፤ ከዚያም ለገበሬዎች አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ። 2በመከር ጊዜም ከወይኑ ፍሬ እንዲያመጣለት ከአገልጋዮቹ አንዱን ወደ ገበሬዎቹ ላከ። 3እነርሱ ግን ይዘው ደበደቡት፤ ባዶ እጁንም ሰደዱት። 4እንደ ገናም ሌላ አገልጋይ ላከ። እነርሱም ራሱን ፈንክተውና አዋርደው መለሱት። 5አሁንም እንደ ገና ሌላ ላከ፤ ይህኛውንም ገደሉት፤ ከሌሎች ከብዙዎቹ መካከል አንዳንዶቹን ደበደቡ፤ አንዳንዶቹንም ገደሉ።

6“አሁንም የሚላክ ሌላ ነበረው፤ እርሱም የሚወድደው ልጁ ነበረ፤ ‘ልጄንስ ያከብሩታል’ በማለት ከሁሉ በኋላ ላከው።

7“ገበሬዎቹ ግን እርስ በርሳቸው፣ ‘ይህማ ዋናው ወራሹ ነው፤ ኑ እንግደለው፤ ርስቱ የእኛ ይሆናል’ ተባባሉ፤ 8ከዚያም ይዘው ገደሉት፤ ከወይኑ ስፍራም አውጥተው ጣሉት።

9“እንግዲህ የወይኑ አትክልት ባለቤት ምን የሚያደርግ ይመስላችኋል? ይመጣል፤ ገበሬዎቹን ይገድላል፤ የወይኑንም አትክልት ለሌሎች ይሰጣል። 10እንዲህ የሚለውን የመጽሐፍ ቃል አላነበባችሁምን፤

“ ‘ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣

እርሱ የማእዘን ራስ12፥10 ወይም የማእዘን ድንጋይ ሆነ፤

11ጌታ ይህን አድርጓል፣

ይህም ለዐይናችን ድንቅ ነው’?”

12ምሳሌውን የተናገረው ስለ እነርሱ መሆኑን ስላወቁ፣ ሊይዙት ፈለጉ፤ ነገር ግን ሕዝቡን ስለ ፈሩ ትተውት ሄዱ።

ለቄሳር ግብር ስለ መክፈል

12፥13-17 ተጓ ምብ – ማቴ 22፥15-22ሉቃ 20፥20-26

13ከዚያም በነገር እንዲያጠምዱት ከፈሪሳውያንና ከሄሮድስ ወገን ሰዎች ወደ እርሱ ላኩ። 14እነርሱም መጥተው እንዲህ አሉት፤ “መምህር ሆይ፤ አንተ ትክክለኛ ሰው መሆንህን እናውቃለን፤ የሰዎች ማንነት ስለማይገድህም አታዳላም፤ የእግዚአብሔርን መንገድ ብቻ በእውነት ታስተምራለህ፤ ለመሆኑ ለቄሳር ግብር መክፈል ይገባል ወይስ አይገባም? 15እኛስ እንክፈል ወይስ አንክፈል?”

ኢየሱስ ግን ግብዝነታቸውን ዐውቆ፣ “ለምን ልታጠምዱኝ ትፈልጋላችሁ? እስቲ አንድ ዲናር አምጡልኝና ልየው” አላቸው። 16እነርሱም አመጡለት፣ “ይህ የማን መልክ ነው? ጽሕፈቱስ የማን ነው?”

አላቸው፤ እነርሱም፣ “የቄሳር ነው” አሉት።

17ኢየሱስም፣ “የቄሳርን ለቄሳር፣ የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ” አላቸው። እነርሱም በእርሱ ተደነቁ።

ጋብቻና ትንሣኤ

12፥18-27 ተጓ ምብ – ማቴ 22፥23-33ሉቃ 20፥27-38

18ከዚህ በኋላ የሙታን ትንሣኤ የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ መጥተው እንዲህ ሲሉ ጠየቁት፤ 19“መምህር ሆይ፤ የአንድ ሰው ወንድም ሚስት አግብቶ ልጅ ሳይወልድ ቢሞት፣ ይህ ሰው ሴትየዋን አግብቶ ለወንድሙ ዘር እንዲተካ ሙሴ ጽፎልናል። 20ታዲያ ሰባት ወንድማማቾች ነበሩ፤ የመጀመሪያው አግብቷት ዘር ሳይተካ ሞተ፤ 21ሁለተኛውም ሴትየዋን አገባት፤ እርሱም ዘር ሳይተካ ሞተ፤ ሦስተኛውም እንዲሁ፤ 22ሰባቱም አገቧት፤ ዘር ግን አልተኩም፤ በመጨረሻም ሴትየዋ ሞተች። 23እንግዲህ፣ ሰባቱም አግብተዋታልና በትንሣኤ12፥23 አንዳንድ ቅጆች በትንሣኤ ሰዎች ከሙታን ሲነሡ የሚል አላቸው ለማናቸው ሚስት ልትሆን ነው?” አሉት።

24ኢየሱስም፣ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “የምትስቱት እኮ ቅዱሳት መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታውቁ ነው! 25ሙታን በሚነሡበት ጊዜ እንደ ሰማይ መላእክት ይሆናሉ እንጂ አያገቡም፤ አይጋቡም። 26ስለ ሙታን መነሣት ግን፣ በሙሴ መጽሐፍ ይኸውም ስለ ቍጥቋጦው በተነገረው ክፍል፣ እግዚአብሔር ‘እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ’ ያለውን አላነበባችሁምን? 27እግዚአብሔር የሕያዋን አምላክ እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም፤ ስለዚህ እጅግ ተሳስታችኋል።”

ከሁሉ የሚበልጠው ትእዛዝ

12፥28-34 ተጓ ምብ – ማቴ 22፥34-40

28ከጸሐፍትም አንዱ መጥቶ ሲከራከሩ ሰማቸው፤ ኢየሱስ ለቀረበለት ጥያቄ ተገቢውን መልስ መስጠቱን አስተውሎ፣ “ለመሆኑ ከትእዛዞች ሁሉ የሚበልጠው የትኛው ነው?” ሲል ጠየቀው።

29ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰለት፤ “ከሁሉ የሚበልጠው ይህ ነው፤ ‘እስራኤል ሆይ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፤ 30አንተም ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ሐሳብህና በፍጹም ኀይልህ ውደድ።’ 31ሁለተኛውም ይህ ነው፤ ‘ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ።’ ከእነዚህም የሚበልጥ ትእዛዝ የለም።”

32ጸሓፊውም እንዲህ አለው፤ “መምህር ሆይ፤ መልካም ብለሃል፤ እርሱ አንድ መሆኑን፣ ከእርሱም ሌላ አለመኖሩን መናገርህ ትክክል ነው፤ 33እርሱን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም አእምሮህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ኀይልህ መውደድ፣ እንዲሁም ባልንጀራህን እንደ ራስህ መውደድ ከሚቃጠል መሥዋዕት ሁሉና ከሌሎችም መሥዋዕቶች ይበልጣል።”

34ኢየሱስም በማስተዋል እንደ መለሰለት አይቶ፣ “አንተ ከእግዚአብሔር መንግሥት የራቅህ አይደለህም” አለው። ከዚህ በኋላ ሊጠይቀው የደፈረ ማንም አልነበረም።

ክርስቶስ የማን ልጅ ነው?

12፥35-37 ተጓ ምብ – ማቴ 24፥41-46ሉቃ 20፥41-44

12፥38-40 ተጓ ምብ – ማቴ 23፥1-7ሉቃ 20፥45-47

35ኢየሱስ በቤተ መቅደሱ አደባባይ በሚያስተምርበት ጊዜ እንዲህ ሲል ጥያቄ አቀረበ፤ “ጸሐፍት እንዴት ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ነው ይላሉ? 36ዳዊት በመንፈስ ቅዱስ ሲናገር፣

“ ‘ጌታ ጌታዬን፣

“ጠላቶችህን ከእግርህ በታች

እስካደርጋቸው ድረስ

በቀኜ ተቀመጥ” ’ አለው። ይላል፤

37ታዲያ ዳዊት ራሱ ‘ጌታ’ ካለው፣ እንዴት ተመልሶ ልጁ ይሆናል?” ብዙ ሕዝብም በደስታ ይሰማው ነበር።

38በሚያስተምርበትም ጊዜ እንዲህ አለ፤ “ከጸሐፍት ተጠንቀቁ፤ የተንዘረፈፈ ቀሚስ ለብሰው መዞርን ይወድዳሉ፤ በየአደባባዩም የአክብሮት ሰላምታ ይሻሉ፤ 39በምኵራብ ከፍተኛውን ወንበር፣ በግብዣም ቦታ የከበሬታን ስፍራ ይፈልጋሉ፤ 40በረጅም ጸሎታቸው እያሳበቡ የመበለቶችን ቤት ያራቍታሉ፤ እነዚህ የባሰ ፍርድ ይቀበላሉ።”

የመበለቲቱ ስጦታ

12፥41-44 ተጓ ምብ – ሉቃ 21፥1-4

41ኢየሱስ በገንዘብ ማስቀመጫው አንጻር ተቀምጦ፣ ብዙ ሰዎች ስጦታቸውን ወደ ቤተ መቅደሱ ገንዘብ ማስቀመጫ ሣጥን ሲያስገቡ ይመለከት ነበር። ብዙ ሀብታሞች ብዙ ገንዘብ አስገቡ፤ 42አንዲት ምስኪን መበለት ግን ከአንድ ሳንቲም የማይበልጡ ሁለት የናስ ቤሳዎች አስገባች።

43ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ፣ እንዲህ አላቸው፤ “እውነት እላችኋለሁ፤ ይህች ድኻ መበለት ሣጥኑ ውስጥ ከጣሉት ከሌሎቹ የበለጠ አስገባች። 44እነዚህ ሁሉ ከተረፈው ሀብታቸው ሰጡ፤ እርሷ ግን በድኽነት ዐቅሟ ያላትን ሁሉ አውጥታ ለመኖሪያ የሚሆናትን እንዳለ ሰጠች።”

Knijga O Kristu

Marko 12:1-44

Prispodoba o zlim vinogradarima

(Mt 21:33-46; Lk 20:9-19)

1Tada im počne govoriti u prispodobama: “Neki čovjek posadi vinograd i ogradi ga, iskopa tijesak za grožđe i izgradi kulu. Zatim ga iznajmi vinogradarima i otputuje. 2Kad dođe vrijeme berbe, pošalje slugu da ubere njegov dio uroda. 3Ali vinogradari ga dograbe, pretuku i pošalju natrag praznih ruku. 4Vlasnik vinograda im zatim pošalje drugog slugu. Zakupci mu razbiju glavu i osramote ga. 5Trećega kojeg im je poslao ubiju. Poslao im je i mnoge druge, ali oni ih sve premlate ili ubiju.

6Preostao mu je samo još jedan: njegov ljubljeni sin. Pošalje napokon i njega misleći: ‘Prema mojem sinu sigurno će se odnositi s poštovanjem.’

7Ali kad vinogradari opaze da dolazi, rekoše: ‘Ovaj će naslijediti imanje. Ubijmo ga pa ćemo se domognuti imanja umjesto njega!’ 8Pa ga pograbe, ubiju i izbace tijelo iz vinograda.

9Što mislite da će učiniti vlasnik kad čuje što se dogodilo? Doći će i pobiti te vinogradare, a vinograd dati u najam drugima. 10Ne sjećate li se ulomka iz Svetog pisma:

‘Kamen koji su graditelji odbacili

postane ugaonim kamenom.

11To je Gospodnje djelo,

čudesno u našim očima.’?”12:10-11 Psalam 118:22-23.

12Židovski su ga vođe već tada htjeli uhvatiti jer su dobro znali da se ta prispodoba odnosi na njih, ali bojali su se mnoštva. Zato odu i ostave ga.

O porezu

(Mt 22:15-22; Lk 20:20-26)

13Vjerski mu vođe pošalju neke farizeje i Herodove sljedbenike da ga uhvate u riječi. 14Oni dođu i rekoše mu: “Učitelju, znamo da govoriš istinu i da si nepristran jer ne gledaš tko je tko, nego prema istini poučavaš putu Božjemu. Reci nam je li dopušteno plaćati porez caru ili nije.”

15Isus prozre njihovo licemjerje pa reče: “Zašto me kušate? Pokažite mi kovani novac12:15 U grčkome: denar. pa ću vam reći.” 16Donesu mu novčić, a on upita: “Čiji su ovo lik i natpis na kovanici?”

“Carevi”, odgovore.

17“Onda dajte caru carevo, ali Bogu valja dati Božje”, reče im. Bili su zadivljeni.

O uskrsnuću

(Mt 22:23-33; Lk 20:27-40)

18Tada dođu k njemu saduceji, koji tvrde da nema uskrsnuća, i upitaju ga: 19“Gospodine, Mojsije nam je dao zakon prema kojemu, umre li oženjen muškarac bez djece, njegov se brat mora oženiti njegovom udovicom kako bi ona rodila sina koji će naslijediti posjed umrloga i nositi njegovo ime.12:19 Ponovljeni zakon 25:5-6. 20Bilo je sedmero braće. Prvi se brat oženi i umre a da nije imao sina. 21Drugi se brat oženi njegovom udovicom, ali također umre a da nije ostavio sina. S trećim se dogodi isto. 22Tako nijedan od sedmorice ne ostavi potomstva. Na posljetku umre i žena. 23Čija će onda ona biti žena o uskrsnuću kad je bila udana za svu sedmoricu?”

24Isus im odgovori: “Niste li vi u zabludi zato što ne razumijete Sveto pismo ni Božju silu? 25Jer kad ljudi uskrsnu od mrtvih, neće se ženiti ni udavati, već će biti kao anđeli na nebu. 26A glede uskrsnuća, niste li u Knjizi Izlaska, ondje gdje piše kako je Mojsije ugledao gorući grm, pročitali da mu je Bog rekao: ‘Ja sam Bog Abrahamov, Izakov i Jakovljev’12:26 Izlazak 3:6. dugo nakon što su oni poumirali? 27A Bog nije Bog mrtvih, već Bog živih! Vi ste, prema tome, u velikoj zabludi!”

Najveća zapovijed

(Mt 22:34-40; Lk 10:25-28)

28Neki pismoznanac koji je ondje stajao shvatio je, slušajući raspravu, da je Isus dobro odgovorio pa ga upita: “Koja je najvažnija od svih zapovijedi?”

29Isus odgovori: “Najvažnija glasi:

‘Čuj, o Izraele! Naš Gospodin Bog jest jedini Bog.

30Ljubi Gospodina Boga svojega svim srcem svojim,

svom dušom svojom, svom pameti svojom i svom snagom svojom!’12:29-30 Ponovljeni zakon 6:4-5.

31Druga glasi:

‘Ljubi svojega bližnjega kao samoga sebe!’12:31 Levitski zakonik 19:18.

Nema zapovijedi koja bi bila veća od tih dviju.”

32Pismoznanac odgovori: “Učitelju, pravo si rekao da je Bog jedini i da nema drugih osim njega. 33Voljeti ga svim srcem, svim razumom i svom snagom, a bližnjega voljeti kao samoga sebe vrijedi više nego sve paljenice i ostale žrtve.”

34Videći da pametno govori, Isus mu reče: “Nisi daleko od Božjeg kraljevstva.” I nitko ga se više nije usudio išta pitati.

Čiji sin je Mesija

(Mt 22:41-46; Lk 20:41-44)

35Poučavajući u Hramu, Isus upita: “Kako pismoznanci mogu tvrditi da je Mesija Davidov sin? 36Pa sâm je David, nadahnut Svetim Duhom, rekao:

‘Gospodin je rekao mojem Gospodinu:

Sjedni mi s desne strane

dok ti ne bacim pod noge tvoje neprijatelje.’12:36 Psalam 110:1.

37Sâm ga je David nazvao svojim Gospodinom. Kako bi mu onda mogao biti sin?” Mnoštvo ga je oduševljeno slušalo.

Upozorenje protiv pismoznanaca

(Mt 23:1-7; Lk 11:43-46; 20:45-47)

38Poučavajući ih dalje, reče: “Čuvajte se pismoznanaca! Vole se šetati u dugim haljinama i da ih ljudi pozdravljaju na trgovima. 39U sinagogama vole sjediti na počasnim mjestima, a na gozbama na pročelju stola. 40Besramno troše udovička dobra, a prikrivaju se dugačkim molitvama u javnosti. Oni će biti strože kažnjeni.”

Udovičin dar

(Lk 21:1-4)

41Zatim ode sjesti do kutije za milodare te je promatrao mnoštvo kako ubacuje bakreni novac. Mnogi su bogataši ubacivali velike iznose. 42Dođe i neka siromašna udovica te ubaci samo dva novčića.12:42 U grčkome: dvije lepte.

43Isus dozove učenike i reče im: “Zaista vam kažem, ta je siromašna udovica ubacila više nego svi ostali skupa! 44Jer svi su oni dali od svojeg viška, a ona je, tako siromašna, dala sve što je imala.”