ማሕልየ መሓልይ 8 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማሕልየ መሓልይ 8:1-14

1ምነው አንተ የእናቴን ጡት እንደ ጠባ፣

እንደ ወንድሜ በሆንህ!

ከዚያም ውጭ ባገኝህ፣

እስምህ ነበር፤

ታዲያ ማንም ባልናቀኝ!

2እኔም ወደ አስተማረችኝ፣

ወደ እናቴም ቤት፣

እጅህን ይዤ በወሰድሁህ ነበር፤

የምትጠጣውን ጣፋጭ የወይን ጠጅ፣

የሮማኔን ጭማቂም በሰጠሁህ።

3ግራ እጁን ተንተርሻለሁ፤

ቀኝ እጁም ዐቅፎኛል።

4እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፤

ራሱ እስኪፈልግ ድረስ፣

ፍቅርን እንዳታስነሡት ወይም እንዳትቀሰቅሱት እማጠናችኋለሁ።

ባልንጀሮቿ

5ውዷን ተደግፋ፣

ከምድረ በዳ የምትወጣ ይህች ማን ናት?

ሙሽራዪቱ

ከእንኮይ ዛፍ ሥር አስነሣሁህ፤ በዚያ እናትህ ፀነሰችህ፤

በዚያም ታምጥ የነበረችው አንተን

ወለደችህ።

6በልብህ እንዳለ፣

በክንድህም እንደምትይዘው ማኅተም አስቀምጠኝ፤

ፍቅር እንደ ሞት የበረታች፣

ቅናቷም8፥6 ወይም ጥልቅ ስሜት እንደ መቃብር8፥6 ዕብራይስጡ ሲኦል ይለዋል ጨካኝ ናትና፤

እንደሚንቦገቦግ እሳት፣

እንደ ኀይለኛም ነበልባል ትነድዳለች።8፥6 ወይም እንደ እግዚአብሔር ነበልባል

7የውሃ ብዛት ፍቅርን ሊያጠፋ አይችልም፤

ፈሳሾችም አያሰጥሟትም፤

ሰው የቤቱን ሀብት ሁሉ

ስለ ፍቅር ቢሰጥ

ፈጽሞ ይናቃል።

ባልንጀሮቿ

8ትንሽ እኅት አለችን፤

ጡትም ገና አላወጣችም፤

ስለ እርሷ በምንጠየቅበት ቀን

ምን ማድረግ እንችል ይሆን?

9እርሷ ቅጥር ብትሆን፣

በላይዋ የብር መጠበቂያ ማማ እንሠራባታለን፤

በር ብትሆን፣

በዝግባ ዕንጨት እንከልላታለን።

ሙሽራዪቱ

10እነሆ እኔ ቅጥር ነኝ፤

ጡቶቼም እንደ ማማ ግንቦች ናቸው፤

እኔም በዐይኖቹ ፊት፣

ሰላምን እንደሚያመጣ ሰው ሆንሁ።

11ሰሎሞን በብኤላሞን የወይን ተክል ቦታ ነበረው፤

የወይኑን ተክል ቦታም ለአትክልተኞች አከራየው፤

እያንዳንዳቸውም የፍሬውን ዋጋ፣

አንድ አንድ ሺሕ ሰቅል ብር ያመጡለት ነበር።

12የወይኔ ተክል ቦታ የራሴ፣ የግሌ ነው፤

ሰሎሞን ሆይ፤ አንድ ሺሁ ሰቅል ለአንተ፤

ፍሬውን ለሚጠብቁ ደግም ሁለት መቶ ይሁን።

ሙሽራው

13አንቺ በአትክልቱ ቦታ የምትኖሪ ሆይ፤

ባልንጀሮቼ ድምፅሽን ይሰማሉ፤

እስቲ እኔም ልስማው።

ሙሽራዪቱ

14ውዴ ሆይ፤ ቶሎ ናልኝ፤

ሚዳቋን፣

ወይም በቅመም ተራራ ላይ የሚዘልል፣

የዋሊያን ግልገል ምሰል።

Thai New Contemporary Bible

เพลงโซโลมอน 8:1-14

1ถ้าเพียงแต่คุณเป็นพี่ชายของดิฉัน

ที่ดูดนมจากอกของแม่ดิฉัน!

ดิฉันก็จะจูบคุณได้

เมื่อพบคุณข้างนอก

และจะไม่มีใครเหยียดหยามดิฉัน

2ดิฉันจะพาคุณ

มายังบ้านแม่ของดิฉัน

ผู้ที่ได้สั่งสอนดิฉันมา

ดิฉันจะให้คุณดื่มเหล้าองุ่นใส่เครื่องเทศ

เป็นเหล้าทับทิมหวานละมุน

3แขนซ้ายของเขาช้อนประคองศีรษะของดิฉัน

และแขนขวาของเขาโอบกอดดิฉันไว้

4บรรดาสตรีชาวเยรูซาเล็มเอ๋ย เรากำชับเจ้าว่า

อย่าปลุกเร้าความรัก

แต่ปล่อยให้เป็นไปตามครรลองของมัน

เพื่อน

5นี่ใครหนอกำลังมาจากทะเลทราย

อิงแอบคู่รักของเธอมา?

หญิงสาว

ใต้ต้นแอปเปิ้ล ซึ่งแม่ของคุณให้กำเนิดคุณด้วยความเจ็บปวด

ดิฉันจะปลุกความรักของคุณที่นั่น

6โปรดให้ดิฉันเป็นดั่งดวงตราประทับที่ใจ

และที่แขนของคุณเพื่อแสดงว่าคุณเป็นของดิฉัน

เพราะความรักทรงอำนาจประหนึ่งความตาย

และความหึงหวง8:6 หรือความเร่าร้อนคงทนราวกับแดนผู้ตาย

ความรักนั้นแผดเผาดั่งไฟ

เสมือนเปลวไฟแรงกล้า8:6 หรือเปลวไฟขององค์พระผู้เป็นเจ้า

7ธารน้ำหลายสายไม่อาจดับเพลิงรัก

แม่น้ำไม่อาจพัดพาความรักไปได้

หากใครทุ่มเททรัพย์สินจนหมดตัว

เพื่อแลกกับความรัก

ไม่แคล้วถูกดูหมิ่นดูแคลน

เพื่อน

8เรามีน้องสาวเล็กๆ คนหนึ่ง

ซึ่งทรวงอกยังไม่ขึ้น

เราจะทำอย่างไรดี

หากมีคนมาสู่ขอน้อง?

9หากน้องเป็นกำแพง

เราจะสร้างหอคอยเงินบนนั้น

หากน้องเป็นประตู

เราจะใส่กลอนด้วยไม้สนซีดาร์

หญิงสาว

10ดิฉันเป็นกำแพง

และทรวงอกของดิฉันเหมือนหอคอย

ในสายตาของที่รัก

ดิฉันเป็นเหมือนคนที่นำความอิ่มใจมา

11กษัตริย์โซโลมอนทรงมีสวนองุ่นขนัดหนึ่งที่บาอัลฮาโมน

พระองค์ให้ชาวสวนที่นั่นเช่า

เก็บค่าเช่าเป็นเงิน

หนักคนละพันเชเขล8:11 1 เชเขล คือเงินหนักประมาณ 11.5 กรัม มีค่าเท่ากับค่าแรงสองเดือน เช่นเดียวกับข้อ 12

12แต่สำหรับสวนองุ่นของดิฉันเอง

แล้วแต่ดิฉันจะให้ใคร

ข้าแต่โซโลมอน พันเชเขลนั้นเป็นของพระองค์

และสองร้อยเชเขลเป็นของผู้ดูแลสวน

ชายหนุ่ม

13เธอซึ่งอยู่ในอุทยาน รายรอบด้วยหมู่เพื่อนๆ

ขอให้ผมได้ยินเสียงของคุณ!

หญิงสาว

14มาเถิด ที่รักของดิฉัน ขอให้คุณเป็นเหมือนละมั่ง

หรือกวางหนุ่มบนภูเขาที่เต็มไปด้วยเครื่องเทศเถิด