ማሕልየ መሓልይ 4 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ማሕልየ መሓልይ 4:1-16

ሙሽራው

1ውዴ ሆይ፤ እንዴት ውብ ነሽ!

እንዴትስ ያለሽ ቈንጆ ነሽ

ከመሸፈኛሽ ውስጥ ያሉት ዐይኖችሽ

እንደ ርግብ ዐይኖች ናቸው፤

ጠጕርሽም ከገለዓድ ተራራ እንደሚወርድ፣

የፍየል መንጋ ነው።

2ጥርሶችሽ ወዲያው ተሸልተው፣

ከመታጠቢያ እንደ ወጡ የበግ መንጋ ናቸው፤

ሁሉም መንታ መንታ የወለዱ፣

ከመካከላቸውም መካን የሌለባቸው ናቸው።

3ከንፈሮችሽ ቀይ የሐር ፈትል ይመስላሉ፤

አፍሽም ውብ ነው፤

ከመሸፈኛሽ ውስጥ ያሉት ጕንጮችሽ፣

ለሁለት የተከፈለ ሮማን ይመስላሉ።

4ዐንገትሽ አምሮ4፥4 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም የተሠራውን

በላዩም የጦረኞች ጋሻዎች ሁሉ ያሉበትን፣

ሺሕ ጋሻዎች የተንጠለጠሉበትን፣

የዳዊትን የመጠበቂያ ማማ ይመስላል።

5ሁለቱ ጡቶችሽ መንታ ሆነው የተወለዱ፣

በውብ አበቦች መካከልም የተሰማሩ፣

ሁለት የሚዳቋ ግልገሎችን ይመስላሉ።

6ጎሕ ከመቅደዱ በፊት፣

ጥላውም ሳይሸሽ፣

ወደ ከርቤ ተራራ፣

ወደ ዕጣኑም ኰረብታ እወጣለሁ።

7ውዴ ሆይ፤ ሁለንተናሽ ውብ ነው፤

እንከንም አይወጣልሽም።

8ሙሽራዬ ሆይ፤ ከሊባኖስ አብረሽኝ ነዪ፤

አዎን ከሊባኖስ አብረሽኝ ነዪ፤

ከአንበሶች ዋሻ፣

ከነብሮች ተራራ፣

ከኤርሞን ራስ፣ ከሳኔር ጫፍ፣

ከአማና ዐናት ውረጂ።

9እኅቴ ሙሽራዬ፣ ልቤን ሰርቀሽዋል፤

በአንድ አፍታ እይታሽ፣

ከሐብልሽም በአንዱ ዕንቍ፣

ልቤን ሰርቀሽዋል።

10እኅቴ ሙሽራዬ፣ ፍቅርሽ እንዴት ደስ ያሰኛል!

ፍቅርሽ ከወይን ጠጅ ይልቅ ምንኛ

የሚያረካ ነው፤

የሽቱሽም መዐዛ ከቅመም ሁሉ ይልቅ የቱን ያህል ይበልጥ!

11ሙሽራዬ ሆይ፤ ከንፈሮችሽ የማር ወለላ ያንጠባጥባሉ፤

ከአንደበትሽም ወተትና ማር

ይፈልቃል፤

የልብስሽም መዐዛ እንደ ሊባኖስ ሽታ ነው።

12እኅቴ ሙሽራዬ፤ የታጠረ የአትክልት ቦታ፣

ዙሪያውን የተከበበ ምንጭ፣ የታተመም ፏፏቴ ነሽ።

13ተክልሽ ሮማን፣

ምርጥ ፍሬዎች፣

ሄናና ናርዶስ ያሉበት ነው።

14እንዲሁም ናርዶስና ቀጋ፣

ጠጅ ሣርና ቀረፋ፣

የተለያዩ የዕጣን ዛፎች፣

ከርቤና እሬት፣

ምርጥ ቅመሞች ሁሉ አሉበት።

15አንቺ4፥15 ወይም እኔ ሙሽራዪቱ የተናገረችው የአትክልት ቦታ ፏፏቴ፣

ከሊባኖስ የሚወርድ፣

የፈሳሽ ውሃ ጕድጓድ ነሽ።

ሙሽራዪቱ

16የሰሜን ነፋስ ሆይ፤ ንቃ፤

የደቡብም ነፋስ ሆይ፤ ና!

መዐዛው ያውድ ዘንድ፣

በአትክልት ቦታዬ ላይ ንፈስ፤

ውዴ ወደ አትክልት ቦታው ይግባ፤

ምርጥ ፍሬዎቹንም ይብላ።

New International Version – UK

Song of Songs 4:1-16

He

1How beautiful you are, my darling!

Oh, how beautiful!

Your eyes behind your veil are doves.

Your hair is like a flock of goats

descending from the hills of Gilead.

2Your teeth are like a flock of sheep just shorn,

coming up from the washing.

Each has its twin;

not one of them is alone.

3Your lips are like a scarlet ribbon;

your mouth is lovely.

Your temples behind your veil

are like the halves of a pomegranate.

4Your neck is like the tower of David,

built with courses of stone4:4 The meaning of the Hebrew for this phrase is uncertain.;

on it hang a thousand shields,

all of them shields of warriors.

5Your breasts are like two fawns,

like twin fawns of a gazelle

that browse among the lilies.

6Until the day breaks

and the shadows flee,

I will go to the mountain of myrrh

and to the hill of incense.

7You are altogether beautiful, my darling;

there is no flaw in you.

8Come with me from Lebanon, my bride,

come with me from Lebanon.

Descend from the crest of Amana,

from the top of Senir, the summit of Hermon,

from the lions’ dens

and the mountain haunts of leopards.

9You have stolen my heart, my sister, my bride;

you have stolen my heart

with one glance of your eyes,

with one jewel of your necklace.

10How delightful is your love, my sister, my bride!

How much more pleasing is your love than wine,

and the fragrance of your perfume

more than any spice!

11Your lips drop sweetness as the honeycomb, my bride;

milk and honey are under your tongue.

The fragrance of your garments

is like the fragrance of Lebanon.

12You are a garden locked up, my sister, my bride;

you are a spring enclosed, a sealed fountain.

13Your plants are an orchard of pomegranates

with choice fruits,

with henna and nard,

14nard and saffron,

calamus and cinnamon,

with every kind of incense tree,

with myrrh and aloes

and all the finest spices.

15You are4:15 Or I am (spoken by She) a garden fountain,

a well of flowing water

streaming down from Lebanon.

She

16Awake, north wind,

and come, south wind!

Blow on my garden,

that its fragrance may spread everywhere.

Let my beloved come into his garden

and taste its choice fruits.