ሚክያስ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 5:1-15

ከቤተ ልሔም ገዥ እንደሚመጣ የተሰጠ ተስፋ

1አንቺ የጭፍሮች ከተማ ሆይ፤

ጭፍሮችሽን አሰልፊ5፥1 ወይም አንቺ የተቀጠርሽ ከተማ ሆይ፤ ቅጥርሽን አጥብቂ

ከበባ ተደርጎብናልና።

የእስራኤልን ገዥ፣

ጕንጩን በበትር ይመቱታል።

2“አንቺ ግን፣ ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፤

ከይሁዳ ነገዶች5፥2 ወይም ገዦች መካከል ትንሿ ብትሆኚም፣

አመጣጡ ከጥንት፣5፥2 ወይም ከቀድሞ ቀናት

ከቀድሞ ዘመን5፥2 ዕብራይስጡ አወጣጡ ይላል ወይም ከዘላለም የሆነ የሆነ፣

የእስራኤል ገዥ፣

ከአንቺ ይወጣልኛል።”

3ስለዚህ ወላዲቱ አምጣ እስክትገላገል ድረስ፣

እስራኤል ትተዋለች፤

የተቀሩት ወንድሞቹም፣

ተመልሰው ከእስራኤላውያን ጋር ይቀላቀላሉ።

4በእግዚአብሔር ኀይል፣

በአምላኩ በእግዚአብሔር ስም ታላቅነት፣

ጸንቶ ይቆማል፤ መንጋውንም ይጠብቃል።

በዚያን ጊዜ ኀያልነቱ እስከ ምድር ዳርቻ ስለሚደርስ፣

ተደላድለው ይኖራሉ።

5እርሱም ሰላማቸው ይሆናል።

ትድግናና ጥፋት

አሦራዊ ምድራችንን ሲወርር፣

ምሽጎቻችንንም ጥሶ ሲገባ፣

ሰባት እረኞችን፣

እንዲያውም ስምንት አለቆችን እናስነሣበታለን።

6የአሦርን ምድር በሰይፍ፣

የናምሩድን ምድር5፥6 ወይም ናምሩድን በመግቢያው በር በተመዘዘ ሰይፍ ይገዛሉ5፥6 ወይም ያፈርሳሉ

አሦራዊው ምድራችንን ሲወርር፣

ዳር ድንበራችንን ሲደፍር፣

እርሱ ነጻ ያወጣናል።

7የያዕቆብ ትሩፍ፣

በብዙ አሕዛብ መካከል

ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደሚወርድ ጠል፣

በሣር ላይ እንደሚጥል ካፊያ፣

ሰውን እንደማይጠብቅ፣

የሰውንም ልጆች ተስፋ እንደማያደርግ ሰው ይሆናል።

8በዱር አራዊት መካከል እንዳለ አንበሳ፣

በእግሩ እየጨፈላለቀ እንደሚሄድ፣

የሰበረውን ማንም ሊነጥቀው እንደማይችል፣

በበግ መንጋ መካከል እንዳለ፣

እንደ ደቦል አንበሳ ሁሉ፣

የያዕቆብም ትሩፍ፣ በአሕዛብ ዘንድ፣ በብዙም ሕዝብ መካከል እንደዚሁ ይሆናል።

9እጅህ በጠላቶችህ ላይ በድል አድራጊነት ከፍ ከፍ ትላለች፤

ጠላቶችህም ሁሉ ይጠፋሉ።

10“በዚያን ጊዜ” ይላል እግዚአብሔር

“ፈረሶቻችሁን ከመካከላችሁ አጠፋለሁ፤

ሠረገሎቻችሁን እደመስሳለሁ።

11የምድራችሁን ከተሞች እደመስሳለሁ፤

ምሽጎቻችሁንም ሁሉ አፈርሳለሁ።

12ጥንቈላችሁን አጠፋለሁ፤

ከእንግዲህም አታሟርቱም።

13የተቀረጹ ምስሎቻችሁን፣

የማምለኪያ ዐምዶቻችሁንም ከመካከላችሁ አጠፋለሁ፤

ከእንግዲህ ለእጃችሁ ሥራ

አትሰግዱም።

14የአሼራ ምስልን ዐምድ5፥14 አሼራ የተባለችው አምላክ ትእምርት ነው። ከመካከላችሁ እነቅላለሁ፤

ከተሞቻችሁንም እደመስሳለሁ።

15ያልታዘዙኝን አሕዛብ፣

በቍጣና በመዓት እበቀላቸዋለሁ።”

Thai New Contemporary Bible

มีคาห์ 5:1-15

ผู้ปกครองตามพระสัญญาจะมาจากเบธเลเฮม

1นครแห่งกองทหารเอ๋ย จัดทัพเถิด5:1 หรือนครแห่งปราการเอ๋ย จงเสริมกำแพงของเจ้าเถิด

เพราะศัตรูมาล้อมเมืองของเราแล้ว

เขาจะเอาไม้เท้าฟาดแก้มผู้ปกครองของอิสราเอล

2“ส่วนเจ้า เบธเลเฮม เอฟราธาห์เอ๋ย

ถึงแม้เจ้าเป็นคนเล็กน้อยในหมู่ตระกูลต่างๆ5:2 หรือผู้ปกครองของยูดาห์

แต่จะมีผู้หนึ่งออกมาจากเจ้าเพื่อเรา

เป็นผู้ที่จะครอบครองอิสราเอล

ผู้นั้นมีที่มา5:2 ภาษาฮีบรูว่าผู้นั้นออกไปจากจากอดีตกาล

จากโบราณกาล5:2 หรือจากนิรันดร์กาล

3ฉะนั้น อิสราเอลจะถูกทอดทิ้ง

จวบจนเมื่อถึงเวลาที่ผู้หญิงซึ่งกำลังเจ็บครรภ์นั้นคลอดบุตร

และพี่น้องอื่นๆ ของบุคคลนั้น

กลับมาสมทบกับชนอิสราเอล

4เขาจะยืนหยัดเลี้ยงดูฝูงแกะของเขา

โดยกำลังขององค์พระผู้เป็นเจ้า

โดยบารมีแห่งพระนามของพระยาห์เวห์พระเจ้าของเขา

และพวกเขาจะมีชีวิตอยู่อย่างมั่นคงปลอดภัย

เพราะความยิ่งใหญ่ของเขาผู้นั้นจะแผ่ถึงสุดปลายแผ่นดินโลก

5และเขาจะนำความสงบสุขมาให้พวกเขา

การช่วยกู้และความย่อยยับ

เมื่อคราวอัสซีเรียรุกรานดินแดนของเรา

และกรีธาทัพผ่านป้อมของเรา

เราจะตั้งคนเลี้ยงแกะเจ็ดแปดคน

คือตั้งเหล่าผู้นำขึ้นมาสู้กับเขา

6พวกเขาจะปกครอง5:6 หรือบดขยี้ดินแดนอัสซีเรียด้วยดาบ

ปกครองดินแดนของนิมโรดด้วยดาบซึ่งชักออก5:6 หรือนิมโรดในประตูเมืองของมัน

ผู้นั้นจะกอบกู้เราจากอัสซีเรีย

ซึ่งมารุกรานดินแดนของเรา

และกรีธาทัพเข้ามาในเขตแดนของเรา

7คนหยิบมือที่เหลือของยาโคบ

จะอยู่ท่ามกลางชนชาติทั้งหลาย

เหมือนน้ำค้างจากองค์พระผู้เป็นเจ้า

เหมือนสายฝนโปรยปรายลงบนหญ้า

ซึ่งไม่ต้องรอคอย

หรือพึ่งพามนุษย์

8คนหยิบมือที่เหลือของยาโคบจะอยู่ในหมู่ประชาชาติ

อยู่ท่ามกลางชนชาติต่างๆ

ดั่งราชสีห์ในหมู่สัตว์ป่า

เหมือนสิงห์หนุ่มในหมู่ฝูงแกะ

ซึ่งเหยียบย่ำและขยี้ขณะย่างไป

โดยไม่มีใครช่วยได้

9เจ้าจะชูมือขึ้นด้วยชัยชนะเหนือข้าศึก

ศัตรูทั้งปวงของเจ้าจะถูกทำลาย

10องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า

“ในวันนั้นเราจะกำจัดม้าให้หมดไปจากพวกเจ้า

และทำลายรถม้าศึกของเจ้า

11เราจะทำลายเมืองต่างๆ ในดินแดนของเจ้า

และทำลายที่มั่นทั้งปวงของเจ้า

12เราจะกำจัดพวกแม่มดของเจ้า

และเจ้าจะไม่ร่ายเวทมนตร์คาถาอีกต่อไป

13เราจะทำลายเทวรูปสลัก

และหินศักดิ์สิทธิ์ท่ามกลางพวกเจ้าให้หมดไป

เจ้าจะไม่หมอบกราบ

สิ่งที่มือของเจ้าทำขึ้นอีกต่อไป

14เราจะรื้อถอนเสาเจ้าแม่อาเชราห์ที่อยู่ท่ามกลางพวกเจ้าออกไป

และทำลายเมืองต่างๆ ของเจ้า

15เราจะแก้แค้นด้วยความพิโรธโกรธกริ้ว

แก่ชนชาติต่างๆ ซึ่งไม่เชื่อฟังเรา”