ሚክያስ 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 4:1-13

የእግዚአብሔር ተራራ

1በመጨረሻው ዘመን፣

የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተራራ፣

ከተራሮች ልቆ ይታያል፤

ከኰረብቶች በላይ ከፍ ይላል፤

ሕዝቦችም ወደ እርሱ ይጐርፋሉ።

2ብዙ አሕዛብ መጥተው እንዲህ ይላሉ፤

“ኑ፤ ወደ እግዚአብሔር ተራራ፣

ወደ ያዕቆብ አምላክ ቤት እንሂድ፤

በመንገዱ እንድንሄድ፣

መንገዱን ያስተምረናል።”

ሕግ ከጽዮን ይመጣል፤

የእግዚአብሔርም ቃል ከኢየሩሳሌም።

3እርሱ በብዙ ሕዝብ መካከል ይፈርዳል፤

በሩቅና በቅርብ ባሉ ኀያላን መንግሥታት መካከል ያለውን ግጭት ያቆማል፤

ሰይፋቸውን ማረሻ፣

ጦራቸውንም ማጭድ ያደርጉታል።

አንዱ መንግሥት በሌላው መንግሥት ላይ ሰይፍ አያነሣም፤

ከእንግዲህም የጦርነት ትምህርት አይማሩም።

4እያንዳንዱ ሰው በገዛ ወይኑ ሥር፣

ከገዛ በለሱም ሥር ይቀመጣል፤

የሚያስፈራቸው አይኖርም፤

የእግዚአብሔር ጸባኦት አፍ ተናግሯልና።

5አሕዛብ ሁሉ፣

በአማልክታቸው ስም ይሄዳሉ፤

እኛ ግን በአምላካችን በእግዚአብሔር ስም፣

ከዘላለም እስከ ዘላለም እንሄዳለን።

የእግዚአብሔር ዕቅድ

6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በዚያች ቀን ሽባውን እሰበስባለሁ፤

ስደተኞችንና ለሐዘን ያደረግኋቸውን፣

ወደ አንድ ቦታ አመጣለሁ።

7የሽባዎችን ትሩፍ፣

የተገፉትንም ብርቱ ሕዝብ አደርጋለሁ፤

ከዚያች ቀን አንሥቶ እስከ ዘላለም፣

እግዚአብሔር በጽዮን ተራራ በእነርሱ ላይ ይነግሣል።

8አንተ የመንጋው መጠበቂያ ማማ ሆይ፤

የጽዮን ሴት ልጅ ዐምባ4፥8 ወይም ኰረብታ ሆይ፤

የቀድሞው ግዛትህ ይመለስልሃል፤

የመንግሥትም ሥልጣን ለኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ይሆናል።”

9አሁንስ እንደዚህ የምትጮኺው ለምንድን ነው?

ንጉሥ የለሽምን?

ምጥ እንደ ያዛት ሴት የተጨነቅሽው፣

መካሪሽ ስለ ጠፋ ነውን?

10የጽዮን ሴት ልጅ ሆይ፤

ምጥ እንደ ያዛት ሴት ተጨነቂ፤

አሁንስ ከከተማ ወጥተሽ፣

በሜዳ ላይ መስፈር አለብሽና፤

ወደ ባቢሎን ትሄጃለሽ፤

በዚያ ከጠላት እጅ ትድኛለሽ።

እግዚአብሔር በዚያ፣

ከጠላቶችሽ ይታደግሻል።

11አሁን ግን ብዙ አሕዛብ፣

በአንቺ ላይ ተሰብስበዋል፤

እነርሱም፣ “የረከሰች ትሁን፤

ዐይናችንም ጽዮንን መዘባበቻ አድርጎ ይያት” ይላሉ።

12ነገር ግን የእግዚአብሔርን ሐሳብ አያውቁም፤

በዐውድማ ላይ እንደ ነዶ የሚሰበስባቸውን፣

የእርሱን ዕቅድ አያስተውሉም።

13“የጽዮን ልጅ ሆይ፤ ተነሥተሽ አበራዪ፤

የብረት ቀንድ እሰጥሻለሁና፤

የናስ ሰኰና እሰጥሻለሁ፤

አሕዛብንም ታደቅቂአቸዋለሽ።”

በግፍ ያግበሰበሱትን ትርፍ ለእግዚአብሔር

ሀብታቸውንም ለምድር ሁሉ ጌታ ታቀርቢአለሽ።

Thai New Contemporary Bible

มีคาห์ 4:1-13

ภูเขาขององค์พระผู้เป็นเจ้า

(อสย.2:1-4)

1ในบั้นปลาย

ภูเขาที่พระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าตั้งอยู่จะได้รับการสถาปนา

ให้เป็นเอกในหมู่ภูเขาทั้งหลาย

จะได้รับการเชิดชูเหนือบรรดาเนินเขา

และชนชาติต่างๆ จะหลั่งไหลไปที่นั่น

2ประชาชาติมากมายจะมาและกล่าวว่า

“มาเถิด ให้เราขึ้นไปบนภูเขาขององค์พระผู้เป็นเจ้า

ไปยังพระนิเวศของพระเจ้าของยาโคบ

พระองค์จะทรงสอนพระมรรคาของพระองค์แก่เรา

เพื่อเราจะดำเนินในวิถีทางของพระองค์”

บทบัญญัติจะออกมาจากศิโยน

พระวจนะขององค์พระผู้เป็นเจ้าจะออกมาจากเยรูซาเล็ม

3พระองค์จะทรงตัดสินความระหว่างชนชาติทั้งหลาย

และยุติกรณีพิพาทให้บรรดาชาติมหาอำนาจทั่วแดน

พวกเขาจะตีดาบให้เป็นผาลไถนา

และตีหอกให้เป็นขอลิด

ชนชาติต่างๆ จะเลิกรบราฆ่าฟันกัน

ทั้งจะไม่มีการฝึกรบอีกต่อไป

4ทุกคนจะนั่งอยู่ใต้เถาองุ่นของตน

และใต้ต้นมะเดื่อของตน

และจะไม่มีใครทำให้เขากลัว

เพราะพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ได้ตรัสไว้แล้ว

5ชนชาติทั้งปวงอาจจะดำเนิน

ในนามของเทพเจ้าของตน

ส่วนเราจะดำเนินในพระนามพระยาห์เวห์พระเจ้าของเราตลอดนิรันดร์

แผนการขององค์พระผู้เป็นเจ้า

6องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า

“ในวันนั้น เราจะรวบรวมคนขาพิการ

เราจะรวบรวมบรรดาเชลย

ตลอดจนบรรดาคนที่เราให้พบกับความทุกข์โศก

7เราจะให้คนขาพิการเป็นคนที่เหลืออยู่

ให้คนที่ถูกเนรเทศเป็นชาติที่แข็งแกร่ง

องค์พระผู้เป็นเจ้าจะปกครองพวกเขาในภูเขาศิโยน

ตั้งแต่วันนั้นตราบชั่วนิรันดร์

8ส่วนเจ้าผู้เป็นหอสังเกตการณ์ของฝูงแกะ

เป็นที่มั่น4:8 หรือเนินเขาของธิดาแห่งศิโยน4:8 คือ ชาวเยรูซาเล็ม เช่นเดียวกับข้อ 10 และ 13

อำนาจดั้งเดิมจะกลับคืนมาเป็นของเจ้า

ธิดาแห่งเยรูซาเล็ม4:8 คือ ชาวเยรูซาเล็มจะได้รับอำนาจครอบครอง”

9เหตุใดเจ้าจึงร้องเสียงดัง

เจ้าไม่มีกษัตริย์หรือ?

ที่ปรึกษาของเจ้าย่อยยับไปแล้วหรือ?

เจ้าจึงเจ็บปวดรวดร้าวเหมือนผู้หญิงกำลังคลอดลูก

10ธิดาแห่งศิโยนเอ๋ย จงทุรนทุรายด้วยความเจ็บปวดแสนสาหัส

เหมือนผู้หญิงที่กำลังคลอดลูก

เพราะบัดนี้เจ้าต้องจากเมือง

ไปตั้งค่ายอยู่กลางทุ่ง

เจ้าจะไปยังบาบิโลน

เจ้าจะได้รับการช่วยเหลือที่นั่น

องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงไถ่เจ้า

ออกจากมือของศัตรูของเจ้าที่นั่น

11แต่บัดนี้หลายชนชาติ

รวมตัวกันมารบกับเจ้า

เขากล่าวว่า “ให้ศิโยนถูกย่ำยี

ให้ตาของเราได้ดูศิโยนด้วยความสะใจ!”

12แต่เขาไม่รู้

พระดำริขององค์พระผู้เป็นเจ้า

เขาไม่เข้าใจแผนการของพระองค์

ผู้ทรงรวบรวมเขาเหมือนรวบรวมฟ่อนข้าวมาสู่ลานนวดข้าว

13“ธิดาแห่งศิโยนเอ๋ย ลุกขึ้นนวดข้าวเถิด

เพราะเราจะให้เจ้ามีเขาเหล็ก

เราจะให้เจ้ามีกีบทองสัมฤทธิ์

และเจ้าจะบดขยี้ชนหลายชาติให้เป็นชิ้นเล็กชิ้นน้อย”

พวกท่านจะถวายสิ่งที่เขาได้มาโดยไม่ชอบธรรมนั้นแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า

ถวายความมั่งคั่งของพวกเขาแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าแห่งสากลโลก