ሚክያስ 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 2:1-13

የእግዚአብሔርና የሰው ዕቅድ

1ክፉ ለመሥራት ለሚያቅዱ፣

በመኝታቸው ሳሉ ተንኰል ለሚያውጠነጥኑ ወዮላቸው!

ሲነጋ በማለዳ ይፈጽሙታል፤

የሚያደርጉበት ኀይል በእጃቸው ነውና።

2ዕርሻ ይመኛሉ፤ ይይዙታልም፤

ቤት ይመኛሉ፤ ይወስዱታልም፤

የሰውን ቤት፣

የባልንጀራን ርስት አታልለው ይወስዳሉ።

3ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ በዚያ ሕዝብ ላይ ጥፋት ላመጣ ዐቅጃለሁ፤

ከዚህም ለማምለጥ አትችሉም።

ከእንግዲህ በትዕቢት አትመላለሱም፤

የመከራ ጊዜ ይሆናልና።

4በዚያ ቀን ሰዎች ይሣለቁባችኋል፤

በሐዘን እንጕርጕሮ እንዲህ እያሉ ያፌዙባችኋል፤

‘እኛ ፈጽሞ ጠፍተናል፤

የወገኔ ርስት ተከፋፍሏል።

ከእኔ ነጥቆ ወስዶ፣

ዕርሻዎቻችንን ላሸነፉን አከፋፈለ።’ ”

5ስለዚህ በእግዚአብሔር ጉባኤ ውስጥ፣

መሬት በዕጣ የሚያካፍል ማንም አይኖርም።

ሐሰተኞች ነቢያት

6ነቢያቶቻቸው፣ “ትንቢት አትናገርብን፤

ስለ እነዚህ ነገሮች ትንቢት አትናገር፤

ውርደት አይደርስብንም” ይላሉ።

7የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ እንዲህ ሊባል ይገባልን?

የእግዚአብሔር መንፈስ የማይታገሥ ነውን?

እንዲህ ያሉ ነገሮችንስ ያደርጋልን?”

“መንገዱ ቀና ለሆነ፣

ቃሌ መልካም አያደርግምን?

8በመጨረሻ በሕዝቤ ላይ ጠላት ሆናችሁ

ተነሣችሁ፤

የጦርነት ሐሳብ ሳይኖራቸው፣

በሰላም ከሚያልፉ ሰዎች ላይ

ማለፊያ መጐናጸፊያ ገፈፋችሁ።

9ከሚወድዱት ቤታቸው፣

የሕዝቤን ሴቶች አስወጣችኋቸው፤

ክብሬን ከልጆቻቸው

ለዘላለም ወሰዳችሁ።

10ተነሡና ከዚያ ሂዱ፤

ይህ ማረፊያ ቦታችሁ አይደለምና፤

ምክንያቱም ረክሷል፤

ክፉኛም ተበላሽቷል።

11ሐሰተኛና አታላይ ሰው መጥቶ፣

‘ስለ ብዙ የወይን ጠጅና ስለሚያሰክር መጠጥ ትንቢት እነግራችኋለሁ’ ቢል፣

ለዚህ ሕዝብ ተቀባይነት ያለው ነቢይ ይሆናል።

የትድግና ተስፋ

12“ያዕቆብ ሆይ፤ በርግጥ ሁላችሁንም እሰበስባለሁ፤

የእስራኤልንም ትሩፍ በአንድነት አመጣለሁ፤

በጕረኖ ውስጥ እንዳሉ በጎች በመሰማሪያ ላይ እንዳለ መንጋ በአንድነት

እሰበስባቸዋለሁ፤

ቦታውም በሕዝብ ይሞላል።

13የሚሰብረው ወጥቶ በፊታቸው ይሄዳል፤

እነርሱም በሩን በመስበር ወጥተው ይሄዳሉ።

እግዚአብሔር እየመራቸው፣

ንጉሣቸው ቀድሟቸው ይሄዳል።”

Thai New Contemporary Bible

มีคาห์ 2:1-13

แผนการของมนุษย์และแผนงานของพระเจ้า

1วิบัติแก่บรรดาผู้ที่วางแผนชั่วร้าย

บรรดาผู้ที่คิดอุบายชั่วร้ายขณะนอนอยู่บนเตียง!

ครั้นรุ่งเช้าก็ดำเนินการตามแผนนั้น

เพราะอยู่ในอำนาจที่เขาจะทำได้

2เขาโลภอยากได้ที่ดินก็ยึดเอา

อยากได้บ้านก็ริบไป

เขาโกงบ้าน

โกงมรดกของเพื่อนมนุษย์

3ฉะนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

“เรากำลังวางแผนนำภัยพิบัติมาให้แก่คนพวกนี้

ซึ่งพวกเจ้าไม่มีทางเอาตัวรอดไปได้เลย

พวกเจ้าจะไม่เดินอย่างหยิ่งทะนงอีกต่อไป

เพราะมันจะเป็นวาระแห่งความพินาศ

4ในวันนั้นผู้คนจะเยาะเย้ยพวกเจ้า

เขาจะถากถางพวกเจ้าด้วยเพลงโศกบทนี้ว่า

‘เราย่อยยับป่นปี้

ข้าวของในกรรมสิทธิ์ของพี่น้องร่วมชาติถูกยึดไปแบ่งกัน

พระองค์ทรงริบไปจากเราแล้ว!

พระองค์ทรงมอบที่ดินของเราให้แก่บรรดาคนทรยศ’ ”

5ฉะนั้นพวกเจ้าจะไม่มีใครสักคนในชุมชนขององค์พระผู้เป็นเจ้า

มาจับสลากแบ่งดินแดน

ผู้เผยพระวจนะเท็จ

6บรรดาผู้เผยพระวจนะของเขากล่าวว่า

“อย่าเผยพระวจนะ

อย่าพยากรณ์เรื่องเหล่านี้

ความอัปยศอดสูจะมาไม่ถึงเรา”

7พงศ์พันธุ์ยาโคบเอ๋ย ควรหรือที่จะพูดกันว่า

“พระวิญญาณขององค์พระผู้เป็นเจ้ากริ้วหรือ?

พระองค์ทรงกระทำสิ่งเหล่านี้หรือ?”

“ถ้อยคำของเราไม่ได้เป็นผลดี

แก่บรรดาผู้ประพฤติอย่างชอบธรรมหรือ?

8เมื่อไม่นานมานี้ประชากรของเราได้ลุกขึ้น

เหมือนเป็นศัตรู

พวกเจ้าริบเอาเสื้อคลุมอย่างดี

จากผู้ที่ผ่านไปโดยไม่ระมัดระวัง

เหมือนคนที่เพิ่งกลับมาจากการรบ

9พวกเจ้าขับไล่ผู้หญิงในหมู่ประชากรให้ออกไป

จากบ้านอันผาสุกของเขา

พวกเจ้าริบพรของเราไป

จากลูกหลานของเขาตลอดกาล

10ลุกขึ้น ไปให้พ้น!

เพราะนี่ไม่ใช่ที่พักของพวกเจ้า

เนื่องจากมันเป็นมลทิน

มันพังทลายเกินกว่าจะแก้ไข

11หากคนโกหกและคนหลอกลวงมาพูดว่า

‘ข้าพเจ้าจะพยากรณ์ว่าท่านจะมีเหล้าองุ่นและเบียร์เหลือเฟือ’

เขาก็จะเป็นผู้พยากรณ์ที่ชนชาตินี้ต้องการ!

ทรงสัญญาจะช่วยกอบกู้

12“ยาโคบเอ๋ย เราจะรวบรวมเจ้าทั้งหมดอย่างแน่นอน

เราจะรวบรวมชนหยิบมือที่เหลือของอิสราเอลกลับคืนมาอย่างแน่นอน

เราจะพาพวกเขามาเหมือนแกะในคอก

เหมือนฝูงสัตว์ในทุ่งหญ้า

ที่นั่นจะคลาคล่ำด้วยผู้คน

13ผู้เบิกทางจะขึ้นหน้านำเขาไป

พวกเขาจะผ่านออกไปทางประตู

กษัตริย์ของเขาจะเสด็จขึ้นหน้าพวกเขา

องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงนำหน้าพวกเขาไป”