ሚክያስ 2 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 2:1-13

የእግዚአብሔርና የሰው ዕቅድ

1ክፉ ለመሥራት ለሚያቅዱ፣

በመኝታቸው ሳሉ ተንኰል ለሚያውጠነጥኑ ወዮላቸው!

ሲነጋ በማለዳ ይፈጽሙታል፤

የሚያደርጉበት ኀይል በእጃቸው ነውና።

2ዕርሻ ይመኛሉ፤ ይይዙታልም፤

ቤት ይመኛሉ፤ ይወስዱታልም፤

የሰውን ቤት፣

የባልንጀራን ርስት አታልለው ይወስዳሉ።

3ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ በዚያ ሕዝብ ላይ ጥፋት ላመጣ ዐቅጃለሁ፤

ከዚህም ለማምለጥ አትችሉም።

ከእንግዲህ በትዕቢት አትመላለሱም፤

የመከራ ጊዜ ይሆናልና።

4በዚያ ቀን ሰዎች ይሣለቁባችኋል፤

በሐዘን እንጕርጕሮ እንዲህ እያሉ ያፌዙባችኋል፤

‘እኛ ፈጽሞ ጠፍተናል፤

የወገኔ ርስት ተከፋፍሏል።

ከእኔ ነጥቆ ወስዶ፣

ዕርሻዎቻችንን ላሸነፉን አከፋፈለ።’ ”

5ስለዚህ በእግዚአብሔር ጉባኤ ውስጥ፣

መሬት በዕጣ የሚያካፍል ማንም አይኖርም።

ሐሰተኞች ነቢያት

6ነቢያቶቻቸው፣ “ትንቢት አትናገርብን፤

ስለ እነዚህ ነገሮች ትንቢት አትናገር፤

ውርደት አይደርስብንም” ይላሉ።

7የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ እንዲህ ሊባል ይገባልን?

የእግዚአብሔር መንፈስ የማይታገሥ ነውን?

እንዲህ ያሉ ነገሮችንስ ያደርጋልን?”

“መንገዱ ቀና ለሆነ፣

ቃሌ መልካም አያደርግምን?

8በመጨረሻ በሕዝቤ ላይ ጠላት ሆናችሁ

ተነሣችሁ፤

የጦርነት ሐሳብ ሳይኖራቸው፣

በሰላም ከሚያልፉ ሰዎች ላይ

ማለፊያ መጐናጸፊያ ገፈፋችሁ።

9ከሚወድዱት ቤታቸው፣

የሕዝቤን ሴቶች አስወጣችኋቸው፤

ክብሬን ከልጆቻቸው

ለዘላለም ወሰዳችሁ።

10ተነሡና ከዚያ ሂዱ፤

ይህ ማረፊያ ቦታችሁ አይደለምና፤

ምክንያቱም ረክሷል፤

ክፉኛም ተበላሽቷል።

11ሐሰተኛና አታላይ ሰው መጥቶ፣

‘ስለ ብዙ የወይን ጠጅና ስለሚያሰክር መጠጥ ትንቢት እነግራችኋለሁ’ ቢል፣

ለዚህ ሕዝብ ተቀባይነት ያለው ነቢይ ይሆናል።

የትድግና ተስፋ

12“ያዕቆብ ሆይ፤ በርግጥ ሁላችሁንም እሰበስባለሁ፤

የእስራኤልንም ትሩፍ በአንድነት አመጣለሁ፤

በጕረኖ ውስጥ እንዳሉ በጎች በመሰማሪያ ላይ እንዳለ መንጋ በአንድነት

እሰበስባቸዋለሁ፤

ቦታውም በሕዝብ ይሞላል።

13የሚሰብረው ወጥቶ በፊታቸው ይሄዳል፤

እነርሱም በሩን በመስበር ወጥተው ይሄዳሉ።

እግዚአብሔር እየመራቸው፣

ንጉሣቸው ቀድሟቸው ይሄዳል።”

New International Version – UK

Micah 2:1-13

Human plans and God’s plans

1Woe to those who plan iniquity,

to those who plot evil on their beds!

At morning’s light they carry it out

because it is in their power to do it.

2They covet fields and seize them,

and houses, and take them.

They defraud people of their homes,

they rob them of their inheritance.

3Therefore, the Lord says:

‘I am planning disaster against this people,

from which you cannot save yourselves.

You will no longer walk proudly,

for it will be a time of calamity.

4In that day people will ridicule you;

they will taunt you with this mournful song:

“We are utterly ruined;

my people’s possession is divided up.

He takes it from me!

He assigns our fields to traitors.” ’

5Therefore you will have no-one in the assembly of the Lord

to divide the land by lot.

False prophets

6‘Do not prophesy,’ their prophets say.

‘Do not prophesy about these things;

disgrace will not overtake us.’

7You descendants of Jacob, should it be said,

‘Does the Lord become2:7 Or Is the Spirit of the Lord impatient?

Does he do such things?’

‘Do not my words do good

to the one whose ways are upright?

8Lately my people have risen up

like an enemy.

You strip off the rich robe

from those who pass by without a care,

like men returning from battle.

9You drive the women of my people

from their pleasant homes.

You take away my blessing

from their children for ever.

10Get up, go away!

For this is not your resting-place,

because it is defiled,

it is ruined, beyond all remedy.

11If a liar and deceiver comes and says,

“I will prophesy for you plenty of wine and beer,”

that would be just the prophet for this people!

Deliverance promised

12‘I will surely gather all of you, Jacob;

I will surely bring together the remnant of Israel.

I will bring them together like sheep in a sheepfold,

like a flock in its pasture;

the place will throng with people.

13The One who breaks open the way will go up before them;

they will break through the gate and go out.

Their King will pass through before them,

the Lord at their head.’